Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 3 November 2012

ከአሥር ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ 15 ቢሊዮን ዶላር መውጣቱ ተረጋገጠ

•    ካቻምና ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ታጥቷል
በአስራት ሥዩም
እ.ኤ.አ. ከ2001 እስከ 2010 ባለው ጊዜ ውስጥ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ሕጋዊ በሆነና ባልሆነ መንገድ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ ተደርጎ ወደ ውጭ ገበያዎች ማምራቱን በቅርቡ ይፋ የሆነ ሪፖርት አመለከተ፡፡ ይህ ችግር በመላ አፍሪካ ትኩረት እየሳበ እንደመጣ ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ምንጭ በእጅጉ ከሚያስፈልጉዋቸው ታዳጊ አገሮች ወደ ሌሎች አገሮች ገንዘብን በማዘዋወርና በሕገወጥ የፋይናንስ ግብይት እየወጣ ያለውን ሀብት በተመለከተ እ.ኤ.አ. ከ2009 ጀምሮ ሲወጡ የነበሩ ሪፖርቶች የሚያረጋግጡት፣ ክስተቱ ትኩረት እየሳበ መምጣቱን ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን ውስን የውጭ ምንዛሪ መጠን ይኼው ከፍተኛ የካፒታል ማዛወር ወይም ማሸሽ ተግባር በእጅጉ እየታየባት በመምጣቱ፣ የመነጋገርያ አጀንዳ እንድትሆን አድርጓታል፡፡

ተሻሽለው የወጡ አኀዞች እንደሚያመለክቱት፣ እ.ኤ.አ. ከ1970 እስከ 2010 በነበሩት ሰላሳ ዓመታት 24 ቢሊዮን ዶላር ከኢትዮጵያ እንዲሸሽ ተደርጓል፡፡ ገንዘብ በከፍተኛ መጠን እየሸሸ መሆኑ ከተመዘገበባቸው ጊዜያት ትልቁን ድርሻ መያዝ የጀመረው እ.ኤ.አ ከ2000 በኋላ ያለው ሲሆን፣ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2010 ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር በአገሪቱ ኢንቨስት ያደረጉ የውጭ ባለሀብቶች ያሸሹት ገንዘብ (ካለፈው ዓመት ኅዳር ወር አኳያ ከአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በላይ ሆኖ ተመዝግቧል) በከፍተኛነቱ ሲጠቀስ፣ ከዚህ መጠን ቀጥሎ የተመዘገበው ከፍተኛ የገንዘብ ማሸሽ እ.ኤ.አ. በ2002 የታየው የ3.1 ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡ በሪፖርቱ የቀረቡት መረጃዎች ሲፈተሹ፣ ባለፉት ሰላሳ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ የካፒታል ማሸሽ የተመዘገበባቸው ጥቂት ዓመታት ሆነው ይገኛሉ፡፡

ህወሃት ኢህአዴግ የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !

ህወሃት ኢህአዴግ የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !
ሜጀር ጄኔራል ሞላ ከስልጣን መውረድ ህወሃት ውስጥ ከተፈጠረው መከፋፈል ጋር የተያያዘ ነው :: ሜጀር ጄኔራል ሞላ የአየር ሃይሉ አዛዥነትን ስልጣን ጨብጠው ከነበሩት አራት የህወሃት አባላት ማለትም ከጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖት( ጆቤ) ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘውዴ) እና ጄኔራል አለምሸት ደግፌ አንዱ ነበረ ::
ባሁኑ ጊዜ የቀድሞው አየር ሃይል አዛዥና የህወሃት አባል የሆነው እንዲሁም በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር በሌለበትና ፓርላማ ባልመከረበት ሁኔታ የወታደራዊ ማዕረግ እድገት ከተደረገላቸው የመከላከያ አባላት አንዱ የሆኑት ሜጄር ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘወዴ) አየር ሃይሉን ባዛዥነት እየመሩ እንደሆነ ታውቋል::
በዚህ አመት ውስጥ ብዙ ባለስልታናቶች ከስልጣናቸው እንደሚነሱ የሚጠቁመው የውስጥ ምንጫችን ሌሎችም በቁልፍ ቦታ ላይ ያሉ ባለስልጣናቶች መነሳታቸው አይቀርም ሲሉ ይናገራሎ ሆኖም ግን ማንነታቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል በአጠቃላይ ህወሃት የሚያደርገው የስልጣን ሽግሽግ አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ከላይ የሚያስቀምጣቸው ከተለያዩ የህወሃት አጋር ድርጅቶች የተመረጡ ባለስልታናትን ብቻ ሲሆን ከዚያ ውጭ ከስር በመሆን የማስተዳደሩን ስራ ሲተገብሩ ይኖራሉ በማለት ምንጫችን ይገልጻሉ ። አጠቃላይ የወያኔ አስተዳደር ከቀድሞው ሊቀመንበሩ አቶ መለስ ዜናዊ ስርአተ ሞት በኋላ የመንሸራተት እና ከፍ ዝቅ የማለት እይታ ይታይበታል። አቶ ጁነዲን ሳዶን ከውጭ አገር ህክምና ካገደ በኋላም ሌሎችን ባለስልጣናትን ጨምሮ የቁም እስረኛ አድርጎ ያስቀመጣቸው ሰዎች እንዳሉ የማለዳ ታይምስ የውስጥ መረጃ ያመለክታል ።በዚህ አመት ውስጥ በወያኔ ኢሃዴግ ከተሰሩት ስህተቶች ውስጥ ያለ ጠቅላይ ሚንስትሩ የመኮንኞች ሹመት ማጽደቁ ፓርላማውን እና እንዲሁም አስተዳደሩንም ያስገመተም ከመሆኑም በላይ የራሱን አካላቶች በከፍተኛ ቦታ ላይ ለማስቀመጥ ያደረገውን ዝግጅቱን ለማሳየት በቂ መረጃ ነው ሲሉ መረጃዎቻችን አብራርተዋል

