Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 15 December 2012

Isaias Afeworki Asks Qatar To Mediate Dispute With Ethiopia


Eritrean Strongman Asks Qatar To Mediate Dispute With Ethiopia


(Awate.com) – Eritrean president Isaias Afwerki has asked Qatar to mediate his long-standing feud with “arch-rival” Ethiopia. This message was communicated to the new Ethiopian Prime Minister, Hailemariam Desalgn, by Qatar, while the Ethiopian prime minister was conducting a state visit. Isaias Afwerki has offered to attend mediation talks without any pre-conditions.
Isaias Afeworki

In an interview with Al Jazeera, Hailemariam Desalegn told his interviewer that he would be willing to travel to Eritrea to hold face-to-face talks with Isaias Afwerki and that this was a long-standing Ethiopian policy: “My predecessor Meles Zenawi had asked for more than 50 times even to go to Asmara and negotiate with Mister Isaias Afwerki,” he said.

Qatar, which is showing greater interest in the region, is weary of the growing Turkish influence in the Horn of Africa. Recently, the Turkish foreign minister visited Asmara at the invitation of Isaias Afwerki, who wanted him to mediate between the new Somali regime and the Eritrean regime. But while in Asmara, Isaias also informed the Turkish foreign minister that he is working to normalize relations with Ethiopia and that he had asked Qatar to mediate.

ባዶ ሥልጣን ይዞ ውሸት ለመሳቂያነት

ዳኛቸው ቢያድግልኝ
ፈጽሞ ለማጅ የማያሰኝ ዋሾነት በአቶ ኃይለማርያም ሲተወን አልጀዚራ ላይ ተመልክተናል። እርግጥ ነው እንደ ‘ባለ ራዕዩ’ ጮሌነትና አራዳዊ መገለባበጥ ቢያንሰውም ለመዋሸት ግንባራቸውን እንደማያጥፉ ግን አረጋግጠውልናል። አቶ ኃይለማርያም ምናልባት እየተቆጡ ሲዋሹ፣ እያስፈራሩ ሲቀጥፉ ስለኖሩ እንጂ እንደዚህ በአንድ ጊዜ የላቀ የዋሾነት ሜዳልያ የሚያሰጥ አቅም ሊኖራቸው ባልቻለ ነበር። ብዙ ሰባኪዎችን የተመለከቱ ግን አይመስለኝም። ቢሆን ኖሮ ቴክኒክ ተውሰው ትንሽ እውነት እያስደገፉ ግዙፍ ውሸት በመዋሸት ማደናቆር በቻሉ ነበር እንደ ታምራት ላይኔ። ግን ይዋሻሉ፣ አረ የምን ሰው ምን ይለኛል ነው፣ እግዜር ምን ይለኛልም አይሉም እኮ። አቤት መለስ እንዴት አድርጎ ጠፍጥፎ ሰራቸው እባካችሁ? ግን አላማረባቸውም ምክንያቱም ባዶስልጣን ይዞ ውሸት መሳቂያነት መሆኑን ሊያውቁ በተገባ ነበርና። ለዚህም ነው አስፎጋሪ ውሸት የዋሹት። ስለመሬት ነጠቃው ቀባጠሩ፣ ስለ ታሰሩት ወገኖችም ዋሹ። አዎ ኳስ ጨዋታዋ ላይም ሳቱ። ለመታጠፍ ደግሞ ዘገዩ ኳሱን ተዉትና መለስ እኮ ሃምሳ ጊዜ ኤርትራ እሄዳለሁ ብሎ ነበር አሉና መታጠፍ ጀመሩ። እናቴ ትሙት እጅሽን ልምታ እያለ የሚማጸን ልጅ መሰሉ። አባቱን ድረስልኝ የሚል ልጅ ይመስል ሮጠው መለስ መለስ ሲሉ ያሳዝናሉ። ጋዜጠኛይቱ በሆድዋ ምስኪን የምትል ይመስል ነበር።

ምላስ አጥንት ቢኖረው ታድያ ቀጨ..ጨ..ጨ ሲል በሰማነው ነበር ሲዋሹ። አቤት ባለቤታቸው እንዴት ይሳቀቁ ይሆን? እሳቸውም ከአንድ ውሀ ካልተቀዱ እና ቀዳማይቱን መምሰል ካልፈለጉ ተሳቅቀው ማለቃቸው ነው። ውይ …. የሰው ዐይንስ እንዴት አያለሁ ይሉ ነበር። ደግነቱ ቤተመንግሥት ነው ያሉት ማየትም መስማትም ከማይችሉበት ድብቅ ስፍራ ብለን እንለፈውና ነጥቦቹን እንመልከት። አለዚያማ መጻፋችንስ ምን ዋጋ አለው። ክቡርነትዎ ግን ድንገት ተፈቅዶልዎ ይህንን ካነበቡ የፕሮፌሰር አልማርያምን ምክር አይርሱ። አለም እንደትስቅሎት እየሳቁ ይዋሹ እንጂ አለም እንዲስቅቦት እየሟሸሹ አይዋሹ ቂ..ቂ….ቂ……

