Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday 16 April 2013

የመለስ ዜናዊ ምስል በገንዘብ ላይ?!



Posted: April 16, 2013 in Uncategorized
0
Image                                                                                                                                                                                                                   
አንዳንዴ ወሬ በባዶ ሜዳ ይናፈሳል። ብዙ ጊዜ ትንሽ ጫፍ ይዞ ይናፈሳል። የህወሓት መንግስትን በተመለከተ አያደርጉም የምለው ነገር ስለሌለ ለመጠራጠሬ ገደብ አብጂቸ ነው የምጠራጠረው። ብዙ ጊዜ ግን ስለነሱ የሚወራውን አልጠራጠርም። ያደርጉታል።
ሰሞኑንን (ምናልባት ሌሎቻችሁ ከሰማችሁ ቆይታችሁ ይሆናል!) የህወሓት መንግስት የአመስት መቶ ብር ኖት የማዘጋጀት ሃሳብ እንዳለው እና በገንዘቡ ላይ የ “ባለ ራዕዮ መሪ” ምስል እንደሚያርፍበት ሰማሁ። የታላላቅ መሪዎችን ምስል በምንዛሬ ላይ ማስቀመጥ አዲስ ነገር አይደለም። ጥያቄው ግን ታላቅ ማነው? ታላቅነቱ እንዴት ነው? በየትኛውም ማህበረሰብ የበቀሉ የፖለቲካ መሪዎች የራሳቸው የሆኑ ተቃዋሚዎች እንደሚኖራቸው እሙን ነው። ነገር ግን ከሚከተሉት ፖሊሲ በመነሳት ዜግነታቸው ጭምር ጥያቄ ውስጥ የገባ እና በእኛ ሃገር ዘይቤ በባንዳነት ሂሳብ የተያዙ የሌሎች ሃገር መሪዎች ያሉ አይመስለኝም። ያውም ምስላቸው ምንዛሬ ላይ የሚወጣ?! ፈጽሞ አይመስለኝም። የቻይናው ማኦ የጠባብ ብሔርተኛ የፖለቲካ መሪ አልነበረም። የዘር ትምክህት አባዜ አልነበረውም። የኢንዶኔዢያው ሱካርኖ እንደዚያው። የፓኪስታኑ መሃመድ አሊ ጂና እንደዚያው። ብዙ የ”ሶስተኛውን ዓለም” ሃገሮች መሪዎች ለአብነት ማንሳት ይቻላል።

Liberating a “Prison Nation” By Prof. Al Mariam

Liberating a “Prison Nation” By Prof. Al MariamEthiopia today is a “prison of nations and nationalities with the Oromo being one of the prisoners”, proclaimed the recently issued Declaration of the Congress of the Oromo Democratic Front (ODF). This open-air prison is administered through a system of “bogus federalism” in which “communities exercise neither self-rule nor shared-rule but have been enduring the TPLF/EPRDF’s tyrannical rule for more than two decades.” The jail keepers or the “ruling party directly and centrally micro-manage all communities by pre-selecting its surrogates that the people are then coerced to ‘elect’ at elections that are neither free nor fair”. Ethiopians can escape from “prison nation” and get on the “path to democracy, stability, peace, justice, and sustainable development” when they are able to establish a democratic process in which “all communities elect their representatives in fair and free elections.”
The ODF is a “new movement” launched by “pioneers of the Oromo nationalist struggle” who “have mapped out a new path that embraces the struggle of all oppressed Ethiopians for social justice and democracy.” Central to the collective struggle to bust the walls and crash the gates of  “prison nation” Ethiopia is a commitment to constitutional democracy based on principles of “shared and separate political institutions as the more promising and enduring uniting factor” and robust protections for civil liberties and civil rights. Shared governance and the rule of law provide the glue “that will bind the diverse nations into a united political community” and return to the people their government which has been privatized and corporatized by the ruling regime “to advance and serve their partisan and sectarian interests.”

