Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 29 June 2012

የኦሎምፒክ ችቦ ቅብብል አባል እንዲሆን የተመረጠው ታዳጊ ወጣት ጠፋ

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ቢቢሲ ዛሬ ባወጠው ዘገባ እንደገለጠው ኢትዮጵያዊው የ15 ዓመት ታዳጊ ወጣት ፣ ናትናኤል የማነ፣ የኦሎምፒክ ችቦ ከሚያዞሩ ወጣቶች መካከል በመሆን ወደ እንግሊዟ ኖቲንግሀም ከተማ ባለፈው ሀሙስ አቅንቷል። ይሁን እንጅ ታዳጊው ወጣት ዛሬ ረፋዱ ላይ ከሆቴሉ እንደወጣ አልተመለሰም።
የታዳጊው እንግሊዝኛ ችሎታ ውስን መሆንና መንገዶችን የማያውቅ በመሆኑ ፣ ታዳጊው ችግር ሊፈጠርበት ይችላል በማለት ፖሊሶቹ ስጋታቸውን ገልጠዋል።
ናትናኤል የማነ የኦሎምፒክን ችቦ እንዲያዞሩ ከ20 አገራት ከተመረጡ ታዳጊዎች መካከል ከኢትዮጵያ ተመርጦ የሄደ ነው።
__________________________________________________________

Thursday 28 June 2012

Ethiopia: Conviction of government opponents a ‘dark day’ for freedom of expression

This is a dark day for justice in Ethiopia, where freedom of expression is being systematically destroyed by a government targeting any dissenting voice
Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Ethiopia: Conviction of government opponents a 'dark day' for freedom of expressionMore Ethiopian government opponents have been convicted on trumped up terrorism and treason charges in what Amnesty International called “a dark day” for freedom of expression.
Iconic dissident journalist Eskinder Nega and leading members of the political opposition, Andualem Arage and Nathnael Mekonnen, along with five other men, were found guilty on charges of “terrorist acts, “encouragement of terrorism”, “high treason” and several other charges.
A further 16 men were found guilty in absentia, including several journalists and one human rights activist. The verdict follows the conviction of five dissidents on similar charges in January.
“This is a dark day for justice in Ethiopia, where freedom of expression is being systematically destroyed by a government targeting any dissenting voice,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
“We believe that Eskinder, Andualem and Nathnael are prisoners of conscience – convicted because of their legitimate and peaceful activities, and particularly for advocating peaceful protest against the government. They should be immediately and unconditionally released.”
The trial was marred by serious irregularities, including allegations of torture made by at least one defendant, which were not investigated.
Statements by the Prime Minister and programmes aired on state TV pronouncing the guilt of the defendants violated their right to be presumed innocent and exerted significant political pressure on the court.
Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation, used to convict the defendants on several of the charges, enables the prosecution of legitimate and peaceful activities as ‘terrorist’ acts.
“We believe the defendants did not receive a fair trial,” said Beston. “The verdict seemed to be a foregone conclusion.”
“Evidence presented against Eskinder, Andualem and Nathnael did not demonstrate criminal wrongdoing, instead much of the evidence showed their peaceful and legitimate activities.”
Several pieces of evidence against Eskinder, a journalist who won this year’s prestigious PEN/Barbara Goldsmith Freedom to Write Award, centred on his discussion of whether last year’s Middle East and North Africa uprisings could spread to Ethiopia.

Tuesday 26 June 2012

የሕወሃት መንግስት በእርዳታ ያገኘውን ምግብ ኤክስፖርት ማድረግ ሊጀምር ነው

ሰኔ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የሕወሃት አስተዳደር ከበጎ አድራጊ ድርጅቶችና መንግስታት በረሃብ ለተጎዳው ወገናችን የሚላከውን የእርዳታ እሕል፤ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት በተሰኘው ተቋም በኩል በአለም ዓቀፍ ገበያ አውጥቶ ለመሸጥ እንዳቀደ ሬውተር የተሰኘው የዜና ወኪል ዘገበ።
በቅርቡ ሃላፊነቴን ለሌላ ሰው አስረክባለሁ ያሉት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድሕን፤ በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ላነጋገራቸው ለሬውተር የዜና ወኪል እንደገለፁት፤ መንግስት በእርዳታ ያገኘውን እህል፣ በተለይም በቆሎና ስንዴ በድርጅቱ አማካኝነት ለሽያጭ በማቅረብ ከዚሁ በሚገኘው ገንዘብ የውሃ ጉድጓዶችን ለመቆፈሪያና፣ ለኤሌክትሪክ ሃይል ማስፋፊያ ሊያውለው እንዳቀደ ጠቁመዋል። ሆኖም  ዶ/ር እሌኒ ይህ እቅድ እንዴት እንደሚተገበር በዝርዝር ማስረዳት እንዳልቻሉ ሬውተርስ በዚሁ የዜና ዘገባው ሳይጠቅስ አላለፈም።
ምንም እንኳን መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ 1995 ከአስር ዓመት በኋላ ስለምትኖረው ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሶስት ጊዜ መመገብ የሚችልበትን አቅም እንገነባለን ሲሉ በተስፋ አስክረውን የነበር ቢሆንም፣ ያልውን ነባራዊ እውነታ ዛሬ ከ16 ዓመታት በኋላ ስናስተውል፤ አብዛኛው የኢትዪጵያ ሕዝብ የሚቀምሰው እንኳን በማጣት እየገፋው ያለው አስከፊ ሕይወት  የህዝብ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል
ሂዮመን ራይትስ ወች የተሰኘው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት፤ ባሳለፍነው የፈረንጆቹ ዓመት ባወጣው መግለጫ እንደጠቆመው፣ 20 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከውጭ አገር የሚመጣ እርዳታ ጠብቆ የሚኖር ሲሆን፣ ከ7 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በመጠባበቂያ ምግብእርዳታ፣  ከ7-10 ሚሊዮን የሚሆነው ደግሞ በአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ሕይወቱን እንደሚታደግ አስታውቆ ነበር።
በያዝነው ዓመትም 12 ሚልዪን የሚጠጋ ኢትዮጵያዊ  ከወዲሁ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ካላገኘ በአገራችን አስከፊ እልቂት ሊከሰት እንደሚችል፣ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ለዓለም ማሕበረሰብ ለማስገንዘብ እየጮሁ ባለበት ወቅት፣ የወያኔ መንግስት፤ በጎ አድራጊዎች የሚመፀውቱትን የምግብ እርዳታ ሳይቀር ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የያዘው ዕቅድ ብዙዎችን ያስገረመ ብቻ ሳይሆን ያስደነገጠ ሆኖ ተገኝቷል።
የቀድሞው የህወሃት የፋይናንስ ክፍል ሃላፊ አቶ ገ/መድህን አርአያን ጨምሮ ሌሎች ውስጥ አዋቂዎች ካሁን ቀደም እንዳጋለጡት፤ የሕወሃት ሹሞች ለስልጣን ከመብቃታቸው በፊት ጀምሮ በረሃብ እየረገፈ ለነበረው የትግራይ ሕዝብ ከበጎ አድራጊ ድርጅቶች የተመፀወተውን የምግብ እርዳታ፣ በድብቅ ዞር አድርገው በመቸብቸብ  ይከሰሳሉ። አሁንም በዚሁ መልኩ ለችግረኛ ወገናችን የመጣውን እርዳታ በይፋ ለመሸጥ ማቀዳቸውን ተከትሎ፤ ለጋሽ ድርጅቶችና መንግስታት ያደርጉ የነበረውን የምግብ እርዳታ ሊቀንሱ አንዳንዶቹም ጨርሶ ሊተውት ይችላሉ የሚለውን ስጋት ብዙዎች ይጋሩታል።
በቀድሞው  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ የቦርድ ሊቀመንበርነት የሚተዳደረው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት፣ ቤተመንግስቱ ድረስ የሚዘረጋ ረጅም እጅ ያለው በሙስና የተጨማለቀ ተቋም እንደሆነ በተደጋጋሚ ይነገርለታል።
ከወራት በፊት የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ሊሰጠው አቅዶት ከነበረው 5 ሚልዮን የሚጠጋ ገንዘብ ውስጥ፤ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ 4 ሚሊዮን 8 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላሩን የድርጅቱን አቅም ለመገንባት በሚል ሰበብ ዶ/ር እሌኒ ገብረመድህን ለሚመሩት ተቋም እንዲሰጥ ጠይቆ ነበር። ሆኖም ዶ/ር እሌኒ “ሚልንየም አይቲ” ከተሰኘው የስሪላንካ ድርጅት ጋር በመመሳጠር አሸንፌአለሁ ሲሉ ያቀረቡት የጨረታ ኮንትራት፤ የሃሰት ድራማ መሆኑን የአለም ባንክ አስቀድሞ ስለደረሰበት፣ እርዳታውን ሙሉ ለሙሉ መሰረዙን  ኢሳት በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።
በያዝነው የፈረንጆቹ አመት መጀመሪያ ላይም “የአገራችን ቡና ላኪዎች ወደ ውጭ አገር የምንልከው ቡና አጥተናል፤ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ግብይት የተፈጸመበት ቡናም ከመሃል አገር ወደ ኬንያ፣ ሱዳን፣ እንዲሁም ኤርትራ በሕገወጥ መንገድ እየተጫነ ነው።” በማለት አቤቱታቸውን አሰምተው ነበር። በዚህ ድርጅት በኩል ለውጪ ገቢያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ከአስር ሺህ ቶን በላይ የተጣራ ቡናም በድንገት ከመጋዘን ጠፋ መባሉ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ሲሆን ይህን ተከትሎም አቶ መለስ ዜናዊ “የአሁኑን እንተወው ከኣሁን በኋላ ግን በእንደዚህ ኣይነት ተግባር ላይ የሚሳተፍ  እጁ ይቆረጣል” በማለት ጥፋተኞቹ እንዳይጠየቁ ጉዳዩን አለባብሰውት ማለፋቸው የሚዘነጋ አይደለም በማለት ቅዱስ ሀብት በላቸው ከአውስትራሊያ ዘግቧል።

አቶ በረከት ስምኦን መንግስታቸው ስካይፒንና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ለመዘጋት መወሰኑን አመኑ

ሰኔ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል መንግስት ስካይፕንና የኢንተርኔት አገልግሎትን ለመዝጋት ወስኗል በማለት የሚገልጡት የምእራባዊያን ጋዜጠኞች ናቸው በማለት መግለጫ በሰጡ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አቶ በረከት ስምኦን ኢንተርኔት ለቴሌኮም አገልግሎት የመጠቀም ተግባር አገሪቱን ከፍተኛ ገቢ እያሳጣት በመምጣቱ ስካይፒን ጨምሮ ሌሎች የኢንተርኔት የቴሌኮም አገልግሎቶችን መንግስት ለመዝጋት ወስኗል ብለዋል።
የመንግሥት የኮምኒኬሸን ሚኒስትር የሆኑት አቶ በረከት ለኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ሰሞኑን እንደተናገሩት መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የስካይፒ ዓይነት አገልግሎቶች በቴሌኮሚኒኬሸን ዓመታዊ ገቢ ላይ ከፍተኛ ጫና በማሳደራቸው ነው፡፡
አቶ በረከት በእርምጃው የተቃጣውን ትልቅ ገቢ በመመለስ ለተያዙት የባቡር ፣ የስኳርና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለመደጎም መታቀዱን ለጋዜጠኞቹ ነግረዋቸዋል፡፡
በኢንፎርሜሸን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ተረቅቆ ለፓርላማ በቅርቡ የቀረበው የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን የሚመለከተው ረቂቅ አዋጅ በህገወጥ የቴሌኮም አገልግሎት አገሪቱ እስከ 83 በመቶ የሚሆን ገቢ እንደምታጣ በመጥቀስ በዚህ ወንጀል ውስጥ ተሰማርቶ መገኘት ከ10-20 ዓመታት እስራትና በዚህ ሕገወጥ አገልግሎት የተገኘ ገቢ እስከ አስር ዕጥፍ የሚደርስ መቀጮ የሚያስቀጣ መሆኑን ተጠቃሚዎችን ደግሞ ከ3 ወራት እስከ 2 ዓመታት እስራትና እስከ 20ሺ ብር መቀጫ የሚጥል ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት ዓርብ ዕለት በጽ/ቤታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት የአቶ በረከት ምክትል የሆኑት አቶ ሸመልስ ከማል ስካይፒ አለመከልከሉን ፣በየድረገጹ የሚነገረው ሁሉ በሬ ወለደ ነው ሲሉ ማሰተባበላቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ሽመልስ ከዚህ ቀደም የአሜሪካንን ደምጽ ለማፈን የመንግስት ዲሞክራሲያዊ ባህሪ አይፈቅድለትም ባሉ በቀናት ውስጥ አቶ መለስ ዜናዊ ቪኦኤን ማፈናቸውን ተናግረው ነበር። አሁን ደግሞ የአቶ ሽመልስ አለቃ አቶ በረከት ስካይፕንና በኢንትርኔት ስልክ የመደወልን አካሄድ እናስቆማለን ማለታቸው የተለያዩ አስተያየቶች እንዲቀርቡ አድርጓል። አንዳንድ ወገኖች ወይ የመንግስት ባለስልጣናት እርስ በርስ አይነጋገሩም ወይም  አቶ ሽመልስ ዬይስሙላ ቃል አቀባይ ናቸው ወይም እርሳቸውን ለማዋረድ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው በማለት አስተያየት ይሰጣሉ።

Monday 25 June 2012

እየመረረ፣ እያመረረ፣ እያስመረረ…

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
ከኢትዮጵያ ሕዝብ ስንት በመቶው በራሱ ጉዳይ፣ በእህል በውሀው ጉዳይ ከማንሾካሾክ አልፎ አፍ አውጥቶ ይናገራል?፤ ለማንስ ይናገራል?፤ ማንስ ይሰማል?፤ በቴሌቪዥኑ፣ በራዲዮውኑ በጋዜጣዎች የሚነጋገረው በአጠቃላይ አምስት ሚልዮን ይሞላል? ሌላው ሰማንያ አምስቱ ሚልዮን ተመችቶት ነው? የዕለት እንጀራውን ማሳደድ ፋታ አልሰጥ ብሎት ነው? መነጋገሩን ንቆት ነው? ብሶቱን ለመናገር ዕድሉን ባለማግኘቱ ነው? ፈርቶ፣ ጎመን በጤና እያለ ነው? ሌላም ምክንያት ሳይኖር አይቀርም፤ ሁሉም ከተናገሩ ሆድ ባዶ ይቀራል! ሆድ ባዶ ከሚቀር ቁርጠት ይሻላል፤ ቆሽቱ ድብን ቢል ይሻላል፤ አንጀቱ እርር ቢል ይሻላል፤ እንደወጣ ከሚቀር! አዲስ ነገርም መጥቶአል፤ አንዳንድ ጓደኞቻችን ዓለምን ስተዋል፤ ምን ሲደረግ እንደነበረም ሆነ ምን እየተደረገ እንዳለ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም፤ እነዚህ ሰዎች እንኳ ስለምግብ ሊያስቡና መብላትም እንዳለባቸው ረስተዋል፤ ስለዚህ ምንም ችግር የለባቸውም።
እንግዲህ አፍ አውጥቶ ራበኝ፤ ጠማኝ፤ በረደኝ፤ አመመኝ፤ ታፈንሁ፤ ተበደልሁ፤ ተጠቃሁ፤ የሚለው ከአምስት ሚልዮን ግምታችን ውስጥ አራት ሚልዮን ይሆናል? ይህ ወደ እውነቱ የሚጠጋ ከሆነ የተመቸው አንድ ሚልዮን ነው ማለት ነው፤ እንግዲህ ንግግሩ ሁሉ በጠገቡና በተመቻቸው በአንድ ሚልዮንና በተጨቆኑትና በደሃዎቹ አራት ሚልዮን መሀከል ነው ማለት ነው፤ የቀረው ሰማንያ አምስት ሚልዮን የሚሆነው (ከሠላሳ በላይ የሚሆኑ ዩኒቨርስቲዎችንም ጨምሮ) በዝምታ ተውጦአል! (አንድ ሚልዮን፣ አራት ሚልዮንና ሰማንያ አምስት ሚልዮን ግምቶች እንጂ የተረጋገጡ ቁጥሮች አይደሉም፤ ካልተስማማችሁባቸው በራሳችሁ ግምት መለወጥ ትችላላችሁ)።
ደሀውና ጭቁኑ ዕለት በዕለት የብሶቱን ቁስል የሚጎረጉሩት ነገር ያያል፤ ይሰማል፤ የሚሰማው ነገር ሁሉ እውነት መሆኑ ወይም አለመሆኑ ለሱ ጉዳይ አይደለም፤ ለሱ ዋናው ነገር ያሳደረበት ስሜትና የሚፈጠርበት ጥላቻ ነው፣ የምሬቱ ሕመም መባባስ ነው፤ እውነቱን ለማጣራት ጊዜ የለውም፤ በዜና ማሰራጫዎቹ የሚሰማቸውና የሚያያቸው ሁሉ የተቀነባበሩና የተዋቡ ሐሰቶች መሆናቸው ከገባው ቆይቶአል፤
ሕመሙ ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ረሀቡ ሲያመው፣ ሲመርረው፣
ብርዱ ሲያመው፣ ሲመርረው፣
ጭቆናው ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ውርደቱ ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ሲመርረው፣ ሲያስመርረው
መኖር ሲያስጠላው
ሞትን ሲያስመኘው፤
በገዛ እጁ ተቃጥሎ ሲሞት፣ ተሰቅሎ ሲሞት፣ ተኝቶ ሲሞት፣ አንድ በአንድ እያለ አራት ሚልዮኑ ቢያልቅ፣ የደላው አንድ ሚልዮኑ ከዝምተኛው ሰማንያ አምስት ሚልዮን ጋር ቢቀር ምን ዓይነት ማኅበረሰብ ይፈጠራል? እንዲያውስ ማኅበረሰብ የሚባል ነገር ይኖራል?
አረቦቹም እንደኛ መረራቸው፤ አመረሩ፤ አስመረሩ፣ ለየላቸው፤ እነሱ ከአደረጉት ለእኛ ምን አስተማሩ? ለአንድ ሚልዮኑ? ለአራት ሚልዮን አረቦቹ የሄዱበትን መንገድ ጭራሽ አይመኘውም፤ አራት ሚልዮኑ ሁሌም ግራ የገባው በመሆኑ ከትግሉ ሜዳ ካልወጣ አይፎክርም፤ ከትግሉ ሜዳ የወጣ ፉከራ ደግሞ ከቲያትር ቤት ጨዋታ አያልፍም፤ ሰማንያ አምስት ሚልዮኑ የዕለት እንጀራውን ለራሱና ለቤተሰቡ ሲያስብ አምስት ሚልዮኑ ለሚሠሩት ቲያትር ለተመልካችነትም ጊዜ ያለው አይመስልም።
ሊብያውያን የጋዳፊን ጭቆና አስወግደው አሁን እየተደባደቡ ነው፤ ግብጻውያንም ለድብድብ እየተዘጋጁ ይመስላል፤ የመናውያን ደንበኛ ጦርነት ላይ ናቸው፤ በቅርቡ የየመኑ ጄኔራል ተገደለ፤… ሶርያውያን ምናልባት ማንም የማያሸንፍበት በጣም ከባድ የሆነ የጦርነት ሁኔታ ውስጥ ናቸው፤ በእነዚህ የአረብ አገሮች የተፈለገው ምን ነበረ? ምን ተገኘ? ለብዙኃኑ ሕዝብ ሥልጣንን የሚያስረክብ ሁኔታ በአንዱም አገር አልተፈጠረም፤ የዓለም ልዕለ-ኃያላኑም የብዙኃኑን ሥልጣን መረከብ አይፈልጉም፤ ወይም አንዱ ቢፈልግ ሌላው አይፈልግም፤ በሥልጣን ወንበር ላይ ለብዙ ዓመታት ተጣብቀው የነበሩት በግድ ወረዱ፤ ተደራጅተው ለሥልጣን አሰፈስፈው ሲጠብቁ የነበሩት ደግሞ አንዱን ዓይነት ጭቆና በሌላ ዓይነት ጭቆና ለመተካት ተጣደፉ፤ በ1966/67 እድሜያቸው ሃያ ዓመት ግድም የደረሰ በዚያን ጊዜ በኢትዮጵያ የሆነውን ያስተዋሉና የሚያስታውሱ ሁሉ የዚያን ጊዜ ተዋናዮች እነማን ነበሩ? አሰላለፋቸውና ትግላቸው እንዴት ነበረ? ውጤታቸውስ ምን ሆነ? ዛሬ በግብጽ ያለውን ሁኔታ ልብ ላለ፣ ልዩነቱ የኢትዮጵያ ጄኔራሎች ፈቃዱም ወኔውም ስላልነበራቸው የጦር ኃይሉ በሻለቆችና በበታች ሹማምንት መመራቱ ብቻ ይመስለኛል፤ ወይም ከላይ በአቀረብሁት ምሳሌ ለመቀጠል የ1966/67 የኢትዮጵያ የጦር ኃይል በጠቅላላ ከተመቸው አንድ ሚልዮን ጋር ሳይሆን ከአራት ሚልዮኑ ጋር ሲቆም ጄኔራሎቹ ከአንዱ ሚልዮን ጋር ቀሩ።
ስለዚህ በራሳችን ታሪክ በተከታታይ ሀሳብ በጥይት እየተጨናገፈ፣ ሰላም በጉልበት እየታመሰ፣ እውነተኛ እድገት በማታለል እየጫጨ፣ ስምምነትና ትብብር በግል ምኞትና በፍቅረ ንዋይ እየመነመነ፣ አፈና ጥላቻን እየወለደ፣ ጥላቻም አፈናን እየወለደ፣ አንዱ ሌላውን እያስመረረው፣ የመረረው እያመረረ ሠላሳ ስምንት ዓመቶች ቆጥረናል፤ ከዛሬዎቹ አንድ ሚልዮን ጋርም ሃያ አንድ ዓመቶችን ቆጥረናል፤ እየመረረንም፣ እያስመረረንም ምንም አልተማርንም? አናሳዝንም?

