Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 3 November 2012

ህወሃት ኢህአዴግ የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !

ህወሃት ኢህአዴግ የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !
ሜጀር ጄኔራል ሞላ ከስልጣን መውረድ ህወሃት ውስጥ ከተፈጠረው መከፋፈል ጋር የተያያዘ ነው :: ሜጀር ጄኔራል ሞላ የአየር ሃይሉ አዛዥነትን ስልጣን ጨብጠው ከነበሩት አራት የህወሃት አባላት ማለትም ከጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖት( ጆቤ) ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘውዴ) እና ጄኔራል አለምሸት ደግፌ አንዱ ነበረ ::
ባሁኑ ጊዜ የቀድሞው አየር ሃይል አዛዥና የህወሃት አባል የሆነው እንዲሁም በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር በሌለበትና ፓርላማ ባልመከረበት ሁኔታ የወታደራዊ ማዕረግ እድገት ከተደረገላቸው የመከላከያ አባላት አንዱ የሆኑት ሜጄር ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘወዴ) አየር ሃይሉን ባዛዥነት እየመሩ እንደሆነ ታውቋል::
በዚህ አመት ውስጥ ብዙ ባለስልታናቶች ከስልጣናቸው እንደሚነሱ የሚጠቁመው የውስጥ ምንጫችን ሌሎችም በቁልፍ ቦታ ላይ ያሉ ባለስልጣናቶች መነሳታቸው አይቀርም ሲሉ ይናገራሎ ሆኖም ግን ማንነታቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል በአጠቃላይ ህወሃት የሚያደርገው የስልጣን ሽግሽግ አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ከላይ የሚያስቀምጣቸው ከተለያዩ የህወሃት አጋር ድርጅቶች የተመረጡ ባለስልታናትን ብቻ ሲሆን ከዚያ ውጭ ከስር በመሆን የማስተዳደሩን ስራ ሲተገብሩ ይኖራሉ በማለት ምንጫችን ይገልጻሉ ። አጠቃላይ የወያኔ አስተዳደር ከቀድሞው ሊቀመንበሩ አቶ መለስ ዜናዊ ስርአተ ሞት በኋላ የመንሸራተት እና ከፍ ዝቅ የማለት እይታ ይታይበታል። አቶ ጁነዲን ሳዶን ከውጭ አገር ህክምና ካገደ በኋላም ሌሎችን ባለስልጣናትን ጨምሮ የቁም እስረኛ አድርጎ ያስቀመጣቸው ሰዎች እንዳሉ የማለዳ ታይምስ የውስጥ መረጃ ያመለክታል ።በዚህ አመት ውስጥ በወያኔ ኢሃዴግ ከተሰሩት ስህተቶች ውስጥ ያለ ጠቅላይ ሚንስትሩ የመኮንኞች ሹመት ማጽደቁ ፓርላማውን እና እንዲሁም አስተዳደሩንም ያስገመተም ከመሆኑም በላይ የራሱን አካላቶች በከፍተኛ ቦታ ላይ ለማስቀመጥ ያደረገውን ዝግጅቱን ለማሳየት በቂ መረጃ ነው ሲሉ መረጃዎቻችን አብራርተዋል

No comments:

Post a Comment