Monday 15 April 2013

የበረሃው ንድፈ-ሀሳብና የኢሕአዴግ መንግስታዊ ቆመጥ ዳንኤል ሺበሺ

በረሃ በነበሩበት ወቅት ከነደፏቸው ንድፈ- ሀሳብ እና ወደ ቤተመንግስት ከገቡ በኋላ በጎሣ፤ በደምና በአጥንት ቆጠራ፤ በፖለቲካዊ አስተሳሰብ ቅርበት/ርቀት ወይም ልዩነት ወገንተኝነት እየለዩና ዳግም እንዳያገግም አከርካሪውን እየሰበሩ፤ ዜጎች እንደየፍጥረታቸው ሳይሆን እንደየራሳቸው እንዲያስቡ፤ ካልሆነም ዳግም እንዳያቆጠቁጥ እንቡጥ እንቡጡን እየቀነጠሱ ቢያንስ ለአንድ ትውልድ
የዘለቁ ሲሆን፤ ጎን ለጎን የራሳቸውን (ከግለሰብ እስከ ፓርቲያቸው ድረስ) የኢኮኖሚ ጡንቻዎችን በማፈርጠም፤ ቀጥሎም በፖለቲካ ካፕታላይዝ እንዲሆኑ ከሚያደርጋቸው ዕቅድና ስትራቴጂ አካል ........ብሔርንና የቀበሌ መታወቂያ ደብተርን ምን አገናኘው?
http://minilik-salsawi.blogspot.com/2013/04/blog-post_15.html

 ፍኖተ ነጻነት
የአማራ ብሔር ጉዳይ ከግንቦት 1983 ዓ.ም በፊት ያለቀ ጉዳይ ነው፡፡ የአማራ ብሔር ተወላጆችን አከራካሪ ለመስበርና ሁለንተናዊ አቅማቸውን (በተለይም የኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ አቅማቸውን) ለማሽመደመድ ውጥኑንና ንድፈ ሀሳቡን ከግንቦት 20,1983 ዓ.ም በፊት በረሃ ባሉበት ጊዜ የወሰኑትና አሁን እየተተገበሩት ነው ባይ ነኝ፡፡  ይህንን ለማረጋገጥ አንድ ምሳሌ ለመጥቀስ ወደድሁ፡፡
ኢህአዴግ አገሪቱን በተቆጣጠረበት ማግሥት ጀምሮ እስከ 1990 መጨረሻዎቹ ድረስ እኔ በነበሪኩበት አከባቢ የሠላምና
መረጋጋት ኮሚቴ አባልነትን ጨምሮ በተለያዩ ፖለቲካዊ መዋቅሮች ውስጥ በተለያየ የኃላፊነት ቦታዎች፤ በሹመት፤

Sunday 14 April 2013

ከቤንሻንጉል የተፈናቅለው የነበሩት አማርኛ ተናጋሪዎች ለደረሰብን ጉዳት ተጠያቂው ብአዴን ነው አሉ

IMG0065A
ከሚኖሩበት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በፍኖተሠላም ሰፍረው የነበሩት አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች “እንድፈናቀል ያደረገንና ለደረሰብን ጉዳት ተጠያቂው የአማራ ክልላዊ መንግስት ገዢው ፓርቲ ብአዴን ነው፡፡” ሲሉ ለዝግጅት ክፍላችን አስታወቁ፡፡

ተፋናቃዮቹ እንደሚሉት “ስንፈናቀል ስድብ፣ዛቻ ድብደባ፣እስራትና ዝርፊያ የደረሰባቸው አሉ፡፡ የስነ ልቦና ጉዳት ደርሶብናል፡፡ ሀብትና ንብረታችን ጥለን በ24 ሰዓት ከአካባቢው እንድንወጣ ተደርገናል፡፡ ለዚህ ሁሉ ድርጊት ግንባር ቀደም ተጠያቂው ብአዴን ነው” በማለት ፓርቲውን ወቅሰዋል፡፡

ተፈናቃዮቹ ለዝግጅት ክፍላችን እንደሚያስረዱት “በሠላም ሠርተን በምንኖርበት ቦታ ልዩ ኃይል (ፌዴራል ፖሊስ) አዝምቶ ያስደበደበንና ከሥራና ከመኖሪያ ቦታችን ያስወጣን የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልላዊ መንግስት የአካባቢው አስተዳዳሪዎች ናቸው፡፡

ምን አጠፋን? ምን በድለናችሁ ነው? እንዲህ የምታሰቃዩን ብለን ስንጠይቅ ፤ የክልላችሁ መንግስት የማዳበሪያ ገንዘብ ዕዳ አለባቸው ፤ነፍስ ገዳዮች አሉበት፤ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሽፍታ ማጠራቀሚያ ሆኗል፡፡ ህዝቤን መልሱልኝ ብሎ ስጠየቀን ነው፡፡ ብለውናል፡፡ ይህ ሁሉ ድብደባና ዝርፊያ ሲፈፀምብን ብአዴን ዝም ብሎ ይመለከታል፡፡ ስለዚህ ለደረሰብን ጉዳት ሁሉ ግንባር ቀደም ተጠያቂው ብአዴን ነው፡፡ ” ሲሉ በስፍራው ለተገኙት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