የአስመራ ጉዳይ ላይ የሰጡት አስተያየት ትንሽ ብልጠት ነበረው ምክንያቱም በመጨረሻ የኤርትራ ክሊክ አሸናፊ ሆኖ ኢትዮጵያን ለመጠቅለል መውጣቱን ልብ በማለታቸው ሊሆን ይችላል ብሎ መጠርጠር አስፈላጊ ነው። አለበለዚያም የሳቸው ‘ኤክሰለንሲ’ ያደርጉ እንደነበረው መተጣጠፍ ፈልገው ነበር። ይሁን እንጂ እንኳን በሀገር ጉዳይ ሊወያዩ ስለ ኳስ ጨዋታ እንኳን ያለማወቃቸው አሳፋሪና ከታማኝ ተላላኪም በታች ያደርጋቸዋል። አቶ ኃይለማርያም እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ መቶ አለቃ ግርማ ሲሆኑ ያሳዝናሉ። እንደዚህ መሳቂያ እናደርግሀለን አርፈህ እንደ እሱ ቁጭ በል የሚሏቸው ይመስላል። ግን እንዲያው ምን አለበት ባያዋርዱዋቸው እሳቸውም እንዲህ ባይወርዱ።

Friday 14 December 2012

Susan Rice withdraws as candidate for secretary of state

By Karen DeYoung and Anne Gearan
(The Washington Post) – U.N. Ambassador Susan E. Rice withdrew her name Thursday as President Obama’s leading candidate for secretary of state, saying the administration could not afford a “lengthy, disruptive and costly” confirmation fight over statements she made about the extremist attack in Libya that killed four Americans.
Rice called Obama on Thursday morning, before sending him a letter officially withdrawing from consideration. Rice said in an interview that she had concluded early this week that what she and Obama considered “unfair and misleading” charges against her over the Sept. 11 attack in Benghazi, Libya, would impede the president’s second-term agenda.
Susan Rice and Hillary Clinton

“This was my decision,” Rice said. When asked if Obama had tried to dissuade her, she said that he “understood that this was the right decision, and that I made it for the right reasons.”
Her withdrawal leaves Senate Foreign Relations Committee Chairman John F. Kerry (D-Mass.) with no apparent competitors to take over from Secretary of State Hillary Rodham Clinton. A senior administration official said that “something strange would have to happen” for Kerry not to be the choice.
The official also said that former senator Chuck Hagel (R-Neb.) has emerged as a “solid” candidate to run the Pentagon, although a final decision has not been made. For the CIA, the official said, Obama is deciding between Acting Director Michael J. Morell and deputy national security adviser John O. Brennan, who has yet to tell the president whether he would accept the job.
As Obama assembles his second-term national security team, formal announcements are due as early as next week. National security adviser Thomas E. Donilon will remain in his job, according to officials who spoke on the condition of anonymity to discuss internal White House deliberations.

Wednesday 12 December 2012

የኃይለ ማርያም የአስመራ መንገድ ከመለስ ይለይ ይሆን?

በየማነ ናግሽ

አንድ በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ወጣት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ‹‹ቶክ ቱ አልጀዚራ›› ከሚለው የአልጄዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በድረ ገጽ ለማግኘት እየታገለ ነው፡፡ አልጄዚራ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲዘጉ ከተደረጉ ድረ ገጾች መካከል ነውና አልቻለም፡፡ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃለ ምልልስ የሰጡት ለጋዜጠኞቹ ብለው ነው? ወይስ በአገራቸው ሕዝብ እንዲነበብ እንዳይታይ ከማይፈቀደው ሚዲያ ጋር መነጋገራቸው ምን ይሉታል?›› እያለ ከጓደኞቹ ጋር በማጉረምረም ከአንድ ኢንተርኔት ካፌ ሲወጣ አየሁት፡፡

እውነት ነው፤ የአልጄዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ ባይዘጋም ዘመኑ ባመጣው የኢንተርኔት ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ ማዳመጥ ወይም ደግሞ ማንበብ ለሚፈልግ ሰው ግን አይቻልም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የተለያዩ አገራዊና አካባቢያዊ ጉዳዮችን አስመልክተው የ25 ደቂቃ ቃለ ምልልስ ያደረጉበት ከኳታር (ዶሃ) የሚሠራጨው የአልጄዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ድረ ገጽ ተዘግቷል፡፡ ቪኦኤ፣ ናዝሬት፣ ዓባይ፣ ኢትዮ ሚድያ፣ መርካቶና ሌሎች በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ትችቶችን የሚያስተናግዱ ድረ ገጾችም እንደዚሁ ተዘግተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሚዲያዎችን በማፈን፣ ጋዜጠኞችን በማሰርና በማዋከብ ግንባር ቀደም ከሆኑ አገሮች ስሟ እየተጠራ ሲሆን፣ በተለይ ግን ድረ ገጾችን ‹‹ጃም›› በማድረግ በቅርብ ጊዜያት ቀዳሚ ሳትሆን እንደማትቀር ብዙዎች ይስማማሉ፡፡