Sunday 24 June 2012

ፍትህን እና አልሸባብን ምን አገናኛቸው?

በተመስገን ደሳለኝ
እንደመንደርደሪያ
አዲስ ዘመን እና በተመሳሳይ መስመር የተሰለፉ ሚዲያዎች (አይጋ ፎረም፣ ዋልታ እና ዛሚ) በፍትህ ጋዜጣ ላይ ‹‹አርማጌዲዮን›› መጀመራቸው ይታወቃል። ሆኖም ለረጅም ጊዜ ምላሽ የመስጠት ፍላጐት ስላልነበረኝ ‹‹ውሾቹ ይጮኻሉ፤ ግመሉ…›› በሚል ብሂል ነበር ለማለፍ የመረጥኩት። አሁን ግን ይህ ውንጀላ አንድ ደረጃ ከፍ እያለ በመሄዱ እና አደገኛ አዝማሚያ እየያዘ በመምጣቱ፤ በአናቱም የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆኔ በአንዳንድ ባልደረቦቼ ላይ ከዚሁ ጫና የመነጨ የስነ ልቦና ተፅዕኖ እያደረሰ በመሆኑ ቢያንስ ህዝብ ይወቀው በሚል መንፈስ ነው ይህንን ፅሁፍ ለመፃፍ የተገደድኩት።
በቅድሚያ ግን አሁንም ከዚህ ቀደም ደጋግሜ እንደገለፅኩት እኔም ሆንኩ ባልደረቦቼ የምናገለግለው አንዱን ለማስደሰት ወይም ሌላውን ለማስከፋት የሚል አላማ ኖሮን አለመሆኑን አፅንኦት መስጠት እፈልጋለሁ። የእኛ አላማ አንድ እና አንድ ነው። ሀገርን ማገልገል እና ለምንወዳት ሀገራችን የዜግነት ግዴታችንን መወጣት። ስለዚህም ፍትህ ምንጊዜም የህዝብ አንደበት እና ጆሮ ሆና ትቀጥል ዘንድ አቅማችን የፈቀደውን ያህል እንሰራለን። ይህንን ግዴታችንን ስንወጣ ህገ-መንግስታዊ መብታችንን አክብረን እስከሆነ ድረስ ደግሞ ለየትኛውም ጫናም ሆነ የፈጠራ ክስ፣ አሊያም ማስፈራሪያ ወይም ማባበያ እጅ የምንሰጥበት ሁኔታ እንደማይኖር ደጋግመን በዚሁ ጋዜጣ፣ በዚሁ ገፅ ላይ ተናግረናል። ይህ አንድ እውነት ነው፡፡ ሌላው እውነት ደግሞ ይኽ ነው፡፡ ሰሞኑን የመጭውን ጊዜ የአደጋ ‹‹ቀለም›› የሚያመላክቱ ምልክቶች በፍትህና አዘጋጆቿ ዙሪያ እያንዣበቡ ነው። ስለነዚህ ምልክቶች ከመነጋገራችን በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ፍትህን በሚመለከት ስለወጡ ፅሁፎች ጥቂት እናንብብ፡፡
የመንግስት አንደበት ምን አለ?
ከተመሰረተበት ዘመን (1933ዓ.ም.) ጀምሮ የመንግስት አይንና ጆሮ ሆኖ ዛሬ ላይ የደረሰው አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚያንፀባርቃቸው አቋሞች እና ለንባብ የሚያበቃቸው መጣጥፎች ‹‹የመንግስትን አቋም›› ያመላክታሉ ወይስ አያመላክቱም? በሚል ክርክር ጉልበት ማባከኑ አስፈላጊ አይመስለኝም፤ ግልፅ ነውና። በዚህ ከተስማማን ደግሞ ከዚህ ቀደም በአዲስ ዘመን ላይ አዲስ ነገር እና አውራምባ ታይምስን በሚመለከት ይታተሙ የነበሩ ውንጀላዎች መንግስታዊ ባለቤት እንዳላቸው እንስማማለን ማለት ነው፤ ከ2002ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ፍትህን የሚመልከቱ የውንጀላ መጣጥፎች የጋዜጣው መለያ ሆነዋል። በተለይ በገፅ 3፤ አልፎ አልፎ ደግሞ በገፅ 11 ላይ ‹‹ፖለቲካ›› በሚል አምድ ስር ነው እነዚህ ውንጀላዎች የሚስተናገዱት። እዚህች ጋር አንድ አስቂኝ ነገር ልንገራችሁ። የአዲስ ዘመን ‹‹ገፅ ሶስት›› በትላልቅ ፊደል ‹‹አጀንዳ/ደብዳቤዎች›› የሚል የአምድ ስም ተሰጥቶት ሲያበቃ ‹‹ርዕሰ- አንቀጽና›› እንዲህ የሚል ማብራሪያ ተለጥፎበታል ‹‹ይህ ዓምድ በተለያዩ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዜጐች ነፃ አስተያየታቸውን የሚሰጡበት ነው››፤ በዚህች ፉገራ ፈገግ ብለን በገፁ ላይ የሚስተናገዱ ፅሁፎችን ብናየው ሙሉ በሙሉ መጀመሪያ ላይ በኢንተርኔት በሚሰራጩ ድረ ገፆች (አይጋ ፎረም እና ዋልታ) ላይ ከታተሙ በኋላ ‹‹የህዝብ አስተያየት›› በሚል የዳቦ ስም ወደአዲስ ዘመን ጋዜጣ ተላልፈው በድጋሚ እንደሚታተሙ እንረዳለን፡፡ መቼም እዚህች ጋርም ለተጨማሪ ጊዜ መሳቃችን አይቀርም ምክንያቱም በመንግስት የሚተዳደረው እና በቂ በጀት የተመደበለት ጋዜጣ ‹‹ፅሁፎችን የማትመው ከኢንተርኔት እየለቃቀምኩ ነው›› እያለን ነውና።
የሆነ ሆኖ አዲስ ዘመን እና ግብረአበሮቹ ለረጅም ጊዜ ፍትህን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ያለእረፍት እየሰሩ መሆኑን የጨረፍታ ግንዛቤ ለመስጠት ያህል የሩቆቹን ትተን የቅርቡን ማለትም በሚያዚያ እና ግንቦት ወር ብቻ የታተሙትን የውንጀላ ጽሑፎች የጥቂቶቹን ርዕሶች ብቻ ላመላክታችሁ፡-
‹‹ተነስ ያሉት እምቢ ቢል በ‹ጊዜ ለኩሉ…›› (የዚህ ፅሁፍ ፀሐፊ የጋዜጣው ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ገፅ ም/ዋና አዘጋጅ የሆነው ሰይፉ ደርቤ ነው፣ ‹‹የገደል ጫፍ ላይ ሩጫ››፣ ‹‹በአዲስ መልክ ሥራ ጀምረናል!› ሌላው የመድረክ የፕሮፓጋንዳ ‹ጭብጥ› ይሆን እንዴ?››፣ ‹‹ፍትህና አምደኞቿን በጨረፍታ›› (ስድስት ክፍል ያለው በስድስት እትም የተስተናገደ)፣ ‹‹የጨለማው ዘማሪዎች መናኸሪያና ደቀ-መዝሙሮቹ›› (በአራት ክፍል ለአራት ጊዜ የታተመ)፣ ‹‹የዋህ ነፍሰ ገዳይ››፣ ‹‹ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚመች ፕሬስ ነፃ አይደለም››፣ ‹‹አንቀጽ 29፣ የፕሬስ ቀንና ማተሚያ ድርጅት››፣ ‹‹በደም የተፃፈው ህገ-መንግስት ያደፈው በማን ነው?››፣ ግራ የተጋባው የፖሊሲ ሰነድ ‹ትንተና›…›› በሚሉ ርዕሶች በሁለት ወር ውስጥ ብቻ በፍትህና ባልደረቦቿ ላይ ያነጣጠሩ አስራ ስምንት (18) ፅሁፎች ታትመዋል።
