Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 10 August 2012

በደሴ ከተማ ሙስሊሞች ከፌደራል ፖሊስ ጋር ተጋጩ


Add captio

ኢሳት ዜና:-የጁመኣን ሶላት ጸሎት ለማድረስ ዛሬ በደሴ አረብገንዳ የተሰባሰቡ ሙስሊሞች ከፖሊስ ጋር ሲጋጩ ውለዋል።

ነሀሴ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
በደሴና አካባቢዋ የሚገኙ ሙስሊሞች አረብገንዳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው መስጊድ ለመስገድ በሚሰባሰቡበት ወቅት፣ በስፍራው ሲጠባበቁ የነበሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በመስጊዱ ጸሎት ማድረስ አይቻልም በማለት መከልከላቸውን ተከትሎ ነው ችግሩ የተፈጠረው።
ፖሊሶቹ ” ሁላችሁም በአካባቢያችሁ በሚገኙ መስጊዶች መስገድ ትችላላችሁ፣ ወደ ዚህ ቦታ የምትመጡት ግን ሌላ የፖለቲካ አጀንዳ ለማራመድ ነው በማለት” ሲያስታዉቁ፣ ሙስሊሞች በበኩላቸው ” ብላችሁ ብላችሁ የምንሰግድበትን መስጊድ እናንተው ትመርጡልን ጀመር” በማለት ውዝግቡ ተጀምሯል። 
ፖሊሶቹ በምእመኑ ላይ እርምጃ መውሰድ ሲጀምሩ፣ ምእመኑም በፖሊሶች ላይ ድንጋይ በመወርወር የአጸፋ እርምጃ ወስዳል።
በዚሁ ውዝግብ ከ5 ያላነሱ ፖሊሶች ሲቆስሉ ከምእመኑ ምን ያክል ሰዎች እንደተጎዱ ለማወቅ አልተቻለም። ይሁን እንጅ በርካታ ወጣቶች በፖሊስ መኪኖች ተጭነው ተወስደወዋል፣ ጉዳት የደረሰባቸውም በርካታ መሆናቸው ታውቋል።
ዘገባውን እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ፖሊሶች መንገዶችን በማጠር በአካባቢው የሚዘዋወረውን ሙስሊም ሁሉ እየያዙ በማሰር ላይ ናቸው።
በርካታ የንግድ ድርጅቶች የተዘጉ ሲሆን፣ በከተማውም ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል።
በአዲስ አበባም ቁጥሩ ከ 500 ሺ እስከ 800 ሺ የሚጠጋ ህዝብ ዛሬ በአንዋር መስኪድ ተካሂዷል። መሪዎቹ እንዲፈቱም በድምጽ ጠይቋል።
በጅማ ፣ በሻሸመኔ ሶስት መሲኪዶች  እንዲሁ ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጓል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ ወርቅነህ ገበየሁ ከሁለት ቀናት በፊት ፦ “ህብረተሰቡ ተረባርቦ ይሄንን ተቃውሞ የማያስቆም ከሆነ፤ የከፋ ነገር ይመጣል!” በማለት ማስጠንቀቃቸውን ይታወሳል።

የአቶ መለስ መሰወር የስልጣን ሽኩቻና ፍርሀትን ጋርጧል ተባለ

የአቶ መለስ ለረጅም ግዜ ከስልጣን መሰወር፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ድብቅ የስልጣን ሽኩቻ፤ በአፍሪካው ቀንድ ደግሞ፤ ፍርሀትን እንደፈጠረ ፋይናንሳል ታይምስ የተሰኘው ጋዜጣ ዘገበ።
መንግስት አቶ መለስ ከሕመማቸው እያገገሙ እንደሆነ ቢናገርም፤ የአቶ መለስ ዜናዊ መሰወር ግን የጎሳ ፖለቲካን አደጋዎች እንዲያገጡ በሚያደርግና፤ ስርአቱን ለአደጋ በሚያጋልጥበት መለኩ ድብቅ የስልጣን ሽኩቻን ጭሯል ሲል ፋይናንሻል ታይምስ ዘግቧል።
“ስለአቶ መለስ ጤና ሁኔታ ምንም አይነት መረጃ የለንም” ያለው፤ የኬንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ፤ “ግልጽ የስልጣን ተተኪ ባለመኖሩና የዚያች አገር ፖለቲካ በቋፍ በመሆኑ፤ ሁኔታው አሳስቦናል” ሲሉ ተናግረዋል።
ተቃዋሚዎችን ቢያፍኑም፤ ጋዜጦችን ቢዘጉም፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ከምርጫ ጋር በተያያዘ ቢገድሉም፤ እንዲሁም ሕዝቡን በድህነት ቢይዙም፤ አቶ መለስ የምእራባዊያን መንግስታት ድጋፍ አላቸው ያለው ፋይናንሺያል ታይምስ፤ አንድ ምእራባዊ ዲፕሎማትን ጠቅሶ፤ “ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ ባላቸው ሚና፤ እንደበርማ ከመወገዝ ተርፈዋል” ሲሉ አትቷል።
ኢትዮጵያ በይስሙላ የአራት ፓርቲዎች ግንባር በሆነው ኢህአዴግ የምትመራ፤ ነግር ግን በአቶ መለስ የሚመራው ሕወሀት አብላጫውን ስልጣን የያዘባት አገር እንደሆነችና፤ አንዳንዶች አቶ መለስ ባይኖሩም ችግር አይፈጠርም ቢሉም፤ አቶ መለስ ባላቸው ሰፊ ስልጣን የተነሳ፤ ለረጅም ግዜ በዙሪያቸው ያሉትን ሰዎች እንዳሻቸው ሲሾሙና ሲሽሩ ስለኖሩ፤ እሳቸውን የመተካት ሂደት በፓርቲው ልሂቃን መካከል ትልቅ የስልጣን ሽኩቻ ይፈጥራል ብሏል።
ፋይናንሺያል ታይምስ፤ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖምን፤ አቶ ብርሀነ ገ/ክርስቶስንና ወ/ሮ አዜብ መስፍንን በስልጣን ተፎካካሪነት አስቀምጠል።

