Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 1 December 2012

የእስራኤል ኩባንያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ማኔጅመንት ሊረከብ ነው

-    ሌሎች 50 ኩባንያዎች በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት ለማድረግ ጠይቀዋል
-    እስራኤል በአፍሪካ ኅብረት መድረክ አለማግኘቷ ቅሬታ ፈጥሮባታል

በታደሰ ገብረማርያም
የእስራኤል ኤሌክትሪክ ኩባንያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ማኔጅመንት ተረክቦ ለሦስት ዓመታት ያህል ለመምራት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቅቋል፡፡ ሌሎች ወደ 50 የሚጠጉ የእስራኤል ልዩ ልዩ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ወይም ኢንቨስት ለማድረግ መጠየቃቸውን በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በላይነሽ ዘቫዲያ ገለጹ፡፡

የእስራኤል ኤሌክትሪክ ኩባንያ 20 መሐንዲሶች በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ መጥተው ሥራውን ይጀምራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አምባሳደሯ አስረድተዋል፡፡ የእስራኤል የኤሌክትሪክ ኩባንያ የኮርፖሬሽኑን ማኔጅመንት ለሦስት ዓመታት ለመምራት የሚያስችለውን ሥራ ያገኘው ለዚህ ተብሎ የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ በማሸነፉ መሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን በሁለት እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ የኃይል ሽያጭ፣ የደንበኞች አገልግሎትና አስትዳደራዊ ጉዳዮች ለእስራኤሉ ኩባንያ ይሰጣሉ፡፡ ሁለተኛው ኃይል የማመንጨትና የማስፋፋት ሥራዎች በኮርፖሬሽኑ አማካይነት ይከናወናል፡፡ ከዚህ ቀደም መንግሥት የቀድሞውን ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ማኔጅመንት ለፈረንሳዩ ፍራንስ ቴሌኮም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ሌሎቹ 50 ኩባንያዎች ለመሰማራት የሚፈልጉት በሶላር ኢነርጂ፣ በውኃ ቴክኖሎጂ፣ በመስኖ ልማት፣ በጤናና በሌሎችም በርካታ የልማት ዘርፎች መሆኑን አምባሳደሯ አስረድተው ከኩባንያዎቹ መካከል የተሟላ አቅም፣ ብቃትና የአሠራር ጥራት ያላቸውን ለይቶ ለማወቅ የሚያስችል የማጣራት ሥራ ኤምባሲው በማከናወን ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

12-year-old video released: How Meles crushed his rivals Eyerusalem Araya December 1, 2012








የተለቀቀው ቪዲዮና የፖለቲካ ውጥንቅጡ እንደምታው

(በሕወሓት ውስጥ ከ12 ዓመት በፊት የተፈጠረውን የፖለቲካ ውዝግብ…..የሚያሳየውን ፊልም አሁን ባልታወቁ ወገኖች ተለቆዋል፣ ለረጅም አመት ይህ ፊልም እንዳይታይ ተደርጎ ቆይቶዋል ....... ብዙዎች ትርጉሙን ለማወቅ በመጠየቃቸው....... ወደ አማርኛ ለመመለስ ተሞክሮዋል....... ተርጓሚው የትኛውም ወገን ደጋፊ እንዳልሆነ ይታወቅ.......) ...... by Eyerusalem Araya December 1, 2012
 
በመስሉ እንደሚታየው የመጀመሪያው ተናጋሪ አቶ ገብሩ አስራት ናቸው፣ ይህን አሉ፣ “ የመጣነው ካድሬው ጥሪ ስላደረገልን ነው፣ እየተመለከትን ያለነው ነገር ግልጽ አይደለም፣ ካድሬው የጠራን ያለንን ሃሳብ እንድናቀርብ ነው፣ ከዛ ባሻገር ይህን ስብሰባ በተመለከተ የምንለው ይኖረናል፣ ከዚሁ ጎን ለጎን ያለውን መረጃ ማቅረብ እንችላለን፣ ይህንን ለማለት ነው እዚህ ስብሰባ ላይ የመጣነው፣ * የለም ይህ አያስፈልግም * የምትሉን ከሆነ ግን ሁሉም ነገር አብቅቶለታል ማለት ነው:: ሃሳባችንን ልትሰሙን፣ ስብሰባውንም በተመለከተ ያለንን አቁዋም ከቻላችሁ አዳምጡን:: ይህንን ኢንፎርሜሽን ግልጽ ለማድረግ ነው እዚህ ስብሰባል ላይ የተገኝነው:: ”

Ethiopia: Meles rules from beyond the grave, but for how long? By René Lefort, Open Democracy

The trade-off offered by authoritarianism to its client-constituents is security and high growth rates. After Meles challenges may force change, or build the case domestically for a new strong man.
Meles Zenawi, the former Prime Minister of Ethiopia, has been dead for around three months. But the “Melesmania” personality cult, though discreet in his lifetime, shows no sign of fading. From giant portraits in the streets to stickers on the windscreens of almost any vehicle, a smiling Meles is still everywhere.
The sudden death of Meles shook the whole of Ethiopia. The shock quickly gave way to fear of an unknown and threatening future.
The regime did everything to exploit this fear for its own benefit. It has issued continuous calls for the nation to unite around the memory of the dead leader and, above all, around the project he designed and imposed with an iron hand. The new Prime Minister, Hailemariam Selassie, endlessly repeats that he will pursue “Meles’s legacy without any change”. He has replaced not a single cabinet minister. It could be said that the regime is running on autopilot, with the Meles software driving the leadership computer. Plunged into disarray, the governing team is hanging on to this software like a lifebelt. Why?
The making of Melesmania
Until the crisis of 2001, the handful of leaders of the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF), the dominant force in the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) in power since 1991,[1] worked in a remarkably collective way.  Within this group Meles was – and not always – the primus inter pares, surrounded by strong, clever and articulate figures united by a radical Marxism. The crisis culminated in the expulsion of most of these figures, in a massive purge and finally in a threefold power shift.
The first shift saw Meles emerge as the unchallenged supremo, moving quickly to clip the wings of the few leaders who seemed to be acquiring a solid political base. He promoted only those whose loyalty he considered unshakeable, whose positions depended entirely on his goodwill, people like Hailemariam Dessalegn. Radiating outwards from a first circle of “advisers”, almost all Tigrayan, all the lines of real power penetrated down to the base of the State apparatus, whether federal or regional,[2]  to the Party and to whole sectors of the economy.

Friday 30 November 2012

PM Hailemariam: Ethiopian troops will remain in Somalia

Ethiopian troops will remain in Somalia until African Union forces fighting Islamists can take over, Prime Minister Hailemariam Desalegn said Wednesday, as he met with his Somali counterpart.
“We are waiting for AMISOM (African Union Mission in Somalia) force to come and replace us, and until we get that assurance then we will be waiting there,” he told reporters.
Ethiopian troops in Somalia

Hailemariam, speaking alongside newly elected Somali President Hassan Sheikh Mohamud, on his first official visit to the Ethiopian capital, gave no timeline for a pull out of troops.
Mohamud said that the Shebab is “literally defeated” although many experts say it remains a potent threat and also warned foreign fighters with the extremists to leave Somalia.
“We have no relationship, and we do not intend to have one, with the foreign fighters in Somalia,” Mohamud said. “The only option for them is to leave the country.”

Tedros Adhanom's assignment as FM and Ali Abdu's return to Asmara

*Ali Abdu is back to Asmara after a short trip to Europe to write an exam for his distance education in political science. Ali Abdu has been pursuing a masters degree in political science and journalism via distance education for the past few years.

*The appointment of Tedros Adhanom will be a good move in improving Ethio-Eritrean relations. Tedros- born to a Tigrayan parents was born and raised in Asmara and did most of his schooling in Asmara,Eritrea. Tedros is a soft spoken and highly intelligent person. He is well respected by many Eritrean officials and his assignment as Ethiopia’s foreign minister will tremendously help the two countries to solve their crippling border problem. PMHD was given a list of DPMs and new FM apointee after intense discussion among TPLF big wigs in Mekele recently. Bereket simon played a major role in denying Berhane gebrekristose the foriegn minstry job and favoring Tedros Adhanom.

Tedros has also been favored by US administration and many donor nations due to his extraordinary talent in cultivating relationships and also respected for his skill in envisioning and implementing complex projects in the health area and his works have earned him accolade from renowned health policy makers and academia circles.