ቁጥራቸው በግምት ከ 3ሺ በላይ የሆኑ እንዚህ ተፈናቃዮች በጊዜያዊነት ሰፍረው በነበረበት ፍኖተ ሰላ ከተማ ተገኝተው ለነበሩት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች እንዳስረዱት “ቤት ንብረታችንን እንዳለ ጥለን እንድንወጣ ተደርገናል፡፡

የ“አብዮታዊ ዲሚክራሲ” መንገድ የት ያደርሳል ? (በአብርሃ ደስታ)

404269_246213892126226_1643997848_nወቅቱ የአካባቢና ከተሞች “ምርጫ” የሚካሄድበት ነው ። ሰለ “ምርጫ” ሲታሰብ ስለ አማራጮች ማሰላሰል ግድ ነው ። አንድ ፖለቲካዊ ምርጫ ምርጫ የሚያሰኙት ነገሮች ምንድን ናቸው? ምርጫው ዲሞክራሲያዊና
የተሟላ እንዲሆን አማራጮች (ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች) መኖር አለባቸው። ምክንያቱም በምርጫ የሚመርጥ ህዝብና የሚመረጡ የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮች መኖር አለባቸው ። መራጩ ህዝብ በአግባቡ መምረጥ እንዲችል ለምርጫ ሰለሚቀርቡ ፓርቲዎች በቂ መረጃ ሊኖረው ይገባል።
ህዝቡ በቂ መረጃ እንዲኖረው በምርጫ የሚቀርቡ ፓርቲዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ከህዝቡ ተገናኝተው አማራጭ ፖሊሲዎቻቸውና ዓላማቸው ማስተዋወቅ ይኖርባቸዋል። እነዚህ ፖሊሲዎችና ዓላማዎች ለማስተዋወቅ ነፃና ገለልተኛ የግል ሚድያዎች መኖር አለባቸው። መራጩ ህዝብም በነፃነት የፈለገውን የመምረጥ መብት ሊከበርለት ይገባል።
ስለዚ በምርጫ የፖለቲካ ድርጅቶች ማቅረብ የሚጠበቅባቸው “የሚመረጡ ሰዎች” ብቻ ሳይሆን ለመመረጥ የሚያስችላቸው የፖሊሲ አቅጣጫዎች ጭምር ነው ።
የኢትዮዽያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ኢህአዴግ ዓፋኝ ስለመሆኑ ይነግሩናል። ኢህአዴግም በበኩሉ ተቃዋሚዎች አማራጭ ፖሊሲዎች እንደሌላቸው ያስረዳል ። ነገር ግን ተቃዋሚዎች አማራጭ ፖሊሲ ይኑራቸው አይኑራቸው “አለን” የሚሉትን ነገር ለህዝብ እንዲያቀርቡት ተፈቅዶላቸዋል ወይ? ፓሊሲ እንዳላቸው ወይ እንደሌላቸው መወሰን ያለበት መራጩ ህዝብ አይደለምን ?
የተቀዋሚዎች አማራጭ የፖሊሲ አቅጣጫ ለማወቅ እንቸገር ይሆናል። ምክንያቱም ገዢው ፓርቲ በሚፈጥረው የመረጃ ዓፈና (የግል ሚድያ ዓፈና) ፣ የፖለቲካ ሙስና ፣የኢኮኖሚ ሸበራ፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ወዘተ የተቀዋሚ ፓርቲ ተወካዮች ከህዝቡ ጋር ተገኛኝተው መግባባት ተስኗቸዋል። በአንፃሩ ደግሞ ገዢው ፓርቲ ኢህአደግ የመንግስትን ሃብት (ለምሳሌ የኢትዮዽያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት) ለግል ፕሮፓጋንዳ በማዋል፣ግለሰዎችን በጥቅማጥቅሞች በመደላል ፣ከምርጫ ደምብ ውጪ የራሱ ሚድያ በመጠቀም (ለምሳሌ ህወሓት ድምፂ ወያነ ሲኖረው ኢህአዴግ ደግሞ ሬድዮ ፋና አለው) ከህዝብ ጋር ያለ ገደብ የመገናኘት ዕድል አለው። ኢህአዴግ ታድያ ከህዝብ ጋር እየተገናኘ የትኛው አማራጭ ይዞ ነው የሚቀርበው ? ተቀዋሚዎች አማራጭ ፖሊሲ ከሌላቸው ኢህዴግስ ይኖረው ይሆን?