ገዢው ፓርቲ ህዝብን ያረጋጋሉ የተባሉ ካድሬዎችን ወደ ገጠር አሰማራ


ኢሳት ዜና:-የአቶ መለስ ዜናዊ የጤና ሁኔታ ከፍተኛ የህዝብ የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ገዢው ፓርቲ ህዝብን ለማሳመን ይችላሉ ብሎ የሚያስባቸውን ካድሬዎች ወደ ገጠር መላኩ ታውቓል።


ነሀሴ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የብአዴን ካድሬዎች በአማራ ክልል በሚገኙ ወረዳዎች ህዝቡን እንዲያረጋጉ እንዲሁም የህዝቡን ስሜት እንዲያጠኑና ወደ ማእከል ሪፖርት እንዲያደርጉ ተልከዋል።
ካድሬዎቹ ህዝቡን ለማሳመን ምን ማለት እንዳለባቸው በትክክል እንደማያውቁ፣ ይልቁንም ራሳቸው ካድሬዎቹ በከፍተኛ ግራ መጋባት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።
ከታማኝ የብአዴን ምንጮች የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ የአቶ መለስ የጤና ሁኔታ ለክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት እንኳ አልተገለጠም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ መለስ ከመጪው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በፊት ሥራ ይጀምራሉ ሲሉ አቶ በረከት ስምዖን ተናግረዋል ።
ቀደም ሲል በሰጧቸው መግለጫዎች  አቶ መለስ በቅርቡ ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ ከማለት አልፈው፤ የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ ያልፈለጉት  የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ሚኒስትሩ፤ለመጀመሪያ ጊዜ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የሥራ መመለሻ ጊዜ  ተናግረዋል።
የመንግስት ቃል አቀባዩ አቶ በረከት ስምዖን ይህን የተናገሩት፤ ጽህፈት ቤቱ በአውስትራሊያ ከሚገኘው ኤስ.ቢ.ኤስ ራዲዮ  ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህክምናቸውን ጨርሰው በአሁኑ ሰዓት በእረፍት ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ በረከት፤”በቅርቡ እረፍታቸውን በመጨረስ ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።
“በቅርቡ ሲሉ መቼ ማለትዎ ነው? ከመጪው የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ በፊት አገር ቤት ይገኛሉ?በየዓመቱስ እንደሚያደርጉት የመልካም አዲስ ዓመት መግለጫ ያስተላልፋሉ ብለው በእርግጠኝነት ሊነግሩን ይችላሉ?” በማለት  ከራዲዮው ለቀረበላቸው  ጥያቄ፦”እጅግ በጣም እርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ”ነው ያሉት አቶ በረከት።
“እንደውም ይህ ነገር ፤ ከአዲስ ዓመት በፊት ባለው ጊዜ ይሆናል”ሲሉም ተደምጠዋል።
ቢቢሲን ጨምሮ የተለያዩ ዓለማቀፍ ሚዲያዎች ፦”አቶ መለስ ወደ ሥራቸው መቼ ይመለሳሉ?” ብለው አቶ በረከትን  ከሳምንት በፊት ሲጠይቋቸው፦”ቀኑን በትክክል መናገር አይቻልም” ነበር ያሉት።
በዚህ ቃለምልልስ ግን አቶ መለስ ባለፉት ዓመታት ያስጀመሯቸውን ፕሮጀክቶች  ዳር  ለማድረስ በፍጥነት ወደ ሥራ ገበታ የመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው ያብራሩት ቃል አቀባዩ፤ ከአዲስ ዓመት በፊት  ወደ ቢሯቸው በመግባት  ሥራቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
አቶ መለስ ከአደባባይ ከጠፉ ወደ ሁለት ወራት እየተጠጋቸው ነው።
ከህዝባዊ ወያነ ሀርነት ትግራይ(ህወሀት) መስራቾች አንዱ የሆኑት እና በአሁኑ ጊዜ  የኢትዮጵያ ዓለማቀፍ የሰላምና የልማት ፕሬዚዳንት ተብለው በሟቹ ዶክተር ክንፈ አብርሀ ምትክ  የተመደቡት አቶ ስብሀት ነጋ፤ ቀደም ሲል ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ  የአማርኛው ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ፦አቶ መለስ ከአስር ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራቸው እንደሚመለሱ መናገራቸው ይታወሳል።
አቶ ስብሀት  ቃለ -ምልልሱን ከሰጡ  ሦስተኛ ሳምንታት  እየተቆጠሩ ቢሆንም፤አቶ መለስ ወደ ሥራቸው ሊመለሱ ቀርቶ በትክክል ስለሚገኙበት ሁኔታ እና ስላሉበት ቦታ ህዝቡ ግልጽና ተጨባጭ መረጃ  ሳያገኝ ቆይቷል።
ነገሩ በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ነው አቶ በረከት  ለኤስ ቢ ኤስ ራዲዮ፦ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመጪው አዲስ ዓመት በፊት ቢሯቸው ውስጥ ገብተው ሥራቸውን ማከናወን እንደሚጀምሩ የተናገሩት።
‘ጠቅላይ ሚኒስትሩ በብራሰልስ ሴንት ሉክ ሆስፒታል ተኝተው በነበሩበት ጊዜ ከጠየቋቸው የመንግስት ባለስልጣናት መካከል አንደኛው አቶ በረከት እንደነበሩም  በቃለ-ምልልሱ ተጠቁሟል።
“በሽታቸው ምን ዐይነት ነው? ቅለትና ክብደቱ እንዴት ነው? በዚህ ረገድ  ለአቶ መለስ ከሐኪማቸው የተነገረ እና እርስዎ የሚያውቁት ነገር ይኖራል?” በማለት ለቀረበላቸው ተከታይ ጥያቄ፦ በሰለጠነው ዓለም እንደሚደረገው ሁሉ ይህ ጉዳይ በሐኪሙ እና በታማሚው መካከል ብቻ ያለ ጉዳይ እንደሆነ አቶ በረከት ተናግረዋል።
“ጠቅላይ ሚኒስትሩ በደህና ሁኔታ ላይ የሚገኙ ከሆነ፤ እንደ መንግስት ቃል አቀባይነትዎ ምስላቸውን በፎቶ ወይም በቪዲዮ አስደግፎ ማሳየቱን ያልወደዱበት ምክንያት ምንድነው?ይህ ብልህ እርምጃ ነው ብለው ያስባሉ? ከዚህ ጋር በተያያዘስ ሥራዬን  በአግባቡ እየተወጣሁ ነው ብለው ያምናሉ? “የሚል ጥያቄም ከራዲዮው -ለአቶ በረከት ቀርቦላቸው ነበር።
ለጥያቄው፦“የኛ ሥራ የሚታወቅ ነው” በማለት ነው አቶ በረከት ምላሽ መስጠት የጀመሩት፦
አቶ በረከት በቃለ-ምልልሱ  መንግስታቸው በህዝብ ተዓማኒ እንደሆነ መግለፃቸው፤ ብዙዎችን ፈገግ አሰኝቷል።
መንግስትን አጠንክሮ በመተቸቱ  የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶበት በእስር ላይ የሚገኘው  ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ  ይሰራበት በነበረው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ፦” ውሸታሙ እረኛ” በሚል ርዕስ ባሰፈረው ጽሁፍ ፤  መንግስት መገለጫው ውሸት ከመሆኑ ብዛት ፤ህዝብ መንግስትን ማመን ያቆመበት ደረጃ ላይ እንደደረሰ መግለጹ ይታወሳል።
የግንቦት ሰባት ለፍትህ ለነፃነት እና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀ-መንበር የሆኑት ዶክተር ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው በአንድ ወቅት ስለ ኢህአዴግ እና ስለሚያስተዳድራቸው ሚዲያዎች ውሸት ከመጠን ማለፍ ሲናገሩ፦ኢህአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ የተወለደ ልጅ ፤በመንግስት ሚዲያዎች እውነት ሳይሰማ 20 ዓመት ሞላው ማለት ነው” ማለታቸው አይዘነጋም።
በዚህ ቃለ-ምልልስ ራዲዮው፤ -የአቶ መለስን የጤና መታወክ ተከትሎ ከተፈጠረው ውዥንብር ጋር በማያያዝ  አቶ በረከትን  -“ሥራዬን በአግባቡ እየተወጣሁ ነው ይላሉን?” በማለት የሰነዘረው ጥያቄ፤ ሚኒስትሩን ሳይቆረቁራቸው እንዳልቀረ ተገምቷል።
አቶ በረከት፦”ሰዎች እየጠበቁኝ ስለሆነ ከዚህ በላይ ላናግራችሁ አልችልም”በማለት  በስልክ የሰጡትን ይህን ቃለ-ምልልስ ያቆሙት፤ ከዚህ ጥያቄ በሁዋላ ነው።
አይጋ ፎረም የተሰኘው የኢህአዴግ ድረ-ገጽ በተመሳሳይ ከሳምንታት በፊት በለጠፈው ጽሁፍ ፦”ዓለም በአቶ መለስ ጤና ዙሪያ የተፈጠረበትን ብዥታ ለማጥራት የኮሙኒኬሽን ሚኒስቴርን መግለጫ  እየጠበቀ ባለበት ጊዜ፤ አንጋፋውና ልምድ ያካበቱት የህወሀቱ መስራች አቶ ስብሀት ሁሉንም ግልጽ አድርገውታል”በማለት አቶ በረከትንና የሚመሩት መስሪያ ቤት በመንቀራፈፍ መውቀሱ እና አቶ ስብሀትን ማወደሱ አይዘነጋም።
ሪፖርተር ጋዜጣ  በበኩሉ በቀጣዩ ቀን ማለትም  እ.አ፣አ በጁላይ 25-2012 ረቡዕ እትሙ፦“ሳሩን አየህ እና በሬውን ሳታይ እንዳይተረትብን  “በሚል ርዕስ ባወጣው ርዕሰ አንቀጽ ፦ በኢትዮጵያ በተለያዩ መስኮች  እየተፈጠሩ ላሉ ውዥንብሮች እና  ተቃውሞዎች፤ የኮሙኒኬሽን   ጽህፈት ቤትን አሠራር ተጠያቂ የሚያደርግ አቋም አንጸባርቋል።
በኢህአዴግና ደጋፊ ሚዲያዎች ላይ የአቶ መለስን መታመም ተከትሎ  አቶ በረከትን እና የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤትን ተጠያቂ የሚያደርጉ  ጥያቄዎችና ፅሁፎች በተከታታይ መንጸባረቃቸው፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩን መሰወር ተከትሎ በገዥው መንደር አለ የሚባለውን የ እርስ በርስ መሻኮት አመላካች ነው ይላሉ -ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ ያሉ ወገኖች። ምንም አቶ በረከት በሰጡት ቃለ-ምልልስ – “እኛ ኢህአዴጎችን የዚህ ዓይነት ነገር ሲያልፍ አይነካንም” ሲሉ ቢደመጡም።
ሌላው አነጋጋሪ ነገር  በርካታ የመንግስትና የድርጅት ሚዲያዎችን በስራቸው የሚያስተዳድሩት አቶ በረከት ይህን ቃለ-ምልልስ  እንዴት ለኤስ.ቢ.ኤስ ራዲዮ ለመስጠት ፈቃደኛ ሆኑ? የሚለው ጉዳይ ነው።
አንዳንዶች  ይህን ያደረጉት፤ ውጪአገር  በሚገኙ ሚዲያዎች መካከል ክፍፍል ለመፍጠር  ነው በማለት ይናገራሉ።
ኤስ.ቢ.ኤስ ቀደም ሲልም የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያምን  ቃለ-መጠይቅ ማድረጉ አይዘነጋም።
ከሁለት ወር በፊት በሬጋን ህንፃ በተደረገው የቡድን 20 አገሮች ስብሰባ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተቃውሞ ከሰነዘረባቸው በሁዋላ አቶ መለስ  በአደባባይ የታዩት በሜክሶኮ የተደረገውን ቀጣይ ስብሰባ ለመካፈል ወደዚያው ባቀኑበት  ጊዜ ሲሆን ፤ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ጋር ሲጨባበጡ በሚያሳየው በዚሁ ቪዲዮ ላይ ሰውነታቸው ከመጠን በላይ ቀንሶ መታየታቸው ይታወቃል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተከሰሰ

ነሀሴ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
Feteh Newspaper owned and editorTemesgen Desalegnኢሳት ዜና:-በማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ሥራ ድርጅት አማካይነት በየሳምንቱ ዓርብ ዕለት እየታተመ ለንባብ የሚበቃው የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝና ድርጅቱ ሶስት ክሶች ዛሬ ተመሰረቱባቸው፡፡
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ የወንጀል ችሎት ክስ የመሰረተባቸው በፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ እና በማስተዋል የህትመት እና ማስታወቂያ ስራ ድርጅት ላይ ነው።
አቃቤ ህግ በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የመሰረታቸው ሶስት ክሶች ማለትም  ወጣቶች በአገሪቱ መንግስትና ህገ መንግስታዊ ስርአቱ ላይ እንዲያምጹ የመገፋፋትና ግዙፍ የሆነ የማሰናዳት ተግባር፣  የሀገሪቱን መንግስት ስም ማጥፋት እና የሀሰት ውንጀላ እንዲሁም የሀሰት ወሬዎችን በማውራት ህዝብን በማነሳሳት ወይም አስተሳሰባቸውን ማናወጥ የሚሉ ናቸው።
የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳው በጋዜጣው የነሃሴ 23 ቀን ቅጽ 04 ቁጥር 149 እትም ላይ “ሞት የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ የአጼ ሃይለስላሴን ስርአት ወጣቶች እንዴት እንዳፈረሱት እና አሁን ያለው ስርአትም አፋኝ እና ጨቋኝ መሆኑን በመግለጽና አሁንም ሞት የማይፈሩ ወጣቶች መኖራቸውን ጠቅሶ በአረቡ አለም የተከሰቱ የህዝብ አመጾችን በሀገራችን እንዲተገበር በማሰብ ወጣቶች አደባባይ ለአመጽ እንዲወጡ በጽሁፍ ቀስቅሷል ይላል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ መከሰሱን የሰማው ከሬዲዮ ፋና መሆኑ ታውቋል።