Thursday 29 November 2012

Hailemariam Desalegn commits his first major blunder since he took office 3 months ago

Ethiopia’s new prime minister, Hailemariam Desalegn, has made a cabinet reshuffle today and appointed Debretsion Gebremichael, the notorious spy and member of Meles Zenawi’s death squad, as a deputy prime minister. Another TPLF politburo member, Teodros Adhanom, is appointed as Minister of Foreign Affairs.
This is a major blunder on Hailemariam’s part since Debretsion is not only a criminal who was responsible for carrying out assassinations for Meles Zenawi, he is a threat to Hailemariam’s own authority. 

On top of being a serial killer, Debretsion’s crime include keeping 99.5 percent of Ethiopians in the information dark age by limiting their access to information technology as Minister of Communication. Because of the policies implemented by him, Ethiopia’s information technology sector is one of the least developed in the world. 

The promotion of Debretsion to the deputy premiership is further proof that Ethiopia is sliding deeper into tyranny even after khat-junkie dictator Meles Zenawi is gone.

However, Hailemariam may not have a choice in the matter in the first place. It is likely that he was forced by TPLF to make such cabinet appointments. 
 EthiopianReview.com

Ethiopia: Cabinet reshuffle, Hailemariam promoted ministers



Hailemariam promoted two ministers to double as deputy prime ministersADDIS ABABA, Ethiopia — Ethiopia’s leader has fired a government minister whose wife faces terrorism charges.
Prime Minister Hailemariam Desalegn on Thursday fired the country’s civil minister, Junedin Sado, whose wife is one of 29 people facing terrorism charges related to protests by Muslims who accuse of the government of meddling in their religious affairs.



Sado published a letter in the country’s independent newspapers in which he defended his wife and criticized the federal prosecutor’s charges.Also in Thursday’s Cabinet reshuffle, Hailemariam promoted two ministers to double as deputy prime ministers, giving the country three deputy prime ministers for the first time, a sign the ruling party is favoring collective leadership after the August death of its longtime leader Meles Zenawi.
Tedros Adhanom was appointed as the country’s new foreign affairs minister, Ato Kebede Chane and Dr, Kesete Birhane Admasu also respectively promoted to Trade and health minister.

ሰበር ዜና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት፣ ኢትዮጵያ ሶስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች



Dawit Wasihun


1.      1.  አቶ ደመቀ መኮንን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የትምህርት ሚኒስቴር 
          2.    አቶ ሙክታር ከድር የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር
    3.  ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የመገናኛ፣ ኢንፎ ርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር



   የሚኒስቴርነት ማእረግ ያገኙ 

      1.     ክተር ቴዎድሮስ አድህኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 
      2.     ቶ ከበደ ጫኔ  ከንግድ ተጠባባቂ ሚኒስቴር ወደ ዋና ሚኒስቴር 
      3.     ክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ደኤታ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

ተጨማሪመረጃ እንደደረሰን እንገልጻለን

Wednesday 28 November 2012

አጫጭር የሀገር ቤት ወሬዎች (2)

ባለፈው የዜና ዕወጃችን ይህን መሰል የሀገር ውስጥ አጫጭር ወሬዎች ዘገባ ቢያንስ በሣምንት አንድ ጊዜ እናቀርባለን ብለን ቃል ባልገባነው መሠረት ከመጀመሪያው የቀጠለውን የዛሬውን ዝግጅት ቀጥለን የምናቀርበው በታላቅ የደስታ ስሜት ነው፡፡ እነዚህ ወሬዎች በምናባዊ የአቀራረብ ፋሽን በመዋዛታቸው የአንዳንዶችን አመኔታ በቀላሉ ላያገኙ እንደሚችሉ ቢጠረጠርም ሀሰት እንዳልሆኑ ግን ለተከታታዮቻችን በዚህ አጋጣሚ ልናስታውስ እንወዳለን፡፡ የዜና ማዕከሉ ውሸትን በመዘገብ የሚያገኘው ቅንጣት ትርፍ አለመኖሩን በሚገባ ስለሚገነዘብ ጥቂቶቹን የሥነ ጽሑፍ አላባውያንና ነገር ማስዋቢያ ግብኣቶችን(literary flavors) ከመጠቀም ውጪ ያልተሰማና ያልተደረገ ወይም ከነአካቴው ‹ይህን ዓይነቱ ነገር ሊደረግ አይችልም!› ተብሎ የሚገመትን ክስተት በዜና ፋይል ውስጥ እንደማያካትት በትህትና ያስታውቃል፡፡ ሃሳብን በተፈለገው መንገድ ማቅረብ ይቻላል፤ ማንበብና ማስነበብ ደግሞ የአስነባቢዎችና የአንባቢዎች ድርሻ ነው፡፡ መንገደኞች ይለያያሉ - ተፈጥሯዊ ነው፡፡ የመንገዱ መለያየት ግን የግድ ያህል አይደለም፡፡ መቃወም ጥሩ ነው፤ መቃወምን የባሕርይ ያህል መላበስ ግን ተፈጥሯዊ አይደለም፡፡

የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሠራተኞች በሥራቸው መሰላቸታቸው ተገለጠ

በአንዳንድ ነገር ጎንጓኞች ‹የስዬ ኮሚሽን› በመባል የሚታወቀው የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አንዳንድ ሠራተኞች በመሥሪያ ቤታቸው የአሠራር ወጥነት መጥፋት የተነሣ ክፉኛ እየተበሳጩና እየተናደዱ መሥሪያ ቤታቸውንም ጥለው በመውጣት ወደሌላ ኅሊናን የማይፈታተን ሥራ ለመግባት እያሰቡ እንደሆነ ከሥፍራው የደረሰን ጥቆማ ይፋ አድርጓል፡፡ ዝርዝሩ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
“እኔ ከተቀጠርኩ ይሄውና አሥር ዓመት አለፈኝ፤ ነገር ግን የሠራሁት ሀገርንና ሕዝብን ሊጠቅም የሚችል ተጨባጭ ነገር የለም፡፡ በሙስና የተጠረጠረን ሰው ልንመረምር እንላካለን፤ በአዲስ አበባም ከአዲስ አበባም ውጪ፡፡ ነገር ግን ምርመራው ተጣርቶ ተጠቋሚው ግለሰብ አንዳች እንከን ሲገኝበት ባላሰብነው ወቅት ከበላይ አካል በሥልክ ለአለቃችን ይነገርና ‹ያን የእገሌን(የነእገሌን) ጉዳይ ተውት፤ ፋይሉ ይዘጋ› እንባልና ልፋታችን ሁሉ ዜሮ ይሆናል፤ ፋይሉም ተዘግቶ ሰውዬው በጀመረው የሙስና መስመር መንጎዱን ይቀጥላል፡፡ ሕግ የማይገዛቸው ብዙ ምርጥና ዕንቁ ዜጎች አሉ፤ ሀገሪቷን እንዳለ ቢሸጧት ዝምባቸውን እሽ የሚል የመንግሥት አካል የለም፤ ዘበናዮች ናቸው፡፡ እንዲህ እንዳፈለገው የሚሆን ሰው ግን በዘርም በዓላማም የነሱው ሰው ከሆነ ወይም በፖለቲካ የማይፈለግ ከሆነ ወይም በልዩ ልዩ ነገሮች ደጋፊያቸውና የሥርዓታቸው ታማኝ ከሆነ ነው፡፡ መሥሪያ ቤቱ የራሱ አቋምና የአሠራር ነጻነት ብሎ ነገርም የለውም፡፡ የወያኔው ቱባ ባለሥልጣናት የሚፈልጉትን ሰው ሀብት ለመቀማትና ሙልጭ ድሃ ለማድረግ ወይም ዘብጥያ ለማውረድ የሚጠቀሙበት እንደግል አሽከራቸው በሥልክ ወይ በቁራጭ ወረቀት ‹የእከሌን ነገር ባፋጣኝ አሳዩን› ሲባል ብቻ የነሱን የበቀል ጥማት ለማስታገስ የቆመ መሥሪያ ቤት ነው፤ የሚያሳዝነው የሕዝብ ከፍተኛ ሀብትና ሁለንተናዊ ፈሰስ ለዚህ ምንም ዕርባና ለሌለው መሥሪያ ቤት እየተመደበ በከንቱ መባከኑ ነው፡፡ ስሜ በዚህ መሥሪያ ቤት የሠራተኞች ዝርዝር ውስጥ ተካትቶ መገኘቱ በውነቱ በጣም ያሳፍረኛል፤ያንገበግበኛልም፡፡ 

ማስገንዘቢያ ለጦማሬ አንባቢዎች!!!



Dawit Wasihun
 
እኔም እንደ አቅሚቲ የምጻጽፍባት እዲሁም የወዳጆቼን ጽሁፍ የማራባባት ጦማሬ አንዳንዴ ስትሰራ ብዙውን ጊዜ ደግሞ ስትታፈንና ስትታገት አልፎ አልፎ ደግሞ ከምድር ተነስታ ስትበጠበጥ  እዚህ እደንደደረሰች የአገር ቤት ወዳጆቼ መልእክት ይልኩለኛል ትላንትና ዛሬ የደረሰኝ መረጃ ደግሞ የሚያስገርም ሆኗል እሱም በጦማሬ ስም የማላምንባቸው እና ባለጊዜዎችን የሚያሞጋግስ እና  የነጻነት ሃይላትን የሚያንቋሽሹ መልእክቶች እንደተላለፉ መረጃዎች ደርሰውኛል በመሆኑም ለወዳጆቼ እንዲህ አይነት መልእክት በጦማሬ ላይ እኔ እንዳላስተላለፍኩ ስገልጽ ነገርግን አሁንም ለማስታወስ የእኔ ጦማር ትክክለኛ ስም http://ethiochange.blogspot.no ሲሆን ማንኛውም የተዛባ መረጃ በዚህ ጦማር ስም እንዳልተለቀቀ ሳስገነዝብ ለቀጣይ በዚህ ጦማር ስም የተዛባ መረጃ ካገኛችሁ ሊንኩን ትልኩልኝ ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ ነገር ግን እኔ ባለኝ መረጃ እስከ አሁን ድረስ ይህንን ጦማር በአገር ቤት ማየት እንደሚያስቸግር ብዙ ወዳጆቼ አረጋግጠውልኛል

አፈናው ከበረታ ገና በ“ፓፒረስ”ላይ እንጽፋለን!



ብሩክ ከበደ

ኢህአዴግ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ የምዕራባውያኖቹን ቀልብ ለመሳብ የሶሻሊዝም ካባውን በብርሃን ፍጥነት አውልቆ የመናገርና የመፃፍ መብትን ሲፈቅድአስቦበትና ቆርጦ እንዳልነበር በዛወቅትም ሆነ አሁን ፕሬሱ ላይ የሚያደርሰውና እያደረሰ ያለው ችግር በቂ ምስክር ነው፡፡ ለስልጣናቸው መደላደልና ለርዳታ ፍጆታ ሲሉ ፈቅደናልማለታቸው ያፀደቁትንም ሆነ የሕሊናን(equity) ሕግ እንዲደፈጥጡ አስችሏቸዋል፡፡
ሕዝብ የማወቅና የማሳወቅ መብቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲገፈፍ በየወቅቱ የተለያዩ ውሃ አይቋጥሬምክንያቶች እየተፈጠሩ አፋኝ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ በዚህ ተቃርኖአዊ አያያዝም በርካታ ጋዜጠኞች ታስረዋል፣ ተደብድበዋል፣ ተሰደዋል፣ ራሳቸውን አጥፍተዋል፡፡ ምንም ነገር ባልተሟላለትና በማይሟላለት ነፃ ፕሬስ ዙሪያም ለተሰባሰቡ ጋዜጠኞች ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ማህበር ከአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀዳሚ የሆነውን
ሽልማት ለኢነጋማ (አቶ ክፍሌ ሙላት ይመሩት ለነበረው ማህበር) መስጠቱ በዚያ አስቸጋሪ ሁኔታ ሳይበገሩ ይሰሩ ለነበሩት የነፃው ፕሬስ አባላት እውቅና የሰጠ ነበር፡፡