ህ.ወ.ሓ.ት. አማራውን ለምን በጠላትነ ፈርጆ ያጠቃዋል?

ገብረመድህን አርአያ
ፐርዝ፤ አውስትራሊያ
Gebremedhin Araya former TPLFይህ ጽሑፍ ትኩረት የሚሰጠው በትግል በረሃ በነበርንበት ወቅት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት.) በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖቶች ላይ ሲከተል የነበረውን አቋሙን
ተቀብሮ ከነበረበት ጉድጓድ አውጥቼ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እነማን ናቸው የሚለውን ታሪካቸውን እና የተፈጸመውን ጸረ-እምነት ግፍ በአጭሩ ለማሳወቅ ነው።
ህ.ወ.ሓ.ት. ገና ሲፈጠርና ተ.ሓ.ህ.ት. ተብሎ እንደተመሰረተ ሙልጭ ያለ ጸረ-ዲሞክራሲ ድርጅት ነው። በጸረ-ኢትዮጵያነትና በጸረ- ሕዝብነት የተሰማራ ቅጥረኛ ድርጅት መሆኑን ብዙ ጊዜ በጽሑፍና በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ለኢትዮጵያ ህዝብ ተናግሬአለሁ። የአሁኑ ጽሑፌ ህ.ወ.ሓ.ት. በሃይማኖት ላይ ሲከተለው የነበረውን ፖሊሲ ገና ከመጀመሪያ ትግሉ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ የነበረውን ጸረ- ሃይማኖት ተግባራቱን የኢትዮጵያ ሕዝብ በግልጽ አውቆታል። እኔ ደግሞ የራሴን ልበል።
በ1969 መጀመሪያ ጀምሮ “ወይን” በሚለው የድርጅቱ ልሳን መጽሔት ላይ በተደጋጋሚ “የክርስትና ሃይማኖትና አማራው” በሚል ርእስ ተጽፎ የሚወጣው ጽሑፍ፣ “የክርስትና ሃይማኖት የአማራው ዋና መሳሪያና የግዛቱን ህልውና ማስጠበቂያ ነው፣ በመሆኑም የትግላችን ጠላት አማራውና መሳሪያው የተዋህዶ ክርስትና ስለሆኑ አብረው እንዲጠፉ ማድረግ አለብን” እያለ ያትት ነበር። ይህንን መጽሔት በሰፊው ለታጋዩና ለአባላቱ በማሰራጨት ሰፊ ቅስቀሳ አካሂዶበታል። በነሐሴ 1969 “ወይን” መጽሔት አማርኛ ቋንቋም አብሮ መጥፋት እንዳለበት ሃተታ ይዞ ወጥቷል።
“ወይን” የምትለውን መጽሔት የሚያዘጋጁት ከፍተኛ የአመራር አባላት በፕሮፓጋንዳ ቢሮ ሆነው ለዚሁ ተግባር የተዘጋጁ ጽሑፎችን በስፋት የሚያሰራጩት፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየና መለስ ዜናዊ ነበሩ። እነዚህ ሶስቱ የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር አባላት እብዶችና በጸረ- ሃይማኖት፣ ጸረ-አማራ ባህሪያቸውና አቋማቸው በሰላማዊው ህብረተሰብና ታግዩም ጭምር በግልጽ የሚታወቁ ናቸው።

Ethiopia: Regime tries to break morale of jailed female journalist By Sudan Tribune

In a protest letter to Birhan Hailu, Ethiopia's justice minister, Joel Simon, CPJ's Executive Director asked that Alemu, whose health has reportedly deteriorated since being held on terrorism charges, to withdraw the threat of placing her in solitary confinement.
Human rights and press freedom groups have long accused Addis Ababa of using its controversial terrorism legislation to curb opposition and stifle the media in the East African nation. "Prison authorities have threatened Reeyot with solitary confinement for two months as punishment for alleged bad behavior toward them and threatening to publicize human rights violations by prison guards" said CPJ's letter, which was published on its website.
Despite pledges to the contrary Ethiopia's Ministry of Justice has failed to ensure that Reeyot's full human rights have not been violated during her detention, which began in June 2011.
"We urge you to fulfill Ethiopia's promise to build a humane and democratic state by withdrawing the threat of solitary confinement against Reeyot and ensuring her access to adequate medical care" CPJ said.
"No journalists should face detention or imprisonment in the exercise of their duty"