Thursday 9 August 2012

ከፍተኛ የፖሊስ አዛዦች ሙስሊሙ ማህበረሰብ ህገመንግስቱን ለመናድ ከሞከረ ውጤቱ የከፋ ይሆናል ሲሉ አስጠነቀቁ

ነሀሴ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጀመሩት ተቃውሞ አንድ አመት ሊመላው ጥቂት ወራቶች ብቻ በቀሩበት በዚህ ጊዜ፣ የፖሊስ አዛዦች ተቃውሞው የሚቀጥል ከሆነ የከፋ ጉዳት ይከተላል ብለዋል።
የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የፖሊስ ፕሮግራም ላይ ቀርበው እንደተናገሩት  ፣  ሙስሊሞች ፍላጎታቸውን በሀይል ለመጫን የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ርብርብ የማይቆም ከሆነ ውጤቱ የከፋ ይሆናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በፌደራል ፖሊስ በጸጥታ እና ህግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት የኦፕሬሽን ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት ኮማንደር ፍጹም ግርማይ በበኩላቸው በህገ መንግስቱ ላይ የሚመጣውን ማንኛውንም ነገር ለመከላከል መስዋት ለመክፈል ዝግጁ ነን ብለዋል::
መንግስት የሙስሊም እንቅስቃሴ መሪዎችን በማሰር ውዝግቡ ሊበርድ ይችላል ብሎ ተስፋ ቢያደርግም፣ ሙስሊሞች ግን መሪዎቻችን ይፈቱ የሚል ተጨማሪ ጥያቄ በማቅረብ  ትግላቸውን ከመቀጠል ውጭ ወደ ሁዋላ ለመመለስ ዝግጁ አለመሆናቸውን ኢሳት ያነጋገራቸው ሙስሊሞች መግለጻቸው ይታወሳለ።
በፖሊስ የቀረበው ማስጠንቀቂያ የሙስሊሙ እንቅስቃሴ መንግስትን በእጅጉ እያሰጋው መምጣቱን እንደሚያሳይ አስተያየታቸውን የሰጡን አንድ ሙስሊም ገልጠዋል።
ሙስሊሙ የጠየቀው ጥያቄ ህገመንግስቱ ይከበርልን የሚል ሆኖ እያለ ፣ የፖሊስ አዛዞች ህገመንግስቱን ለማስከበር አስፈላጊውን እርምጃ እንወስዳለን ብለው መዛታቸው በመንግስትና በሙስሊሙ መካከል ያለው ውዝግብ በቀላሉ ሊበርድ እንደማይችል አመላካች ነው በማለት አስተያየት ሰጪው ተናግረዋል።
ከ500 ሺ በላይ የሚሆኑ ሙስሊሞች ባለፈው አርብ ነጭ ጨርቅ በመያዝ ተቃውዋቸውን ገልጸው እንደነበር ይታወሳል፡፤ የፊታችን አርብም ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሎአል።

በአማራ ክልል ባለስልጣናት በሕዝብ ታገቱ

ነሀሴ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአማራ ክልል ባለስልጣናት በሕዝብ ታገቱ በእገታው ተሳትፈዋል የተባሉ 12 ወጣቶች በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ታሰሩ በአማራ ክልል የክልሉ ባለስልጣናትን ጨምሮ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪዎች፣ የሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ባለስልጣናትና ሌሎች የክብር እንግዶች ተሰርቶ ያልተጠናቀቀ መንገድ ተረክበዋል በማለት በአካባቢው ነዋሪዎች መታገታቸውን ሰንደቅ ዘገበ።
እገታውም በድርድርና ውይይት ከተፈታ በኋላ መንገድ ዘግተዋል የተባሉ 12 ወጣቶች በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው ታስረዋል።
እንደ ጋዜጣው ዘገባ፤በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ከድልብ እስከ ሙጃ ከተማ በ150 ሚሊዮን ብር የሚሰራው 27 ኪ.ሜ የገጠር ጠጠር መንገድ ኤም ኬ ኤች በተባለ ተቋራጭ በሶስት አመት ውስጥ ሰርቶ ለማጠናቀቅ ቃል ገብቶ ነበር።
ነገር ግን የመንገዱ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ሳይጠናቀቅ የክልሉ ባለስልጣናት በተገኙበት ሐምሌ 15 ቀን 2004 ዓ.ም የመንገድ ርክክብ መፈፀሙ ከአካባቢዋ ነዋሪዎች ተቃውሞ ተነስቷል።

