Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 13 April 2012

አርሶአደሮች ለአባይ ግድብ መዋጮ እንዲያዋጡ በካድሬዎች እየተዋከቡ መሆኑን ገለጡ

ሚያዚያ ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የባህርዳር ዘጋቢያችን እንደገለጠው በማዳበሪያ እና በምርጥ ዘር እዳ እየተዋከበ የሚገኘው አርሶ አደሩ አሁን ደግሞ ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ቦንድ እንዲገዛ በመታዘዙ ምሬቱን ገልጧል። አንድ አርሶ አደር እናደሉት 50 ኪሎ ማዳበሪያ 900 ብር፣ አንድ ኪሎ ምርጥ ዘር ደግሞ እስከ 250 ብር በመሸት ላይ ሲሆን፣ አርሶ አደሩ ይህንን እዳ ከፍሎ ሳይጨርስ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ቦንድ እንዲገዛ እዳ ተጥሎበታል ብለዋል።
በክልሉ ውስጥ የሚታየው ችጋር እንኳን ለተጨማሪ ወጪ ኑሮአችንም ለማሸነፍ አላስቻለንም ያሉት አርሶ አደሩ፣ መንግስት ካልራራልን በስተቀር አሁን በሚታየው ችጋር ብዙ ህዝብ ሊጎዳ ይችላል ሲል ስጋታቸውን ገልጠዋል። ከማዳበሪያ ዋጋ መጨመር ባሻገር የፍጆታ እቃዎች መጨመር የገበሬውን ኑሮ አስቻጋሪ እንዳደረገው፣ ገበሬውም በየጊዜው የሚንረውን ኑሮ ለመቆጣጠር ሲል በእህል ላይ ዋጋ ለመጨመር መገደዱን ፣ ይህን በተቃራኒው የከተማውን ኑሮ አስከፊ እንዳደረገው ገልጠዋል።
አቶ መለስ በቅርቡ አርሶ አደሩ የቦንድ ግዢ እንዲፈጽም ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment