Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Monday 15 October 2012

አቶ ብርሀነ ገ/ክርስቶስ ተጠባባቂ ጠ/ሚር ሆነዋል

ጥቅምት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የውጭ  ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዕምባሳደር ብርሀነ ገብረክርስቶስ ተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ተደርገው እንደተሾሙ ታወቀ። የሹመት ደብዳቤው ተፈርሞ የወጣው ከጠቅላይ ሚ/ሩ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙክታር ከድር ቢሮ እንደሆነ ታውቋል።
በአቶ ሀይለማሪያም ሹመትና በሌሎች ሁኔታዎች ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ በኢህአዴግ ነባር ፓርቲዎች በተለይም፤ በኦህዴድ ውስጥ ያለው ልዩነት እልባት አለማግኘቱ አዲስ ካቢኔ እንዳይቆቆም እንቅፋት መሆኑም ተመልክቶል::
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ስፍራ ለኦሆዴድ አባል እንደሚሰጥ በአንዳንድ ወገኖች ቢገመትም፤ ሌሎች ወገኖች ደግሞ ስፍራውን ሕወሀት እንደሚይዘው ሲገልጡ ቆይተዋል::
የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህውሀት) ማእከላዊ ኮሚቴ አባል አምባሳደረ ብርሀነ ገብረክርስቶስ ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው መሰየማቸው በአዲሱ የካቢኔ ድልድል ስፍራውን በሙሉ ስልጣን እንደሚይዙት አመላካች ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ቢናገሩም፤ አቶ ተቀዳ አለሙም ለውች ጉዳይ ሚንስትርነት እንደታጩ እንዳንድ ምንጮች ተናግረዋል::

No comments:

Post a Comment