Tuesday 30 October 2012

በማረቃ ወረዳ የየኔሰው ገብሬ ጓደኛ የሆነው ወጣት ራሱን በአደባባይ ሰቀለ

ጥቅምት ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ የትምህርት ክፍል የሜዳሊያ ተሸላሚ  የነበረው ወጣት ግርማ ወ/ማርያም ራሱን በአደባባይ ለመስቀል የተገደደው በአካባቢው ያለውን የመልካም አስተዳዳርና የፍትህ እጦት በመቃወም መሆኑን ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ለኢሳት ገልጠዋል።
በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ፣ በዳውሮ ዞን ፣በማረቃ ወረዳ ፣ በዋካ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ወጣት ግርማ ወ/ማርያም፣ በ1980 ዓም ነበር የተወለደው ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን 3 ነጥብ 8 በማምጣት  በአንደኝነት አጠናቆ ወደ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ መግባቱንና የኢኮኖሚክስ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት ማጠናቀቁን ለማወቅ አጠናቋል።
ትምህርቱን እንዳጠናቀቀም በማረቃ ወረዳ በታክስና አስተዳዳር ተቀጥሮ መስራቱን፣  ይሁን እንጅ በስራ ላይ እያለ ከፍተኛ የሆነ የአስተደዳር በደል እንደደረሰበት በተለይም ወጣት የኔሰው ገብሬ ራሱን በማቃጠል ከገደለ በሁዋላ ወጣቱ የየኔሰውን ጥያቄዎች ያቀነቅናል በሚል ከፍተኛ ጫና ሲደርስበት እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ይገልጻሉ። የወረዳው ባለስልጣናትም ወጣት ግርማ ከስራው እንዲታገድ በማድረግ ለ4 ወራት ያክል ምንም ክፍያ ሳያገኝ ያለስራ እንዲቀመጥ አድርገዋል። ወጣት ግርማ ወደ ባለስልጣናት በተደጋጋሚ በመመላለስ መፍትሄ ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ሊሳካለት ባለመቻሉ ባለፈው አርብ ራሱን በአደባባይ በገመድ በመስቀል አጥፍቷል።
ኢሳት ከወጣት ግርማ ወ/ ማርያም ቤተሰቦች ጋር ቃለምልልስ አድርጓል።
በሌላ በኩል የማረቃ ወረዳ  አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ መላኩ ወጣት ግርማ ወ/ ማርያም በመልካም አስተዳዳር እጦት ራሱን አጥፍቷል የሚለውን እንደማይቀበሉት ለኢሳት ገልጠዋል።

Monday 29 October 2012

ለፉት 30 አመታት ከኢትዮጵያ ተዘርፎ ወደ ውጭ አገራት ባንኮች የተሻገረው ገንዘብ 450 ቢሊዮን ብር ደረሰ

ጥቅምት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-አሜሪካ የሚገኘው የማሳቹሴትስ ዩኒቨርስቲ በያዝነው ወር ባወጣው አዲስ ጥናት ከኢትዮጵያ እየተዘረፈ ወደ ውጭ አገራት ባንኮች የተሻገረው ገንዘብ ባለፉት 30 አመታት ውስጥ 25 ቢሊዮን ዶላር ወይም 450 ቢሊዮን ብር መድረሱን ይፋ አድርጓል። ይህ አሀዝ  አገሪቱ ካላት አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ነው።
ኢትዮጵያ ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጋር ሲተያይ የ8ኛ ደረጃነት ብትይም ነዳጅ ከማያመርቱ አፍሪካ አገሮች ጋር ስትወዳደር ደግሞ ቀዳሚ ሆናለች።
አብዛኛው ገንዘብ የሚዘረፈው ወደ ውጭ አገራት ከሚላኩና ከውጭ አገራት ከሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ከሚልኩት ገንዘብ ነው፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ስፖንሰርነት ጥናቱን ያካሄደው ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ባለፉት 7 አመታት ከኢትዮጵያ ከ 11 ቢሊዮን ዶላር  ወይም ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ መዘረፉን ይፋ ባደረገ አመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ነው ማሳቹሴትስ ዩኒቨርስቲ አዲሱን አስደንጋጭ ሪፖርት ይፋ ያደረገው።
ከቻይናና ህንድ የተገኘውን ብድር ጨምሮ ኢትዮጵያ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ የውጭ እዳ እንዳለባት መዘገባችን ይታወሳል።