The secret government of Ethiopia

Wednesday, August 8, 2012 @ 08:08 AM ed
By Amanuel Biedemariam
On its 28th of July report Ethiopian Satellite Television (ESAT) described the impact of the absence of Meles Zenawi and his leadership. Contrary to what Sebhat Nega and Bereket Simon portrayed, ESAT reported those middle management are in suspense all over. The poorly explained absence of Meles has created deep tension that could tear the country apart. Rumors are abundant about emergency meetings. Lack of information has made high-ranking bureaucrats nervous and unable to run the daily affairs of the nation. According to the report, these groups are in a panic mode desperately seeking to get their families and dollars out thus creating a vacuum.
The absence of Meles is one obvious dilemma and a minefield the junta is trying to figure out how to address carefully. For the author the question is not what Meles’s crime partners are doing. The criminals will do all they can to retain the status-quo. According to Sibhat Nega, the junta runs the country in accordance to their standard practices that is, even if a leader goes down, they have a method in place that enables them to run the nations affairs uninterrupted. Hence, Sibhat inadvertently admitted that the junta runs Ethiopia in disregard to the wishes of the public hence minimized the absence of Meles. Therefore, it is more important to focus on what this criminal junta is trying to attain, which is the continuation of the defunct regime, rather than the life or death of the criminal Meles.

Ethiopians contemplate a nation without Prime Minister Meles Zenawi


But at this moment it seems the entire city is holding its breath. Prime Minister Meles Zenawi, the rebel-turned-technocrat who has led Ethiopia since 1991, is sick. And his long absence from public view has given Ethiopians cause to contemplate what their nation — now enjoying one of the longest sustained periods of economic development in its history — might look like without him.

ADDIS ABABA, Ethiopia — When the summer rains come, as they have in cleansing torrents over recent weeks, the 3 million residents of Ethiopia’s smog-choked capital usually inhale a little more deeply and exhale a little more freely.
Muslim women who say a national ban on full-face veils is a violation of their rights refuse to obey law.

Ethiopian prime minister Meles Zenawi not seen for seven weeks Addis Ababa mute on whereabouts of PM – latest African leader believed to be unwell but subject of information blackout

Ethiopian Prime Minister Zenawi health concernsHe hasn't been seen in public since the G8 summit in Mexico, and since then Ethiopia's prime minister, Meles Zenawi, has even missed the African Union summit held in his own capital city, Addis Ababa.
Zenawi, 57, usually a conspicuous figure at meetings of African and international heads of state, has now been missing for more than seven weeks, amid growing incredulity.
Government sources in the secretive African nation say that Meles – who was seen looking frail before his disappearance – is resting but well, but more than one eyebrow has been raised at the reasons for his absence. "The Prime Minister is on vacation recovering from illness," an Ethiopian government source told the Guardian. "There has been a lot of ill-meant speculation about his health."

Meles Zenawi: Ethiopia's pragmatic philosopher-king or cruel despot?

Meles Zenawi, Ethiopian prime ministerMeles Zenawi, the cerebral ruler of Ethiopia for the last 21 years, is a man with many reputations. Celebrated by donors as a visionary philosopher-king who has brought development to his impoverished country of 75 million people, his domestic critics have condemned him as an iron-fisted dictator.
Meles, now 57, came to power in 1991 after his Tigray People's Liberation Front waged a successful 30-year war, alongside the Eritrean People's Liberation Front, that toppled the dictatorship of the Soviet-backed Mengistu Haile Mariam.
The new leader strongly supported Eritrea's independence in 1993, but within five years the former allies were fighting a bloody conflict that lasted between 1998 and 2000 and resulted in nearly 100,000 deaths.
Matters were not all peaceful at home either. In 2005, when the opposition won 23 seats in parliamentary elections, the regime reacted harshly, killing 200 protestors and locking up 30,000 opponents. Some were later tried for treason.

Wednesday 8 August 2012

Ethiopia: Addis Ababa is holding its breath

Mesay and Sisay analyse Meles Zenawi's G20 presence and his physical appearance.ADDIS ABABA, Ethiopia — When the summer rains come, as they have in cleansing torrents over recent weeks, the 3 million residents of Ethiopia’s smog-choked capital usually inhale a little more deeply and exhale a little more freely.
But at this moment it seems the entire city is holding its breath. Prime Minister Meles Zenawi, the rebel-turned-technocrat who has led Ethiopia since 1991, is sick. And his long absence from public view has given Ethiopians cause to contemplate what their nation — now enjoying one of the longest sustained periods of economic development in its history — might look like without him.
“We are worried,” said Makeda Taye, who will enter college in Addis Ababa this fall having known life under no other leader. “This country has grown stronger and it’s not certain — did it grow this way because of Meles or in spite of him? In absence of knowing one way or the other, we prefer things the way they are.”
The U.S. government has long viewed Meles as a stable partner in a region peppered with despots and religious extremists. The United States has given Ethi­o­pia, which serves as an ally in the fight against terrorism and hosts a base for U.S. drones, hundreds of millions of dollars in aid over the years.

ለውይይት የተጠሩት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ፍርድ ቤት ቀረቡ


Unity for Democracy and Justice Party በፌደራሉ ከፍተኛ /ቤት ልደታ ምድብ 3 ወንጀል ችሎት ውሳኔ ተስጥቶበት በተዘጋው በነ አንዱዓለም አራጌ የክስ መዝገብ ቁጥር 112546 “ተከሳሽዓቃቤ ህግ በሚል ደብዳቤ ለውይይት ተብሎ ፍርድ ቤት የተጠራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፤ ተወካይ ከፍተኛ አመራሮች የተከበሩ / ነጋሶ ጊዳዳ፣የተከበሩአቶ ግርማ ሰይፉ እና አቶ አስራት ጣሴ ትናንት ሰኞ ሐምሌ 30 ቀን 2004.. ከሰዓት በኋላ በድንገት ችሎት ፊት እንዲቀርቡ ተደረገ፡፡



አንድነት በእነ አንዱዓለም አራጌ ላይ የተሰጠውን የፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ በተቃውሞ መግለጫ መስጠቱ በፓርቲው ፍርድ ቤቱ ላይ እና የፍትህ ስርዓቱ ላይ የተቃጣ ከፍተኛ ጥፋት ነው በማለት በስፋት ካተተ በኋላ ፓርቲው በአገሪቱ ለመድበለ ፓርቲ ግንባታ የሚያደርገውን ከፍተኛ አሰተዋፅዖ ከግምት ውስጥ በማስገባት በተግሳፅ እንዲታለፍ መወሰኑን የግራ ዳኛው ሁሴን ይመር በንባብ አሰምተዋል፡፡