የፅሑፎቹን ይዘት ስንመለከት ደግሞ ሁሉም ፍትህ በአሸባሪ ድርጅቶች እና በኤርትራ መንግስት በገንዘብ ይደገፋል በሚል መደምደሚያ የሚያልቁ ናቸው። ለዚህ ደግሞ እንደምክንያት የሚያቀርቡት ጋዜጣዋ ያለ በቂ ማስታወቂያ እስከአሁን በህትመት መቆየቷን ነው። ለምሳሌ ‹‹የጨለማው ዘማሪዎች መናኸሪያና ደቀ-መዝሙሮቹ›› በሚል ርዕስ በወጣው ክፍል ሁለት ፅሁፍ ላይ ‹‹ፍትህ ጋዜጣ ባለ16 ገጽ እንደመሆኑ መጠን፣ 6 ገፅ ተኩል የሚጠጋውን ማስታወቂያና 9 ተኩል የሚጠጋውን ገፅ ደግሞ ፅሑፎችን መያዝ ይገባው ነበር። ሆኖም ጋዜጣው ግን 16ቱንም ገፆች ሊባል በሚችል የጭፍን ጥላቻ አሉባልታ መጋለቢያ ጽሑፍ አድርጎ ያለምንም ማስታወቂያ ወጪዎቹን በሙሉ እየሸፈነ ህልውናው ሳይናጋ ገበያው ላይ ከዘለቀ አራት ዓመቱን ሊያስቆጥር ነው።…. የገቢያቸው ምንጭ ከወዴት ነው? የሚለው ጥያቄ በማናቸውም መስፈርቶች ምላሽ የሚያሻው ጉዳይ ነው።›› ይልና ቀጥሎ እንዲህ ሲል ይጠነቁላል ወይም ይወነጅላል ‹‹የገቢ ምንጩም ከእነዚሁ ፀረ-ሰላም ኃይሎች እንደሚሆን ለመገመት አይከብድም። ጋዜጣውም ቢሆን በእነዚህ ኃይሎች የማይደጎም መሆኑን በአሳማኝ አመክንዮ ማረጋገጥ የሚችል አይመስለኝም። በእንካ ሰላምቲያ ዙሪያ ጥምጥም እየሄደ ዓይኔን ግንባር ያድርገው ለማለት ካልፈለገ በስተቀር።››
አሁንም ቆይታችንን ከአዲስ ዘመን ጋር እንዳደረግን እንቀጥልና ‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ-ክፍል ሶስት›› በሚል ርዕስ ከታተመው ፅሁፍ ላይ ሌላ ጥንቆላ እንቀንጭብ ‹‹የፍትህና አምደኞቹን ጀርባ ለማየት ባደረኩት ጥረት የደረስኩበት ነጥብ የባዕድ እጅ ድጋፋቸው የጠላት ገንዘብ ኪሳቸውን መሙላቱን ነው›› ይላል። መቼም አዲስ ዘመን ‹‹ጋዜጣ›› እንጂ ‹‹የስለላ›› /የደህንነት/ መስሪያ ቤት እንዳልሆነ እናውቃለን። ነገር ግን ያለአንዳች ይሉኝታ ‹‹የፍትህና አምደኞቹን ጀርባ ለማየት ባደረኩት ጥረት…›› ይልና ሲሰልለን እንደቆየ ይነግረናል፡፡ አሁን ነው ‹‹እሪ በይ!›› ሀገሬ ማለት፡፡ እንግዲህ አዲስ ዘመን ስለራሱ፣ በራሱ ጋዜጣ ከሰጠን ምስክርነት ስንነሳ ከጋዜጣው ጀርባ እነማን ተሰልፈው የሀሰት ውንጀላ እየለጠፉ እንደሆነ ለመናገር ነቢይ መሆን አይጠይቅም።
‹‹የዋህ ነፍሰ ገዳይ›› የሚል ርዕስ ያለው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ፅሁፍም እንደሌሎቹ ፅሁፎች በጥንቆላ የተገኙ ውንጀላዎችን ዘርዝሮ ሲያበቃ እንዲህ ይልና ይደመድማል፡- ‹‹የተመስገን ‹ተቀጣጣይ› አጀንዳዎቹ ደግሞ የተመስገን ብቻ ሳይሆኑ የግንቦት 7፣ የኦነግና የኦብነግ እንዲሁም የዜሮ ድምር ፖለቲካው ስብስቦች ሁሉ ናቸው። ለዚህ ነው የፍትህና የአምደኞቿ ጭንቀት የሽብር ተግባራቸውን የሚመሩበትን አካሄድ ውሉ እንዳያግድባቸው የፈጠረባቸው ስጋት ነው የምለው።››
እንግዲህ እነዚህን ሁሉ መንግስታዊ ሽብሮችን ነው መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በምክትል ዋና አዘጋጁ ሰይፈ ደርቤ እና በተለያዩ ሰዎች ስም እያተመ በመወንጀል ላይ ያለው። በነገራችን ላይ ጋዜጣው ከፀሀፊዎቹ ጀርባ ማን እንዳለ አልፎ አልፎም ቢሆን ሳት እያለው ይናገራል። ለምሳሌ በስድስት የአዲስ ዘመን እትሞች ላይ በተስተናገደው ‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ›› ፅሁፍ ክፍል አምስት ላይ ድንገት ተነስቶ ‹‹እነሆ የጨረፍታዬን አምስተኛ ክፍል በግሌ ለመፃፍ ስነሳ የመንግስት ማስፈራሪያ ስላለመሆኑ አንባቢያን እንደሚረዱልኝ በማመን ነው›› ሲል የውስጡን ይነግረናል። እዚህ ጋር የሚተኮርበት ነጥብ የዚህ ፅሁፍ ባለቤት ወይም ባለቤቶች እስከ ክፍል አራት ድረስ ሲፅፉ ‹‹መንግስት አልላከኝም›› የሚል ማሳሰቢያ አያይዘው አልፃፉም፡፡ አምስተኛው ላይ ነው ‹‹የአቡዬን መገበሪያ የበላ…›› እንደሚባለው መለፍለፍ የጀመሩት። እናም ከዚህ ‹‹ማሳሰቢያ›› ስነሳ ጋዜጣው ይህን ያለው በራሱ ፍላጎት ነው ለማለት ይቸግረኛል። ምን አልባት የጋዜጣው ባለቤት (መንግስት) ‹‹እንዴት አንድ ጋዜጣን እንዲህ ታስፈራራለህ?›› የሚል ጫና ስለተፈጠረበት ሊሆንም ይችላል እንዲህ በደፈናው ማስተባበል የፈለገው፡፡ ይህ ማስተባበያ ከዚህ ቀደም የታዋቂው አክቲቪስት እና አርቲስት ታማኝ በየነ ወንድም ተወልደ /ተቦርነ/ በየነ በፍትህ ላይ በፃፈው ፅሁፍ ያጣቀሳትን አይነት የጦጢት ታሪክን ያስታውሰኛል፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፤ አንዲት ጦጣ ከዛፍ ስር ቆማ ሳለ ድንገት አንበሳ ወደ እሷ ሲመጣ ታያለች፤ እናም አደጋ ስለሸተታት በፈጣን ሁኔታ ተደግፋው በነበረው ዛፍ ላይ ዘላ ትወጣለች። አያ አንበሶም ‹‹ጦጢት ውረጂ! አልበላሽም›› ይላታል-የሆዱን በሆዱ ይዞ፡፡ ይህን ጊዜም ጦጣዋ ‹‹አልበላሽምን ምን አመጣው›› አለችው ይላል የተረቱ ትርክት። እኔ ደግሞ እንዲህ እጠይቃለሁ አዲስ ዘመን ሆይ! ‹‹በፍትህ ላይ የሚፃፈው ሁሉ የመንግስት ማስፈራሪያ አይደለም›› ማለትን ምን አመጣው?
ከሚያዚያ ወር ጀምሮ በተደራጀ መልኩ መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በፍትህ ላይ አፍራሽ እና ወንጃይ ዘመቻ እንደከፈተ ለማብራራት እየሞከርኩ እንደሆነ ይሰማኛል። በዚህ የውንጀላ ዘመቻ ውስጥም በዋናነት እየተራገበ ያለው ‹‹ፍትህ ያለማስታወቂያ እስከዛሬ ድረስ በገበያ ላይ የቆየችው በአለም አቀፍ አሸባሪ ድርጅቶች፣ በኤርትራ መንግስት፣ በግንቦት 7፣ በኦብነግ፣ በኦነግ፣ በአክራሪ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ… ድጋፍ ነው›› የሚል እንደሆነም ተነጋግረናል። (መቼም ከላይ የተጠቀሱትን ሀገር እና ድርጅቶች በጨረፍታም ቢሆን የሚያውቅ ግለሰብ እነዚህ ኃይሎች ‹‹ፍትህን መደገፍ›› በሚል አጀንዳ ቀርቶ፣ በሀገሪቱ የቀን አቆጣጠር ስርአት እንኳ በጋራ እንደማይስማሙ ይረዳል። ለዚህም ነው አዲስ ዘመን እንዲህ በአንድ ላይ ሊያሰልፋቸው የቻለበትን ምክንያት ከጋዜጣው አለቆች ባሻገር ሰይጣንም ቢሆን አያውቀውም እያልኳችሁ ነው ያለሁት)
የሆነ ሆኖ በተለይም ያለፈው ሳምንት ፍትህ ለንባብ ከበቃች በኋላ ነገሮች እየተበላሹ እየሄዱ እንደሆነ የሚያመላክቱ ‹‹እከሌ›› ወይም ‹‹እከሊት›› የሚል መጠሪያ እና ባለቤት የሌለው መልእክት እየደረሰን ነው። በእርግጥ ለእኔ የደረሰኝን መልእክት ከቀድሞዎቹ የአዲስ ዘመን ውንጀላዎች የተለየ የሚያደርገው የላኪው ማንነት እና የተፃፈበት ቋንቋ የተለየ መሆኑ ብቻ ነው። ምክንያቱም በዚህ መልእክት ላይ ‹‹ላኪ›› ተብሎ የተቀመጠው እንደተለመደው ‹‹አዲስ ዘመን›› ሳይሆን ‹‹አልሸባብ›› የተባለው የሶማሊያ አሸባሪ ድርጅት ነውና፡፡ የመልእክቱ ይዘት ግን አዲስ ዘመን በሚያዚያ እና በግንቦት ወር ፍትህን ሲወነጅልበት ከነበረው በምንም አይለይም፤ ተመሳስሎአቸው ቃል በቃል ነው። ይህንን መመሳሰል ለማስረዳት ሁሉንም እዚህ ቦታ ላይ መፃፉ አንድም የቦታ ጥበት ስላለ፣ ሁለትም አስፈላጊ ባለመሆኑ አንዱን ብቻ መርጬ በሁለት ምክንያት አቀርባለሁ፡፡ የመጀመሪያው ለአንባብያን ግንዛቤ እንዲረዳ የሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው የሚመለከተው አካል እኛ ጋዜጠኞችን ከዚህ መሰሉ ማስፈራሪያ ይጠብቀንና ይከላከለን ዘንድ ግዴታው እንደሆነ ለማሳወቅ ነው፡፡ (ምንም እንኳን አስቀድሞም ቢሆን የሚያውቀው ቢሆንም እንዲህ በህዝብ ፊት ማሳወቁ ቢያንስ ለታሪክ መጥቀሙ ስለማይቀር ነው) መልእክቱ የመጣው ጋዜጣው ላይ በግልፅ በተፃፈ የጋዜጣው የ‹‹ኢ-ሜል›› (E-mail) አድራሻ ሲሆን ሙሉ ቃሉን እንደወረደ ስናነበው እንዲህ ይላል፡-
“To Ato Temesgen Desalegne
Chief Editor of Fitih magazine
Ethiopia
It has to be remembered that AlShebab has assigned me secretly to make propagation activities in Ethiopia, Somaliland, Kenya and Uganda. To accomplish the task we have agreed with you through your representative Ato Mamush Sentie in Eritrea to publish propaganda articles against the Ethiopian government, against the interest of the Ethiopian people and the American government. It has to be remembered that we have paid US dollar 24,000 for 30 consecutive editions. Now alshebab has made strategic change to accomplish its tasks. Therefore we need the 14 edition charges US dollar 11,200 dollar to alshebab. We believe that you will return back the money to our organization. If this is not fulfilled on time you will bear a cost on your representative Ato Mamush Sentie and your life according to the rule of the organization.
Alshebab wins
Ahmedin Nasir”
(ለአቶ ተመስገን ደሳለኝ
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ
ኢትዮጵያ
እንደሚታወሰው አልሸባብ በኢትዮጵያ፣ በሱማሌላንድ፣ በኬንያ እና በኡጋንዳ የፕሮፓጋንዳ ስራ እንድሰራ በሚስጥር መድቦኛል። ይህንኑ ግዴታዬን ለመወጣት በአንተ ጋዜጣ ላይ የኢትዮጵያ መንግስትን፣ የኢትዮጵያ ህዝብን እና የአሜሪካንን መንግስት ጥቅም የሚጎዳ የቅስቀሳ ፅሁፎች ይታተሙ ዘንድ አቶ ማሙሽ ሴንጢ በተባለው ተወካይህ አማካኝነት ኤርትራ ውስጥ ተስማምተን ነበር። እንደምታውቀውም ለ30 ተከታታይ እትምች 24,000 የአሜሪካን ዶላር ከፍለንሃል። አሁን ግን አልሸባብ ዕቅዶቹን ለመፈፀም የስልት ለውጥ አድርጓል። ስለዚህም 11,200 የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን የ14 እትሞች ክፍያ ለአልሸባብ እንዲመለስ እንፈልጋለን። ይህንን ገንዘብ ለድርጅታችን ትመልሳለህ ብለንም እናምናለን። ነገረ ግን ምናልባት ይህ ሁኔታ በሰዓቱ ባይሳካ በድርጅቱ ህግ መሰረት በአቶ ማሙሽ ሴንጢና በአንተ ህይወት ዋጋ ትከፍላለህ።
አልሸባብ ያሸንፋል።
አህመድ ናስር)
እንግዲህ ይህ መልዕክት የተላከው ከአልሸባብ-ለእኔ መሆኑ ነው። በእርግጥ የዚህ መልዕክት ዋናው ቅጅ ሚያዚያ 2/2004 ዓ.ም በወጣው‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ-ክፍል ሶስት›› በሚል ርዕስ የታተመው ጋዜጣ ላይ የተጠቀሰ ሲሆን ይህ ደግሞ የእንግሊዝኛው ግልባጭ መሆኑ ነው፡፡ ለማስታወስ ያህልም በጠቀስኩት ቀን ከታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ልቀንጭብላችሁ፡- ‹‹ከምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ለተቀመጠችው ሀገራችን አልሸባብን ጨምሮ ሌሎችን ከውስጥም ከውጭም የፀረ-ሰላም ኃይሎች ያሰባሰበው የኢሳያስ አፈወርቄ መንግስት ናቅፋ እስከፍትህ ቢሮና አምደኞች ኪስ አይደርስም ማለት አይቻልም፤ ይህ ባይሆን እመኛለሁ፤ እኔ ግን በበኩሌ ጠረጠርኩ፤ በርካታ ማሳያዎች አሉኛ›› የሚል ሆኖ እናገኘዋለን። አልሸባብ እንኳን ከፍትህ ጋር የስራ ስምምነት ሊያደርግ ቀርቶ ፍትህ የሚባል የአማርኛ ጋዜጣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስከመኖሩ ያውቃል? የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ መልዕክቱን ስናነብው በእርግጥም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ደጋግሞ ፍትህን ሲወነጀል የነበረበት መልዕክት መሆኑ አያከራክርም። ልዩነቱ የአዲስ ዘመን በአማርኛ ቋንቋ፣ አልሸባብ ላከው የተባለው ደግሞ በእንግሊዝኛ መሆኑ ብቻ ነው። በነገራችን ላይ ይህንን የሀሰት መልእክት ፈጥሮ እኔን ለመወንጀል ያሰበው ሰው ለውንጀላው ከመጣደፉ የተነሳ፣ የላከው መልዕክት እና ከፍትህ ጋር ያቆራኘው አልሸባብ ጭራሹኑ እንደማይተዋወቁ በግልፅ የሚያሳይ ስህተት ሰርቷል። ይኸውም ላኪው የአራት የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ወኪል ነኝ ብሎን ሲያበቃ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በላከው መልዕክት ላይ ግን የኢትየጵያ የስራ ቋንቋ የሆነውን አማርኛ ደባልቆበታል፡፡ ‹‹አቶ…›› እያለ ፅፎ ማለቴ ነው፡፡
መቼም አልሸባብ የተቋቋመውም ሆነ እየታገለ ያለው እንደ አልቃይዳ ‹‹ድንበር የለሽ›› ወይም ሳውዲአረቢያን አልያም ግብፅን በሼሪያ ህግ ላስተዳድር ብሎ አይደለም፡፡ የአልሸባብ አፈጣጠር ግልፅና አጭር ነው፡፡ ይህ አሸባሪ ድርጅት የተመሰረተው ‹‹ሶማሊያ ሀገራችን›› ባሉ የሶማሊያ ተወላጆች ሲሆን አላማቸውም ‹‹ሶማሊያን በሼሪያ ህግ ማስተዳደር›› የሚል እንደሆነ ደጋግመው ገልፀዋል፡፡ እንግዲህ በዚህ ከተስማማን ‹‹በዕቅዴ ላይ ጣልቃ ገቡ›› በሚል ኩርፊያ በኢትዮጵያ፣ በኬኒያ፣ በኡጋንዳ እና ከራሷ ሶማሊያ በተገነጠለችው ሶማሌላንድ ላይ የሽብር ድርጊት ለማካሄድ አፉን በአማርኛ የፈታ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ የፕሮፓጋንዳ ሀላፊ የሚሾምበት ምንም አይነት ምክንያት የለውም፡፡ ስለዚህም የአልሸባብ ወኪል ነኝ የሚለው ሰው ‹‹አቶ…›› የሚለውን የአማርኛ የአክብሮት አጠራር ሳይሆን ‹‹ሚስተር…›› የሚለውን የእንግሊዝኛ አቻ ትርጉምን ነው ይጠቀም የነበረው ማለት ነው፡፡ ይህን አይነት ቅድመ-ጥንቃቄ ቢያደርግ ደግሞ ቢያንስ የእኔ አስፈራሪና ወንጃይ ‹‹ድርሰት›› የተዋጣለት ይሆን ነበር። አሊያም ‹‹አቶ…›› የሚለውን የአማርኛ ቃል የግድ መጠቀም አለበኝ ካለ እንደተለመደው ከአንዱ ኢትዮጵያዊ አሸባሪ ድርጅት ጋር አቆራኝቶ ቢወነጅለኝ የተሻለ ይሆንለት ነበር።
ሌላው የዚህ መልእክት ባለቤት የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ እንደሆነ የሚያሳየው ፍትህን በእንግሊዘኛ ሲፅፍ፣ እንግሊዝኛ ሆሄያት ተጠቅሞ አማርኛ በሚፃፍበት መልክ “Fitih” ብሎ መሆኑን ልብ ስንል ነው። መቼም ‹‹ፍትህ›› የሚለው ቃል የአማርኛ እንጂ የእንግሊዘኛ ቃል አይደለም። ስለዚም ፀሐፊው አልሸባብ ቢሆን ይህንን አፃፃፍ ከየትም ሊያገኘው ስለማይችል ‹‹ፍትህ›› ብሎ ለመፃፍ ሁለት አማራጭ ብቻ ነው የሚኖረው። የመጀመሪያው አማራጭ ከፍትህ ኢ-ሜል አካውንት ላይ ‹‹ፍትህ›› የሚለውን በሚያውቀው እንግሊዘኛ የተፃፈውን መውሰድ ነው። ይህን ቢያደርግ ኖሮ የፍትህ አካውንት ‹‹fetih_gazeta@yahoo.com” የሚል ስለሆነ የማስፈራሪያው ባለቤት ‹‹fitih›› ብሎ ሳይሆን የሚፅፈው ‹‹fetih›› ብሎ ይሆን ነበር፡፡ ሁለተኛው ምርጫው ደግሞ ከፍትህ ዌብሳይት ላይ መውሰድ ነው። ዌብሳይቱ ላይ ያለው “www.fetehe.com” ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያዊ ያልሆነው አልሸባብ ፍትህ የሚለውን የአማርኛ ቃል የዌብሳይቱ መጠሪያ የሆነውን ‹‹fetehe›› ብሎ ይጠቀም ነበር ማለት ነው፡፡ ታዲያ አማርኛ የማያውቀው አልሸባብ “Fitih” የምትለውን በእንግሊዝኛ ፊደል የተፃፈች የአማርኛ ቃል ከየት አመጣት? (እንዴት ነው ነገሩ? አልያም አንድዬውን እኛ እዚሁ አራት ኪሎ ተጎልተን ሳንሰማ አልሸባብ የሚባል ኢትዮጵያዊ ድርጅት ተመስርቷል በሉንና በሳቅ እንፈንዳ? ሌላ ማድረግ ባንችል በሳቅ ራሳችንን ማፈንዳት ማን ይከለክለናል?)
የአልሸባቡ ሰው ፃፈው ከተባለው ተጨማሪ አንድ ስህተት እንምዘዝ፡፡ ደህና! እንደሚታወቀው የእኔ የሀላፊነት ደረጃ ‹‹ዋና አዘጋጅ›› የሚል ነው፡፡ ይህ ሀላፊነት በእንግሊዝኛ ሲሆን ደግሞ ‹‹Editor in chief›› የሚል ይሆናል፡፡ ሆኖም ‹‹ዋና አዘጋጅ›› የሚለውን ቃል ከአማርኛ ወደ እንግሊዘኛ ቃል በቃል ስንቀይረው ‹‹Chief Editor›› የሚል ይሆናል፡፡ ይህ ትርጓሜ ደግሞ አማርኛ ቋንቋን ለማይናገር ሰው ስህተት ሆኖ ሳለ፣ የአልሸባብ ወኪል የተባለው የፃፈው ግን ከአማርኛ በቀጥታ ተርጉሞ ‹‹Chief Editor›› ብሎ ነው፡፡ እዚሁ ጋር ያለው ሌላ ስህተት ፅሁፉን ለመወንጀል የቸኮለ ፀሀፊ እንደፃፈው ያሳየናል፡፡ ምክንያቱም ፍትህ ጋዜጣ ስትሆን፤ ጋዜጣ ደግሞ በእንግሊዘኛ ‹‹News paper›› እንጂ ‹‹Magazine›› አይደለም፡፡ ሜጋዚን ለሚለው ቃል አቻ የአማርኛ ትርጉም ‹‹መፅሄት›› ነው፡፡ አልሸባብ የተባለው ሰው ‹‹Magazine›› እያለ መፃፉን ልብ በሉ፡፡ እዚሁ መልዕክት ላይ አንድ ግጥምጥሞሽ ልጥቀስላችሁ፡፡ ከዚህ ቀደም የፍትህ ሚኒስቴር በበርካታ ክስ በከሰሰኝ ጊዜ ያቀረበው ማስረጃ በተከታታይ የታተሙ 14 የፍትህ እትሞችን ሲሆን፣ አልሸባብም ፍትህ ላይ ቀረኝ አለ የተባለው ሂሳብ የ14 ዕትም ነው፡፡ …ይህ መመሳሰልስ የአጋጣሚ ይሆን? ወይስ…
የሆነ ሆኖ ከዚህ የሀሰት መወንጀያ ለማሳያ ያህል እነዚህን የመዘዝኩት በሀገራችን ዜጎች ምን ያህል በሀሰተኛ ማስረጃ እና ምስክር ለእስር እየተዳረጉ እንደሆነ እንድትረዱት ነው። ከዚህ ውጭ ከአራት ሳምንት በፊት ያቀረብኩላችሁ የሲሳይ አጌና ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› መጽሐፍ ለፍርድ ቤት ይቀርቡ የነበሩ ማስረጃዎች በፎርጅድ እና በሀሰተኛ ምስክርነት የተሞሉ በመሆኑ ራሱ አቃቤ ህግ ለተደጋጋሚ ጊዜ በፍርድ ቤት ሲያፍር እንደነበረ ማስነበቡን አስታውሰን እንለፍ።
በተቀረ በመልዕክቱ ውስጥ አልሸባብ በፍትህ አስራ ስድስት ተከታታይ እትሞች ላይ የሽብር ፅሁፎቹ እንደታተሙለት ገልጿል፡፡ መቼም የትኛውም የፍትህ አንባቢ እንደሚያስታውሰው በፍትህ ላይ አንድም ቀን ቢሆን የኢትዮጵያን ህዝብና የአሜሪካንን መንግስት ጥቅም የሚፃረር ወይም አልሸባብን የሚደግፍ ፅሁፍ ታትሞ አያውቅም፡፡ ይህ ማለት ግን የኢትዮጵያን መንግስት ደካማ ፖሊሲ፣ የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የፕሬስ አፈና፣ የባለስልጣናቶችን ዘረፋና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምክንያታዊ ትችቶች አላቀረብንም ማለት አይደለም፡፡ ህዝብ ማወቅ አለበት ያልነውንም ህገወጥ ድርጊት አጋልጠናል፡፡ ይህ ደግሞ አንድም የሞያ ግዴታችን ሲሆን ሁለትም እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ ሀላፊነታችንን መወጣታችን ነው፡፡ ስለዚህም እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ፍትህን ከአልሸባብ ጋር አያይዞ መወንጀሉ ክፉ ጥርጣሬን ያጭራል፡፡ ከጥርጣሬዎቹ ውስጥ ምናልባት የተለመደው የክስ ቻርጅ በዚህ በኩል እንዲያልፍ ለማድረግ ይሆን? የሚለው አንዱ ሊሆን ይችላል፡፡ በመልዕክቱ ላይ የተገለፀውን ዛቻ ተከልሎ በፍትህ አዘጋጆች ላይ የ‹‹ቀይ ሽብር›› እርምጃ ለመውሰድ ያሰበ አካል ‹‹በልጅ አመካኝቶ…›› አካሄድን ለመከተል አስቦ ይሆን? የሚለው ደግሞ ሌላኛው ክፉ ጥርጣሬ ሊሆን ይችላል፡፡ …ጊዜ የሚፈታው ቋጠሮ ነው፡፡
ርዕሰ ጉዳዩን ስናጠቃልለውም እነዚህ በመንግስታዊው ጋዜጣ እና በአፍቃሬ ኢህአዴግ ድረ-ገፅ ከወጡት ቁጥራቸው የበዛ ፅሁፎች መሀከል በጥቂቱ ለማሳያነት ያህል የጠቀስኳቸው ውንጀላዎች በአምባገነዊ ስርዓት ውስጥ ያለውን የነፃ ጋዜጠኝነት ፈተና በበቂ የሚያሳይ ይመስለኛል። ስርዓቱ እዚህ ድረስ ወርዶ ለመወንጀል እየሞከረ ያለው ሀገራችንን ጥለን እንድንሄድ አልያም ራሳችንን በዝምታ እንድንሸብብ ከሆነ፤ የሚሰማ ካለ አቋማችንን በተደጋጋሚ ማሳወቃችንን ብቻ አስታውሶ ከማለፍ ውጭ አማራጭ የለውም፡፡ እንዲሁም የሃገሪቱ ህገ-መንግስት ላይ የሰፈሩ የዜግነት ነፃነት አክባሪ ዕሴቶችን አምነን ስለሀገራችን በዋተትን፣ ለተጎዱና ለተገፉት ወገኖቻችን ባበርን፣ የህዝባችን ያለስጋት በነፃነት የመኖር መሻት ይተገበር ዘንድ በብዕሮቻችን በቃተትን፤ በማንኛውም መልክ ሊመጣ የሚችል አደጋ ካለ ከመቀበል ውጪ ሌላ ምርጫ የለንም። ምክንያቱም ሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ናትና።