ያም ሆነ ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ከአልጄዚራ ጋዜጠኛዋ ዥ ዱተን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር ስለተፈጠረው ቀውስ፣ ዕርዳታ ለፖለቲካ ጥቅም ፍጆታ ስለመዋሉ፣ የመሬት ወረራ፣ በቅርቡ ስለተደረገው የሥልጣን ሽግግርና የዓባይን ግድብ በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ፈገግ እያሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ በጋዜጠኛዋ ጥያቄዎች ሲቀርቡላቸው፣ በተለይ ደግሞ ግብፅንና ሱዳንን በተመለከተ ጋዜጠኛዋ ያቀረበችው ጥያቄ ከመረጃ እጥረት የተነሳ መሆኑን እያዋዙ ዘና ብለው ሲናገሩ፣ ከዚህ በፊት ለአገር ውስጥ ከሰጡዋቸው ማብራሪያዎች ብዙም ያልተለዩ ነበሩ፡፡

ተቋርጦ የነበረው የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ክስ እንደገና ተጀመረ

-    ዋስትና ተፈቅዶለት በ50 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቀ
በታምሩ ጽጌ

ሦስት ክሶች ተመሥርተውበትና ዋስትና ተከልክሎ ለአራት ቀናት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ፣ ክሱ ተቋርጦ በነፃ የተሰናበተው የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ የተቋረጠው ክስ በድጋሚ ትናንትና ፍርድ ቤት ቀርቦበት በ50 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቀ፡፡ ከነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በፍትሕ ጋዜጣ ላይ በራሱና በጽሑፍ አቅራቢዎች አምስት ጊዜያት ታትመው በወጡ መጣጥፎች ምክንያት ክስ ተመሥርቶበት፣ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ዋስትና በመከልከሉ ማረሚያ ቤት እንዲቆይ መደረጉ ይታወሳል፡፡

ክስ መሥርቶበት የነበረው የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ፣ ‹‹የማጣራው ምርመራ ስላለኝ እስከዚያው ድረስ ክሴን አቋርጫለሁ፤›› በማለት ነሐሴ 21 ቀን 2004 ዓ.ም. ለፍርድ ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ አማካይነት፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ነሐሴ 22 ቀን 2004 ዓ.ም. ከእስር ተፈትቶ ነበር፡፡ ዓቃቤ ሕግ ላለፉት ሦስት ወራት አቋርጦት በድጋሚ በተንቀሳቀሰው ክስ ውስጥ ጋዜጠኛ ተመስገን በተለያዩ ጊዜያት ዕትሞች ‹‹ሞት የማይፈሩ ወጣቶች፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እስከ መጨፈር፣ የሁለተኛ ዜግነት ሕይወት እስከመቼና ሲኖዶስና መጅሊስ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ማጥመቂያ›› የሚሉ መጣጥፎች ማወጣቱ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም በወጡት መጣጥፎች ወጣቶችን ለአመፅ አነሳስቷል፣ ቀስቅሷል፣ ስም አጥፍቷል በሚል ነበር የመጀመሪያው ክስ የቀረበው፡፡ አሁንም የቀረበው ክስ ይኼው ነው፡፡

በትናንትናው ዕለት ዓቃቤ ሕግ ለምን ክሱን ማንቀሳቀስ እንደፈለገ እንዲያስረዳ ችሎቱ ጠይቆት፣ ፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ክስን የማቋረጥና የመጀመር ሥልጣን እንዳልው ከመግለጽ ባለፈ በዝርዝር አላስረዳም፡፡ ፍርድ ቤቱ በሁለተኛነት ክስ የተመሠረተበትና የፍትሕ አሳታሚ የሆነው ማስተዋል የሕትመትና የማስታወቂያ ድርጅትም እንዲቀርብ አዞ፣ ክሱ መቀጠል አለመቀጠሉን በሚመለከት ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በአመራር ለውጥ የሚናጠው አዳማ የተረጋጋ አስተዳደር እንዲያገኝ ተወሰነ

•    ከተማውን የኦሕዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ይከታተለዋል
በውድነህ ዘነበ

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በየጊዜው በሚካሄድ የአመራር ለውጥ መረጋጋት ለተሳነው አዳማ (ናዝሬት) ከተማ የተረጋጋ አስተዳደር እንዲኖረው የሚያስችል ዕቅድ መንደፉ ታወቀ፡፡ በአዳማ ከተማ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ አራት ከንቲባዎች ከሥልጣናቸው ተነስተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአስተዳደሩ ሥር በሚገኙ መሥሪያ ቤቶች በተለያዩ እርከኖች ላይ የሚገኙ አመራሮችም ከቦታቸው ተነስተዋል፡፡

ይህ ከፍተኛ ሹምሽር ከተማው የሚፈልገውን ዕድገትና ለውጥ ማምጣት እንዳያስችል አድርጓል በሚል፣ የክልሉ መንግሥት የከተማው አስተዳደር የተረጋጋና ብቃት ያላቸው አመራሮች እንዲመድቡ ከተማው ከክልሉ መንግሥት የበጀት ድጋፍ የሚያገኝበትን መንገድ ቀይሷል፡፡

በዚህ ዕቅድ መሠረት ክልላዊ መንግሥቱ ከሁለት ሳምንት በፊት የከተማው ከንቲባ የነበሩትን አቶ ጉታ ላንቾሬንና ምክትላቸውን ከሥልጣን አንስቷል፡፡ በምትካቸው በፌዴራል ደረጃ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ የነበሩትን አቶ በኩር ሳህሌ ሾሟል፡፡