አምባሳደር ስዩም መስፍን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቦታ ተክተው እየሰሩ መሆኑ ተጠቆመ


የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በገጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት 45 ቀናት በላይ በመደበኛ ስራቸው ላይ ባለመሆናቸው በኢህአዴግ አመራሮች መካከል በስልጣን ሽኩቻ እንደተፈጠረና አቶ ስዩም መስፍን የአቶ መለስን ቦታ ተክተው በመስራት ላይ እንደሚገኙ የፍኖተ ነፃነት ታማኝ ምንጮች ጠቆሙ፡፡



የፍኖተ ነፃነት ታማኝ ምንጮች እንደገለፁት የቻይና ዲፕሎማቶች ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረጉት ድርድር የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ስዩም መስፍን ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ጋር በመምጣት ቤተመንግስት ሆነው የመሪነቱን ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የዝግጅት ክፍላችን ይህንን ለማጣራት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች /ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ በረከት ስምዖን ጋር ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ቢያደርግም ስልካቸው ባለመነሳቱ ሐሳባቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡

ጋዜጠኛዋ በምሽት በደህንነቶች ተጠለፈች

ነሀሴ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን በሽብርተኝነት ለመክሰስ የወሰነው የኢህአዴግ መንግስት፤ አንዲት ጋዜጠኛን በምሽት  በደህንነቶች በማስጠለፍ  በተመስገን ላይ በሀሰት እንድትመሰክር  ትዕዛዝ እና ማስፈራሪያ መስጠቱን የማዕከላዊ ምንጮቻችን አጋለጡ።
ምንጮቻችን እንዳሉት፤  በአንድ ሳምንታዊ የአማርኛ ጋዜጣ የምትሠራ ጋዜጠኛ  ባለፈው ሐሙስ ምሽት ከቢሮዋ ወጥታ በኮንትራት ታክሲ ወደ ቤቷ በምታመራበት ወቅት  የደህንነት ሀይሎች ታክሲዋን አግተው በመጥለፍ ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ይወስዷታል።
ደህንነቶቹ ጋዜጠኛዋን ወደ ወንጀል ምርመራ ክፍል በማስገባት፦”ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ያለሽን ግንኙነት ደርሰንበታል። ሀጎስ ኪዳኔ የተባለና  ከአልሸባብ ጋር አብሮ የሚሠራ የሻዕቢያ ሰው ከ አልሸባብ በአንቺ በኩል ለተመስገን በርካታ ብር እንደተላከለት ስለመሰከረ እና ይህንንም ተመስገን ስላመነ፤ አንቺም ፍርድ ቤት ቀርበሽ ይህንኑ እንድትመሰክሪ እንጠይቅሻለን” ብለዋታል።
ደህንነቶቹ በማያያዝም፦ ጋዜጠኛዋ ፍርድ ቤት ቀርባ የተባለችውን የማትመሰክር ከሆነ፤እርሷም አብራ ከተመስገን ጋር  እንደምትከሰስ አስፈራርተዋታል።

Tuesday 7 August 2012

Ethiopia: Has Meles Zenawi Gone AWOL?

by Alemayehu G. Mariam
An AWOL “Prime Minister”?
Ethiopian Dictator Meles Zenawi has disappeared from public view for several weeks now.What happens when a “prime minister” goes AWOL? That is, absent without constitutional leave of absence.  Ethiopian Dictator Meles Zenawi has disappeared from public view for several weeks now. He was last seen in public on June 19 at the G20 Summit in Mexico. His disappearing act has provided more grist for speculation and caused pained and grimaced official obfuscation. On July 19, in a rambling, disjointed and incoherent press statement, Zenawi’s spinmesiter and “communication minister”, Bereket Simon, stonewalled any information on Zenawi’s health and whereabouts by offering a cryptic and manifestly dubious explanation on July 19. Simon said Zenawi was receiving medical care for some undisclosed minor health problem at some undisclosed location. The cause of Zenawi’s health problem is alleged to be exhaustion resulting from long public service. Simon’s statement strangely suggested that Zenawi was simultaneously at a medical facility and a Club Med-type vacation spot. Simon assured the public that Zenawi will return to his duties shortly. “Deputy prime minister” Hailemariam Desalegn chimed in with the inane observation that “There is no serious illness at all. It’s minor only. As any human being, he has to get medication and he’ll be coming back soon.” Of course, the overwhelming majority of Ethiopian human beings get no medication whatsoever when they face “serious illness”. Anyway, what exactly is Zenawi’s “not serious illness”? What kind of medication is Zenawi getting? How soon is soon for Zenawi to return to office? Just to keep things in perspective, on July 18 an Agence France Press report citing “several diplomatic sources” reported  that Zenawi “is in a critical state” at a hospital in Belgium and that “his life is in danger” and “might not survive”.

በኢትዮጵያ ከፍተኛ የዶላር እጥረት ተከሰተ

ሐምሌ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም -
ኢሳት ዜና:-የውጭ ባለሀብቶች የውጭ አገር የንግድ ስራዎችን ለመስራት ኤልሲ ( ሌተር ኦፍ ክሬዲት) ለመክፈት በሚሄዱበት ጊዜም ይሁን ሌሎች ለትምህርት ወይም ለህክምና ወደ ውጭ አገር ለመሄድ የሚፈልጉ ሰዎች ዶላር ለመግዛት ወደ ባንኮች ሲሄዱ፣ ዶላር የለም በሚል እንደሚመለሱ ታውቋል።
አቶ መለስ ከ6 ወራት በፊትበቂ የሆነ የዶላር ክምችት መኖሩን ተናግረው የነበረ ሲሆን፣ አሁን የታየውን የዶላር እጥረት ምን እንደፈጠረው አልታወቀም። ይሁን እንጅ ብዙዎች እንደሚገምቱት አንዳንድ ባለሀብቶች ከአቶ መለስ ዜናዊ ጤና ጋር ተያይዞ ተቀማጭ ገንዘባቸውን ወደ ዶላር በመቀየር ማሸሽ መጀመራቸው ምናልባትም ችግሩን አባብሶት ሊሆን ይችላል።
ብሄራዊ ባንክ ባለሀብቶች ሊተር ኦፍ ክሬዲት እንዳይከፍቱ እገዳ መጣሉም ተሰምቷል።
ዶላር መልሶ ከገበያ መጥፋቱ ባለፉት 3 ወራት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቶ የነበረውን የገንዘብ ግሽበት ወደ ነበረበት ደረጃ እንዳይመልሰው ተሰግቷል።
ኢሳት ባለፈው ሳምንት በአገሪቱ የሚታየው የንግድ እንቅስቃሴ መዳከሙን፣ በገጠር አካባቢዎች ኢንቨስት ያደረጉ ባለሀብቶች ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸውን፣ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ የውጭ አገር ባለሀብቶችና ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ ከመሄዳቸው በፊት መረጃዎችን ማጣራት መጀመራቸውን መዘገቡ ይታወሳል።
ኢትዮጵያ አብዛኛውን የውጭ ምንዛሬዋን በውጭ አገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ከውጭ እርዳታ እንደምታገኝ ይታወቃል።