ሕዝብ እንዲመሩት ይሁንታ ያልሰጣቸው አምባገነን ገዢዎች ከሕዝባቸው የሚነሳውን ጥያቄና ቅሬታ በፍፁም ማድመጥም ሆነ ማንበብ ስለማይፈልጉ፣ እነሱ ብቻ የሚናገሩትና የሚያስቡት በጭብጨባ ፀድቆ በመሳሪያ ኃይል ተግባራዊ እንዲሆን ለማድረግ ካላቸው ፍላጐት ስላላቸው፣ ለዚህ እኩይ አላማቸው የማይተባበረውን ነፃ ፕሬስ የጦር ያህል ይፈሩታል፡፡ በተለይ በአምባገነኖች ዙሪያ የተኮለኮሉ ሆድ እንጂ ሚዛናዊ ህሊና ያልፈጠረባቸው ግለሰቦችና ቡድኖች በግል ያካበቱት በዘረፋ የተገኘ ሀብት እንዳይነካባቸው ስለሚፈልጉ ዋንኛ የፕሬስ ጠላት ሆነው በፊት መስመር ይሰለፋሉ፡፡ ሟቹ ጠቅላይ / የመንግስት ሌቦችያሏቸው አይነቶች ለዚህ በቂ ማስረጃ ናቸው፡፡ እኚህ ሟች ጠቅላይ / አፋኝ ህጐችንና ደንቦችን የማውጣት ሥራ አይመለከታቸውም እንዳንል ሀገሪቷን 21 አመታት ብቻቸውን እንደመሯት ሰዎቻቸው በሚገባ ነግረውናል አሁንም እየነገሩን ነው፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ ለድምፅ ወያኔ ሬዲዮ የተለያዩ ጽሁፎቹን የሚያቀርቡ፣ አዲስ ራዕይ መጽሄትን (ከአሁን በኋላ የምትታተም አይመስለኝም) የሚያዘጋጁ፣ በደርግ ጊዜም አዲስ አበባ ድረስ የፃፉትን መጽሐፍ በድብቅ ልከው ያሳተሙ፣ የኢህአዴግን ፖሊሲና ርዕይ (ራዕይ አይደለም ርዕይ ነው፡ የሁለቱ ትርጉም የማይገናኝ ነው) የሪፖርተሩን አማረ አረጋዊን ጨምሮ ለሌሎቹም በረሀ ላይ የጋዜጠኛነት ኮርስ ሰተዋል የተባለላቸው መለስ ዜናዊ የጽሁፍ ነፃነትን የሚገድብ አዋጅና መመሪያ ለምን ያወጡ እንደነበር በርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡

ሙያው ስለሚያስፈልገው ጥበቃ በቂ ግንዛቤም እየነበራቸው ሆነብለው ፀረ ፕሬስ አቋም ማራመዳቸው የስርአታቸው ገበና በነፃው ፕሬስ አባላት ለህዝብ እንዳይጋለጥ በመስጋታቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሰውየው ከሳቸው ውጪ ማንም ልቆ እንዲወጣ ፍላጐት እንዳይወጣ ከነበራቸው ተፅእኖ አድራሽነት የመነጨ ሊሆንም እንደሚችል ለመገመት ይቻላል፡፡ ነፃው ፕሬስ የሀገራችንን ህዝብ የማወቅና የማሳወቅ መብቱና ኃላፊነቱ በየጊዜው ከሚወጡ አዳዲስ የማጥበቢያ ብሎም የማጥፊያ አዋጅና ደንቦች ውጪ ከምርጫ97 በኋላ ለሁለት ዓመታት ያህል ተከርችሞ ቆይቶ እንደገና ብልጭ ቢልም አፈናው ግን አሁንም የሚያሰራ አልሆነም፡፡ የኢህአዴግ መንግስት ስውር የአፈና አሰራር ምናልባት አቶ በረከት ከጫካ ጀምረን ምስጢር ጠባቂ ነንያሉት ውጤት ሊሆን ይችላልና አንድ ቀን ይፋ እስከሚሆን መጠበቅ ነው፡፡ አሁን ደግሞ .. 1930 . አጋማሽ ለሀገራቸው እውቀት መዳበር ሲሉ የተከሉትና አሁን በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኘው ብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት ለፕሬስ አፈና ተጨማሪ ኃይል ሆኖ ብቅ ማለቱ ሁሉንም ወገን ያስገረመ ብቻ ሣይሆን ያስደነገጠ ሆኗል፡፡