አቶ በኩር ሳህሌ የኦሕዴድን ማዕከላዊ ኮሚቴ ይሁንታ አግኝተው የተሾሙ ሲሆን፣ አስተዳደራቸውን ማዕከላዊ ኮሚቴው በቅርበት ይከታተለዋል ተብሏል፡፡ የአዳማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙት አቶ በኩር በየደረጃው ያሉ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች የሁለተኛውን የሦስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያስጀመሩ ሲሆን፣ ግምገማው ለሁለት ሳምንት ይቆያል ተብሏል፡፡

በግምገማው የተደረሰበት ነጥብ ከሕዝቡ ጋር ምክክር ከተደረገበት በኋላ ጥፋት አለባቸው የሚባሉ አመራሮች ዕርምጃ ሊወስድባቸው እንደሚችል ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከዚህ የአመራር ለውጥ በተጨማሪ አዳማ ከተማ ከክልሉ መንግሥት የበጀት ድጋፍ እንዲደረግለት ተወስኗል፡፡

በተለይ በቅርቡ የክልሉን የበጀት ድጋፍ ያገኛሉ ተብሎ በግንባር ቀደምትነት ከተቀመጡት የአዳማ ከተማ ፕሮጀክቶች መካከል የከተማውን የመጠጥ ውኃ እጥረት ለመቅረፍ የተቀመጠው ዕቅድና ከተማውን ከዓመት ዓመት እየመታ የሚገኘውን ጎርፍ በዘላቂነት ለማስወገድ የተቀመጠው ዕቅድ ይገኙበታል፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የመድረክ አመራር በእስራት ተቀጡ

-    ጋዜጠኛ ርዕዮተ ዓለሙ ለሰበር ያቀረበችው አቤቱታ ለውሳኔ ተቀጠረ
በታምሩ ጽጌ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውጭ ቋንቋ መምህርና የመድረክ ፓርቲ አመራር አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች ስምንት ተከሳሾች፣ ከሦስት ዓመታት እስከ 13 ዓመታት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትናንትና ተወሰነባቸው፡፡ በሽብርተኝነት ወንጀል በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የተመሠረተባቸውን ክስ ሲመረምር የሰነበተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ትናንትና በሰጠው የቅጣት ውሳኔ፣ አንደኛ ተከሳሽ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባን በስምንት ዓመታት፣ የኦህኮ ፓርቲ አመራር የነበሩትን አቶ ኦልባና ሌሊሳን በ13 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡

ሌሎቹ ተከሳሾች ማለትም ወልቤካ ለሜ፣ መሐመድ ቡሳ፣ ሐዋ ዋቆ፣ ደረጀ ከተማ፣ አዲሱ ሙከሪና ገልገሎ ቱፋ ከሦስት እስከ 12 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል፡፡ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ኦልባና ሌሊሳና አቶ ገልገሎ ቱፋ ለአራት ዓመታት ከማንኛውም ማኅበራዊ መብቶቻቸው ታግደዋል፡፡ ሌሎቹም ለሁለት ዓመታት ታግደዋል፡፡

አቶ በቀለ ገርባ በ2003 ዓ.ም. የተማሪዎች የመመረቂያ ጽሑፍ ሲመረምሩ በአጋጣሚ ያገኟቸውን ተማሪዎች፣ ‹‹ገዢውን መንግሥት መጣል አሁን ነው›› በማለትና በመመልመል ለኦነግ በመሥራትና ኦፌዴንን ከለላ በማድረግ የሽብር ተልዕኮ ሲፈጽሙ ነበር በማለት መከሰሳቸው ይታወሳል፡፡

አቶ ኦልባናም በአምቦ ተማሪዎችን በመመልመልና ወደ ኦነግ እንዲገቡ በማደራጀት ፀረ ሽብር ተግባር ሲፈጽሙ እንደነበር፣ ሌሎቹም እስከ ኬንያ ድረስ በመሄድ ሥልጠና እንዲወስዱ በማድረግ፣ ከኦነግ ጋር በመሥራት የሽብር ተልዕኮ ሊፈጽሙ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን መሠረት መከላከያ ቢያቀርቡም፣ የዓቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ሊያስተባብሉ አለመቻላቸውን በመግለጽ ጥፋተኛ ብሏቸዋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ያቀረበው የቅጣት ማክበጃ ቅጣቱ ከብዶ እንዲወሰን ነበር፡፡

በሁለት ቀናት ልዩነት ሦስት ጊዜ ቀብሯ የተፈጸመው ወላድ ጉዳይ እያነጋገረ ነው

-    አስከሬኗ ከመቃብር ወጥቶ ተገኝቷል
በታምሩ ጽጌ

የመጀመርያ ልጇን በቀዶ ሕክምና ከተገላገለች በኋላ ደም ፈሷት ሕይወቷ ያለፈው የ27 ዓመት ወጣት የቀብር ሥርዓቷ ባለፈው ቅዳሜ፣ እሑድና ከትናንት በስቲያ ሰኞ የመፈጸሙ ጉዳይ እያነጋገረ ነው፡፡ ሟች ቤተልሔም ሰለሞን ልጅ ወልዳ ለመሳም ዘጠኝ ወራትን ስትጠብቅና የእርግዝናዋንም ሁኔታ ስትከታተል ቆይታ የመውለጃዋ ዕለት በመድረሱ፣ ጎፋ ማዞሪያ ወደሚገኘው ሮያል የጽንስና የማኅፀን ሕክምና ከፍተኛ ክሊኒክ የሄደችው ኅዳር 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ነበር፡፡