Economic corruption in Ethiopia must take front burner to bring down the Woyane regime faster

Given Woyane’s stranglehold on the economy through its network of criminal enterprises and its official corruption it is important to bring down the rotten system sooner than later. It is the responsibility of all concerned to organize properly to take immediate action on the Merchants-of-Death.
by Teshome Debalke
Economic corruption in Ethiopia must take front burner to bring down the Woyane regime fasterEthiopians are taken for a ride by an atrocious ethnic tyranny on the top of notorious criminal syndicate called Woyane. The ruling regime in Addis Ababa and its corrupt partners in crime in-and-around the world are having it easy; robbing the nation blind while distracting the public with all kinds of diversions. The politically bankrupt ethnic regime hopes to hang on power by-all-means on its disposal to continue its robbery going.
The moving target regime managed to elude the world for too long. Its newfound love with ‘economic transformation’ is noting more than another diversion to legitimize its modern day robbery under institution of larceny it setup to help it. The regime and its partner-in-crime genuinely believe they outsmart everyone in ransacking the nation with impunity.
The regime’s apologists are simply bottom feeders enjoying their pretty corruption granted them for their service. Equipped with well orchestrated propaganda they created enough confusion to allow the regime get away with its heist while protect their ill-gotten petty theft as willing participants. In reality, the economy driven by top-down vertically integrated criminal enterprises run by TPLF operatives. Congregated around the usual economic activities with all the ‘legal’ cover they can master the operatives channel illicit goods and launder ill-gotten money at will.

Where in the World is Meles Zenawi? (And Why it Doesn’t Matter…)

by Mitmita Girls
Where in the World is Meles Zenawi?Like much of the world, including organizations such as the Committee to Protect Journalists, the Mitmita Girls have been spending the past couple of weeks wondering where oh where is our esteemed Prime Minister? Could he be at a Belgian hospital? Is he at a resort somewhere in the islands? Is he emptying out his Swiss Bank accounts? Did he “go long on the euro” and is now regretting it in hiding? Could he be seeking a much needed spiritual guidance at an ashram—constantly thinking of ways to torture your opponents IS mentally exhausting! Is he going to stun us by joining the first ever Ethiopian Men’s Synchronized Swimming Olympic Team? Perhaps he ran away with the circus! Anything is possible!
Meles might be pulling off the greatest disappearance act since Houdini but it has the Mitmita Girls wondering if this is all just subterfuge. Is this melodrama a way to distract us from what is already happening in Ethiopia and whatever other delightful surprises the ruling regime has coming our way?

The Free Ethiopian Armed Forces movement

Press Release
The Free Ethiopian Armed Forces movement
For peace, justice, unity and democracy
The role of the Ethiopian Armed Forces has historically been to:
  • Defend the territorial integrity of the country
  • Protect the unity of its people
  • Act as the vanguard of freedom and defend the constitution
The Free Ethiopian Armed Forces movement for peace, justice, unity and democracyThe members of the Armed Forces have left us a legacy of unconditional commitment and loyalty to the needs and demands of our people in the protection and maintenance of peace, unity and territorial integrity of our beloved country as well as the advancement of its people for a better life.
The current members of the Armed Forces, like their predecessors have declared their allegiance to these principles and unconditionally  prepared themselves to sacrifice their lives for this cause despite repeated attempts by the ruling party to reduce the Ethiopian Defense forces to simply as an  instrument  of the regime in its attempt to retain its illegitimate power. But after 20 years of rule by a minority ethno centric government and a policy of brutal repression of the freedom of our people and realizing the extent to which it is willing to go in order to perpetuate these structures and policies in the interest  of the few, and at the expense of the core interest of the country and its people, a significant number of concerned  members of the Armed Forces  have decided to align themselves with the forces of peace, equality, justice, democracy and unity in our country.

ብታምኑም ባታምኑም፤ ፌስ ቡክን በመጠቀማቸው ሰራተኞች ሃርድ እየተሰጣቸው ከስራም እየተባረሩ ነው!.....ከአቤ ቶክቻው

ከዚህ በፊት በፌስ ቡክ የመልዕክት ሳጥኔ ውስጥ አንድ ወዳጄ አላባ አካባቢ ወደ ሶስት የሚጠጉ የመንግስት ሰራተኞች በፌስ ቡክ ላይ ፖለቲካ ነክ ፅሁፍ ለጥፋችኋል ተብለው ከስራ መባረራቸውን ነገሮኝ ነበር። እኔ ግን ይሄንን ነገር ከራሳቸው ከተባራሪዎቹ ሰዎች ካልሰማው በስተቀር የመንግስቴን ስም “በከንቱ” አላጎድፍም ብዬ ስልካቸውን እንዲልክልኝ ጠየኩት። (እንዴት ያለሁ ልማታዊ ወገኛ እንደሆንኩ ብቻ ግራ ቀኝ ልብ አድርጉልኝ!) ልጁ ግን ስልካቸውን ፈልጌ ልክልሃለሁ ብሎኝ ሳይልክልኝ ቀረ።  እኔም ያንን ወሬ አላወራም ብዬ ፀጥ አልኩ።
ነገር ግን በሌላም ግዜ በተደጋጋሚ የተለያዩ ወደጆቼ  “በፌስ ቡክ ግድግዳችሁ ላይ ፖለቲካ ፖልትካችኋል” እየተባሉ ከአለቆቻቸው ዘንድ ግሳፄ እየተሰጣቸው መሆኑን   ስሰማ ይሄ ነገር  ሁሉም ዘንድ ነው ማለት ነው… ብዬ በማንሰላሰል ላይ ሳለለሁ፤
አንዱ ወዳጄ  ደግሞ ከምስራቅ የኢትዮጵያችን ክፍል ከአንዱ ወረዳ ሌላ መልዕክት ሰደደልኝ።
ይህ ወዳጃችን በወረዳው ውስጥ በአንዱ የመንግስት መስሪያ ቤት “ICT” ኤክስፐርት የስራ መደብ ላይ ተቀጥሮ ይሰራ ነበር። በመስሪያ ቤቱ የሚገኙ በርካታ ወዳጆችን ወደ ፌስ ቡክ ሰፈር እንዲቀላቀሉ አድርጓል። ራሱም አዘውትሮ ፌስ ቡኩን ይጠቀማል።