ክትትል ስታደርግበት የነበረው ክሊኒክ ተቀብሎአት ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገባት በኋላ የምጥ መርፌ ቢወጋትም፣ በዕለቱ ልትወልድ አለመቻሏንና ወደ ቤቷ መመለሷን ወላጅ እናቷ ወይዘሮ በለጡ አበበና ባለቤቷ አቶ ፍስሐ እሸቴ ገልጸዋል፡፡

ቤተሰቦቿ እንደሚሉት፣ ቤተልሔም ምጧ እየተፋፋመ በመምጣቱ ኅዳር 28 ቀን 2005 ዓ.ም. ተመልሳ ወደ ክሊኒኩ ትሄዳለች፡፡ የክሊኒኩ ሐኪሞች ተቀብለዋት ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገቧት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ፣ ቤተሰቦቿ ተጠርተው “እንኳን ደስ ያላችሁ፤ በሰላም ተገላግላለችና የሕፃኗን ማቀፊያ አምጡ፤” ይባላሉ፡፡ በክሊኒኩ የተገኙት እናቷና ባለቤቷ ደስታቸውን በእልልታና እርስ በርስ በመሳሳም ገልጸው ለጥቂት ደቂቃዎች እንደቆዩ፣ ቤተልሔም “እናቴን፣ ባለቤቴንና ልጄን አሳዩኝ፤” ብላለች ተባሉና ሁሉም ገቡ፡፡ ቤተልሔም ከማደንዘዣ ነቅታ በደንብ እንዳነጋገረቻቸው ተናግረው፣ “ጠብቁ አሁን ትወጣለች” በመባላቸው ሕፃኗን ይዘው ከነበረችበት ክፍል ወጥተው መጠባበቅ መጀመራቸውን አስረድተዋል፡፡ ሐኪሞቹ “ትንሽ ቆዩና ባለቤቷን ጠሩት” የሚሉት የቤተልሔም እናት፣ እሳቸው ግራ ገብቷቸው በመጠባበቅ ላይ እያሉ፣ ባለቤቷ መኪናቸውን ይዘው ሲወጡ መመልከታቸውንና በዚያው መቅረታቸውን ተናግረዋል፡፡

ልጃቸው ምን እንደሆነች ያላወቁትና ግራ ተጋብተው ሲንቆራጠጡ ለነበሩት የቤተልሔም እናት፣ አንዲት ነርስና ዶክተር መጥተው የባለቤቷን ስልክ ሲጠይቋቸው፣ “ምነው ልጄ ምን ሆነች?” ሲሏቸው፣ “ደም ስላነሳት ደም እንዲሰጥ ነው” እንዳሏቸው ተናግረዋል፡፡

Panic in the fading powerhouse of TPLF By Robele Ababya

The late Zenawi kept all top state secrets close to his chest and went to his grave without sharing any of those to his successors. Therefore there is no doubt that damaging disarray and or split has taken center-stage within his party. The extinction of TPLF and the emergence of freedom for all Ethiopians are inevitable.

  There is fear in the vanishing TPLF powerhouse; now is the time to finish it off by staging a debilitating civil strike and invigorating the ongoing Ethiopian Muslims’ demand for civil rights. 

The mighty CPSU (Communist Party of the defunct Soviet Union) disintegrated leaving in its wake ruins upon which the process of building a democratic system flourished in earnest. The slogan “to each according to his needs and from each according to his ability” has long gone down the drain. Anti-corruption storm is sweeping across China, which is good news for the democratic opposition at home in Ethiopia and in the Diaspora - and a nightmare to the corrupt TPLF top officials. In the circumstances the TPLF borne out of Marxist Leninist League of Tigray has no chance to rebuild its gravely ruined powerhouse as argued in the paragraphs below.

Let us face the fact that the USA has to protect its huge investment on military assets in Ethiopia primarily for fighting Al Qaeda’s surrogate the Al Shabab in Somalia. This was the reason that President Obama had to call Prime Minister Hailemariam Desalegn and talk to him by telephone at the critical time that successor to the late tyrant was in doubt. The call was interpreted by many that the Ethiopian constitution must be upheld and that the Deputy Prime Minister should take over the reign of ‘power’. Obviously this would put the new PM under the control of the US authorities by proxy.

Journalists in prison reach record high: Turkey, Iran, and China among leading jailers

 CPJ
New York, December 11, 2012--The number of journalists imprisoned worldwide reached a record high this year, a trend driven primarily by terrorism and other anti-state charges levied against critical reporters and editors, according to a new report by the Committee to Protect Journalists.

"We are living in an age when anti-state charges and 'terrorist' labels have become the preferred means that governments use to intimidate, detain, and imprison journalists," said CPJ Executive Director Joel Simon. "Criminalizing probing coverage of inconvenient topics violates not only international law, but impedes the right of people around the world to gather, disseminate, and receive independent information."

The three leading jailers of journalists were Turkey (49), Iran (45), and China (32), where imprisonments followed sweeping crackdowns on criticism and dissent, making use of anti-state charges in retaliation for critical coverage. This pattern is present in most of the countries in the census. In Turkey, the world's worst jailer, authorities held dozens of Kurdish reporters and editors on terror-related charges and other journalists for allegedly plotting against the government. Following an extensive case-by-case review in 2012, CPJ confirmed journalism-related reasons in numerous cases previously unlisted by the organization, thus significantly raising the country's total.

CPJ's 2012 census of imprisoned journalists identified 232 writers, editors, and photojournalists behind bars on December 1, an increase of 53 from 2011 and the highest since the organization began the survey in 1990. The 2012 figure surpasses the previous record of 185 journalists imprisoned in 1996, underlining a disturbing trend of conflating coverage of opposition groups or sensitive topics with terrorism, evident since 2001.

Monday 10 December 2012

የታህሳስ ግርግር ሊደገም ይሆን?

 By Temesgen Desalegn
ለዘመናት በኢትዮጵያውያን ጫንቃ ላይ በመጣበቅ ‹‹ቫምፓየር›› ሆኖ የነበረው የአጼ ኃይለስላሴ አገዛዝ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማ ቁጭትና ኃዘኔታ የፈጠረባቸው ጥቂት ሰዎች ነበሩ፡፡ ግርማሜ ነዋይና አባሪዎቹ፡፡

ከሀገሪቱ ህዝብ ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው ‹‹አፈር ገፍቶ›› አዳሪ ቢሆንም፣ ጉልተኛው ስርዓት የወዙን ሲሶ ብቻ እንዲያገኝ ነበርና የተፈቀደለት፣ ከዓመት ዓመት በረሃብ እንዳለቀ፣ ጎጆው ከኃዘን ጋር ጋብቻ እንደፈፀመ፣ ህፃናት ልጆቹ ጠግበው ሳይበሉ፣ እንደ ልጅ ሳይቦርቁ በልጅነታቸው ዳግም ወደ ማይመለሱበት ዓለም መሄዳቸው ከማንም በላይ ያንገበገበው በሀገረ አሜሪካ እስከ ሁለተኛ ዲግሪው ድረስ የተማረው ግርማሜ ነዋይ፣ በወቅቱ በብርጋዴል ጄነራል ማዕረግ የአፄው ስርዓት ዋነኛ ጠባቂ የነበረው የ‹‹ክብር ዘበኛ›› አዛዥ ከነበረው ታላቅ ወንድሙ መንግስቱ ንዋይ፣ የፖሊስ አዛዡ ጄነራል ፅጌ ዲቡ፣ የፀጥታ ኃላፊው ኮለኔል ወርቅነህ ገበየው እና ጥቂት ቆራጦች ያላቸውን ኃይል አስተባብረው፣ ዘራፊውን ዘውዳዊ ስርዓት በኃይል ለማስወገድ ታህሳስ 2 ቀን 1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አደረጉ፡፡ ሆኖም ሙከራው በብዙ መስዕዋትነት ቢቀለበስም፣ የለውጡን መንፈስና ይዘውት የተነሱትን ጥያቄ ግን መቀልበስ አልተቻለምና፤ ይህ ከሆነ ከ13 ዓመት በኋላ የንጉሱ ስርዓት ላይመለስ በሕዝብ ኃይል ተሰናበተ፡፡ …የእነ ግርማሜ ነዋይ ሕዝባዊ ትግል የተቀሰቀሰበት ያ ዕለትም በሀገሪቱ ታሪክ ‹‹የታህሳስ ግርግር›› በመባል በወርቅ መዝገብ ተጻፈ፡፡

ታሪክ ሊደገም ይሆን?

እነሆም በስምና በጥቂት ነገሮች ከ“ቫምፓየሩ” የአጼው ስርአት መጠነኛ ለውጥ አድርጎ ወደ ስልጣን የመጣው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የዲሞክራሲና የፍትሕ ጥያቄ ያነሱ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን በዛሬው ዕለት (ታህሳስ ሁለት ቀን) ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡ በዚህም መሰረት ርዕዮት አለሙ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የኦፌዴንና የኦህኮ የአመራር አባላት ኦልባና ሌሊሳ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ 29 ሰዎች በከፍተኛው ፍርድ ቤት ፣ እኔ ደግሞ በነሃሴ ወር ተቋርጦ ከቃሊቲ በነፃ በተለቀኩበት ክስ በድጋሚ በከፍተኛው ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት እንቀርብ ዘንድ ተገደናል፡፡ የታህሳስ ግርግር መንፈስ ማለትም ይህ መሰለኝ፡፡

ምሁራንና ‘አክቲቪስቶቻችን’ ሆይ ትግላችን ከመለስ ዜናዊ ወይስ ከሥርዓቱ?