Supporting Stability, Abetting Repression


BERKELEY, CALIFORNIA — Next time I travel to Ethiopia, I may be arrested as a terrorist. Why? Because I have published articles about Ethiopian politics.


I wrote a policy report on Ethiopia’s difficulties with federalism. I gave a talk in which I questioned Ethiopia’s May 2010 elections, in which the ruling EPRDF party (Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front) won 545 out of 547 seats in the Parliament. As part of my ongoing research on mass violence in the Somali territories, I interviewed members of the Ogaden National Liberation Front, a separatist rebel group in eastern Ethiopia that the government has designated as a terrorist organization.
In the eyes of the government of Prime Minister Meles Zenawi, my work is tantamount to subversion. Not only do his officials have zero tolerance for criticism, they consider people who either talk to or write about the opposition as abetting terrorists.

“እስላም ክርስቲያኑ ባንድ ሆነ ፆማቸው… ከአምላክ ለመድረስ ቀጠሮ እንዳላቸው” ማን ያውቃል! | አቤ ቶኪቻው


አመጣጤ ክርስቲያን ወዳጆቼን አንኳን ለፆመ ፍልሰታ አደረሳችሁ ለማለት እና ሙስሊም ወዳጆቼን ደግሞ የተጀመረው “ዱዓ” ይቀጥልልን ብሎ ለማበከር ቢሆንም “በልጅ አመካኝቶ ይበላል እንኩቶ” እንዲል እንኮቶ ያማረው አባት… እግረ መንገዴን ከመጣሁ አይቀር ኮስተር ብዬ የማነሳው አንድ ጉዳይ አለኝ።

ትላንት አንድ መረጃ ለጥፌ ነበር። መረጃው “በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በህቡዕ የሚንቀሳቀስ” አንድ ንቅናቄ ያወጣው መግለጫ ነበር። ይህ መግለጫ “የሰራዊቱ አባላት ከዚህ በኋላ ህዝብ ላይ አንተኩስም እስከ መቼ ለአምባገነን መሪዎች አግዘን፤ እኛ መሳሪያ ታጥቀን ቀበቶ እና መቀነት ብቻ የታጠቀውን ህዝብ እንደበድባለን!? ይሄ ነገር ነውር መሆኑን አየን ከዚህ በኋላ እንዲህ አይነት ነገር ላለመፈፀም ዝግጅታችንን አጠናቀናል” የሚል ነበር።

የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንቅስቃሴ በወያኔና አላሙዲ ላይ እያደረሰ ያለው ክስረት

የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል


ከሃገራቸው ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው የህዝብን ብሶት እንዳያሰሙና ወያኔን በማስወገድ ትግል በቀጥታ እንዳይሳተፉ ለማድረግ አገዛዙ የማይሸርበው ተንኮል የለም። የወያኔ ህልውና መሰረት በማንኛውም መንገድ ህዝቡንና ተቃዋሚውን መከፋፈል በመሆኑ እስትንፋሱ እስካለ ድረስ ስልቱን በመቀያየር መሞከሩ አይቀርም።
በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባህል ፌደሬሽን አመራርን በመያዝ ተልእኮውን ለማስለወጥ ያደደረገው ጥረት በህዝብ ወገኖች ትግል መክሸፉ ይታወቃል። ከዚያም 29ኛውን የአንጋፋው ስፖርት ፌደሬሽን የዳላስ ዝግጅት ለማሰናከልና የህዝብ ወገኖችን ለመነጣጠል AESA ONE የሚባል ምንደኛ ቡድን በሼህ አላሙዲን ገንዘብ በመመስረት፤ በዋሽንግተን ዲሲ “ፌስቲቫል አዘጋጅቻለሁ” ብሎ ነበር። ይህ በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ የተረጨበት የሆድአደሮች ዝግጅት ግን በኢትዮጵያውያን አገር ወዳዶች ጠንካራ ተቃውሞና እቀባ ብኩን ሆኖ ቀርቷል። ይህ ታሪካዊ ድርጊት ወያኔንና አጋፋሪዎቹን የውርደት ማቅ ከማልበሱ በተጨማሪ፤ ግልፅ በሆነ የተግባር አላማ ስር በአንድነት ለተሰለፈ ወገን ያሰበውን ለማሳካት የሚያግደው ሃይል አለመኖሩን አሳይቷል።

Sunday 5 August 2012

Political and Economic Forces: Living with Disagreement [In the Event of the Death or Disability of Meles Zenawi] By Tecola W. Hagos

“There were some bandas who spread rumors that the Emperor had fled the country. A Patriot would never say that.”
Grazmach Hagos Hailu

I. Introduction
Now that we are hearing from BBC News that Prime Minister Meles Zenawi is alive and recovering from undisclosed illness, I am particularly incensed that I have to learn about the health condition of an Ethiopian leader from foreign sources. I find the silence of the officials of the Ethiopian Government, under the present situation of the public absence of Meles Zenawi from view, irresponsible and utterly callous and disrespectful of the Ethiopian People. As Ethiopians we have every right to know where Meles Zenawi is being taken care of, if such is the case. What is his current situation? Is he dead or alive? What preparation of transfer of power is being arranged? Is there some kind of accommodation being implemented to invite the opposition groups/parties that are located in Ethiopia to participate in the transition? No matter how this crisis of the condition of Meles Zenawi is resolved, we are in a different phase from now on ward.