አንዳንድ በትኩሱ ስሜታዊነትን እንዳዘሉ የሚሰነዘሩ ሀሳቦችን ትንሽ ፋታ መስጠትና ማስተዋል የታከለበት የታረመና የተስተክካለ ሀሳብን መጠበቅ መልካም ምግባር ነው። የጠቅላይ አስለቃሻችን ነብስ ሙታኑን ከተቀላቀሉ በሁዋላ በአሳርና በመከራ ያልታሰበው ሰው ሁሉም ወደሚያስበው ስልጣን ላይ መምጣቱን ተከትሎ የሚሰነዘሩት ሀሳቦች ግን አሁን ድረስ ስክነት አሳይተዋል ብዬ ላስብ አልቻልኩም። ስህተቱ የኔ ከሆነ እዳው ገብስ ነው። የኔ አይነት ሀሳብ ያላቸው ሰዎች ብዙ ከሆኑ ግን መመለስ ያለበት ጥያቄ አለ ማለት ነው።

አቶ ኃይለማርያምን በተመለከተ ከፈጣሪ ጋራ ቀጥታ የግንኙነት መስመር አላቸው ከሚሉን አንስቶ ስለመልካም ባህሪያቸውና የአስተዳደር ችሎታቸው የሚነግሩንን ሰዎች የተለያዩ መድረኮች አስተናግደዋል። ፍትህን እውነትንና ነጻነትን በምድር፣ ሰማያዊ አምላክን ደግሞ ለነብሱ የያዘ ሰው ራሱ ተኩሶ ባይገድል እንኳን በአባሪነትና በተባባሪነት ወንጀል ስሙ ሊነሳ የግድ ነውና እንደምን ሆኖ መልካሙ ሁሉ እንደተቸራቸው ማሰብ ይከብዳል። በአንድ ስርዐት ውስጥ ያገለገለ ሁሉ የግድ ወንጀለኛ ነው ለማለት ፈጽሞ አይደለም። ነገር ግን የፖለቲካ ስልጣን ይዞ ቁንጮ ሆኖ የተቀመጠና በግድ ያልተመደበ ሰው እሺ ወይም እምቢ የማለት መብት አለውና የማይጠየቅበት ምክንያት የለም። እራሴን ለማዳን ሌሎቹን ማደን ግዴታዬ ነበር የሚል ካለ የፍትህ አካል የሚዳኘው ጉዳይ ይሆናል።

የሀገራችን ልሂቃን፣ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲከኞች በአብዛኛው ያቀርቡ የነበረው ሀሳብ ወያኔ ወይም የሽፍታው መንግሥት በጉልበቱ ስልጣን ላይ የተቀመጠና ተልዕኮውም አፍራሽ የሆነ ነው የሚል ነው። የዚያ ማስረጃውም ፍትህ የጎደለበት ጎጠኞች እንዳሻቸው የሚፈርዱበትና አሸባሪዎች ተሸባሪዎችን እየከሰሱ ጭለማ ቤት የሚያጉሩበት መሆኑ ነው። ጥላቻ ባደረባቸው የህብረተሰብ ክፍል ላይ የተነጣጠረ ጥቃት በመፈጸም የዘር ጥፋት የሚያስከትሉ ናቸው። የሀገሪቱን ሉዐላዊነት በማፍረስ፣ የተፈጥሮ ሀብትዋን በመመዝበር ከፍተኛ ዘረፋ ማድረጋቸው፤ በሀገሪቱ ስም ከሚመጣው እርዳታ በላይ ለሁለትና ሶስት መጪ ትውልድ የሚተርፍ ብድር በመበደር አገሪቱን ባለሀብቶች እንዳሻቸው የሚያደርጉበት አደገኛ ሁኔታ መፈጠር፤ የመናገር ብቻ ሳይሆን የማሰብም መብት መነፈግ ነው እያሉ ድህረ ገጾችን አጣበዋል፣ ኮንፈረንስ ላይ ተናግረዋል፣ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ መፈክር አሰምተውበታል። ነገር ግን ለዚሁ ሥርአት ትንሽ ፋታ እንስጠው የሚሉት ደግሞ ከዚሁ ወገን ያሉ መሆናቸው ግራ ያጋባል። ምክንያቱም የምንረካው በሰው ለውጥ ወይስ በሥርአት ለውጥ? ለኃይለማርያም የምንሰጠው ፋታ ለሥርዓቱ የሚሰጥ ፋታ አይደለምን? የሚለው ጥያቄ መመለስ ይገባዋልና ነው።

የጦር ሃይሎች ጠ/አዛዥ ማነው?

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
በከፍተኛው ፍ/ቤት ዳኛ ሆነው ለረጅም ዓመት አገልግለዋል፤ ከዚያ ከለቀቁ በሁዋላ በጥብቅና ሙያ እየሰሩ ይገኛሉ። ታዋቂው የህግ ባለሙያ አነጋጋሪ በሆኑ የኢህአዴግ የፈጠራ ክሶች ዙሪያ ለተከሳሾች ጥብቅና በመቆምና በድፍረት በመሙዋገት ይታወቃሉ። በ1997 ከአንድ የፈጠራ ክስ ጋር በተያያዘ ለተከሳሾች ጥብቅና ቆመው ነበር፤ በፌደራል ጠ/ፍ/ቤት በተሰየሙ ዳኛ ተብዬዋች ተግባር ክፉኛ የተበሳጩት እኚህ የህግ ባለሙያ በወቅቱ እንዲህ አሉኝ፥ «በንጉሱ ዘመን ነው፤ በአ.አ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ልንመረቅ ሽር ጉድ እንላለን። የምንወደው የህግ መምህራችን የኛን ሁኔታ ታዝቦ ኖሮ…አንድ ጥያቄ አቀረበልን፤ “p አሁን ሳያችሁ በደስታ እንደተዋጣችሁ ነው፤ በመመረቃችሁ ደስተኛ ናችሁ ማለት ነው?... “ ሁላችንም በጥያቄው ተገርመን ..< እንዴት መምህር?..በጣም ደስተኞች ነን ፤ > አልነው። ደግሞ ጠየቀን ፥ “pሁላችሁም ደስተኞች ናችሁ?”..ሲለን..< አዎን ደስተኞች ነን > አልነው በአንድ ድምፅ። በጣም አዝኖ እንዲህ አለን ፥ < ሕግ በሌለበት አገር ህግ ተምራችሁ ..ሕግ የምታስፈፅሙ ይመስል፥ እንዲህ
መደሰታችሁና መመፃደቃችሁ ታሳዝናላችሁ.!>… ዛሬ የበለጠ የመምህራችን ንግግር ታወሰኝ፤ እውነትም ሕግ በሌለበት አገር…»pሲሉ ታዋቂው የህግ ባለሙያ ያወጉኝን ለመጣጥፌ መንደርደሪያ ማስቀደሜ ያለምክንያት አይደለም።
                       
ጠ/ሚ/ር ተብለው የተቀመጡት ሃ/ማሪያም ደሳለኝ የጦር ሃይሎች ጠ/አዛዥነቱ ስልጣን አልተቀበሉም። ቀደም ሲል ይህ ስልጣን በአቶ መለስ እጅ ነበር። እንዲያውም የከፍተኛ ጄኔራሎች ሹመት በተመለከተ ቀደም ሲል የነበረውን ሕግ በመሻር ስልጣኑን ጠቅልለው የያዙት አቶ መለስ ነበሩ። ይህ የተደረገው ከ1993ዓ.ም ወዲህ ነበር፤ ከዚያ በፊት ግን የጦር አዛዦችን ሹመት የሚያቀርበው ጠ/ሚኒስትሩ ሲሆን የሚያፀድቀውና የሚሽረው ደግሞ ፕሬዝዳንቱ ነበር። ፕ/ት ነጋሶ ከስልጣን ለመልቀቅ የወሰኑበት አንዱ ምክንያት ይህው ነበር። ከሳቸው እውቅና ውጭ ጠ/ሚ/ሩ ጄኔራሎችን በማባረራቸው እንደነበር ይታወሳል። ከዛ በሁዋላ አቶ መለስ ስልጣኑ ሙሉ በሙሉ የጠ/ሚ/ሩ እንዲሆን የሚያስችል ህግ አውጥተው አረፉት። የሚሽሩትም የሚሾሙትም እርሳቸው ሆኑ።

ባለፈው ጊዜ ጠ/ሚ/ር ሳይኖር 34 ጄኔራሎች መሾማቸው ተነገረ፤ አስገራሚና አነጋጋሪነቱ እንዳለ ሆኖ ለዚህ የተሰጠው መልስ ይበልጥ አስቂኝ ነበር። «p ቀደም ሲል በጠ/ሚ/ሩ የተዘጋጀ ነው»p ብለው በረከት ተናገሩ። ከተሾሙት መካከል መለስ ለሹመት ለአፍታ ሊያስቡዋቸው የማይችሉ መኮንኖች መኖራቸው የበረከት መልስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ታዛቢዋች በወቅቱ አስተያየት
የሰጡበት ነው።

Susan Rice and Africa’s Unholy Trinity – By Prof. Al Mariam

Matriarch of the Unholy Trinity
Susan Rice, the current U.S. Ambassador to the U.N., has been waltzing (or should I say do-se-do-ing) with Africa’s slyest, slickest and meanest dictators for nearly two decades. More cynical commentators have said she has been in bed with them, as it were. No doubt, international politics does make for strange bedfellows.
Susan Rice, the current U.S. Ambassador to the U.NSusan Rice, the current U.S. Ambassador to the U.N
Rice’s favorite dictators in Africa are the “Unholy Trinity” — Paul Kagame of Rwanda, Yoweri Museveni of Uganda and the late Meles Zenawi of Ethiopia — all former rebel leaders who seized power through the barrel of the gun and were later baptized to become the “new breed of  African leaders” (a phrase of endearment coined by Bill Clinton to celebrate the “Three African Amigos” and memorialize their professed commitment to democracy and  economic development). She has been best friend for life and the acknowledged Guardian Angel, champion, apologist, promoter, advocate, grand dame and matriarch of the trio. She has shielded the “Fearsome, Threesome” from legal and political accountability, deflected from them much deserved criticism and thwarted national and international scrutiny and sanctions against them.
Rice, Rwanda and the Genocide That Was Not
In April 1994, when the Clinton Administration pretended to be ignorant of the unspeakable terror and massacres in Rwanda, Susan Rice — who by her own description “was a young Director on the National Security Council staff at the White House, accompanying the then-National Security Advisor, Anthony Lake” — and currently the putative heir apparent to Secretary of State Hilary Clinton, was unconcerned about taking immediate action to stop the killings. Rather, she was fretting about the political consequences of calling the Rwandan tragedy a “genocide”. In a monument to utter moral depravity and conscience-bending callous indifference, Rice casually inquired of her colleagues,