መስማት የተሳነው፡ ስብሃት ነጋ

ከማተቤ መለሰ ተሰማ
sebehat nega one of the founders of TPLFበአጼ ምኒልክ ዘመን፡ አንድ ኢትዮጵያዊ፡ በድንገት መስማት ይሳነዋል አሉ፡ ሰውየው እድሜ ጠግቦ እስከሚሞት፡ የምኒልክ፣ የእያሱ፣ የዘውዲቱ ንግስና አልፎ፡ ከሀይለ ስላሴ የግዛት ዘመን አጋማሽ ድረስ ቆይቶ ነበርና፡ ጆሮው መስማት ከማቆሙ በፊት የነበረው ሁሉ እንዳለ፡ የቀጠለ መስሎት፡ በምኒልክ አምላክ እንዳለ ነው የሞተው ይባላል። በአጠቃላይ ስነምግባሩ፡ ሲታይ ከሰው ተወልዶ ከእንስሳት ጋር እንዳደገ፡ በግልጽ የሚመሰክርበት፡ ስብሃት ነጋም፡ እንዳይሰማ ጆሮው የደነቆረው፣ እንዳያነብ አይኑ የታወረው፡ ደደቢት ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን የሚቀር አይመስለኝም። ምክናያቱም ዛሪ ሕዋሃት የማስመሰያ ካባውን አጥልቆ፡ ኢትዮጵያዊ ለመባል እየጣረ ባለበት ወቅት ስብሃት ከ21 አመት በሗላ የሚናገረው ሁሉ፡ በምኒልክ ሲል እንዳለፈው ሰው ደደቢት በነበረበት ጊዜ ሲሰበክ የነበረውን፡ የኢትዮጵያን ህዝብ ማዋረድንና አማራንና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን  ማጥላላት፣ ስለአከተመለት ስርአት ሰለደርግ ማውራትን ነው። ከዚህ አንጻር ሲታይ፡ በአሁኑ ወቅት ሰውየውን በጥሞና ለሚከታተለው ሰው፡ ዘመናት ጥለውት ከንፈው እሱ አንድ ቦታላይ ቆሞ ለብቻው እየቆዘመ እንዳለ ለመገንዘብ አያዳግተውም።

ለነገሩማ እርጅናም፡ በአንዳንድ ሰዎች ላይ የህሌና ሚዛንን ማዛባቱ ባይቀርም፡ ስብሃትን ግን ከእድሜው በላይ ያደነቆርው፡ ቀን ሲያኝከው የሚውለው ጫት፣ ማታ ተዘፍዝፎበት የሚያድረው አረቄ ነውና፡ እነዚህ ሁለት አድገኛ የሰው ልጅ የአካልም የአእምሮም ጠንቅ የሆኑና አቅልን የሚያስቱ ነገሮች፡ ማየትና መስማቱን ብቻ አይደለም፡ ህይወቱንም አለመንጠቃቸው የሚያስገርም ነው።

ውድ አንባብያን፡ በዚህ ጽሁፊ ስብሃት ነጋን አንተ እያልሁ የምገለጸው፡ የክብርን ዋጋ ለማያውቅና፡ በ90 ሚሊዮን የሚገመተውን ጭዋና አስተዋዩን የኢትዮጵያን ህዝብ በጠቅላላ ለሚዘልፍ ሰድ አክብሮት መስጠት፡ እራስን እንደማዋረድ ስለምቆጥረው መሆኑ ይታወቅልኝ። ለምን የሚል ካለ መልሴ፡ ሌላውን ትቸ 19/10/2012 የጀርመን ሶሻሊስት ፓርቲ ባዘጋጀው፡ የአፍሪካ የውይይት መድረክ ሰብሰባ ላይ ተገኝቶ በነበረበት ወቀት ከተናገረው 2ቱን ለአብነት ብጠቅስ በቂ ይመስለኛል። ስብሃት ነጋ ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ መጻሂ እድልና የፓለቲካ ምህዳር እንዲያብራራ ለቀረበለት ጥያቄ፡ በተለመደውና ስነምግባር ባልገራው አንደበቱ የሰጠው ከጥያቄው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው መልስ፡ 1ኛ/ ስነስራት የሌለውን የኢትዮጵያን ህዝብ ስራት ለማስተማርና፡ የደርግ እርዝራዦችን፡ ለመቆጣጠር በዙ ጊዜ አሳልፈናል። 2ኛ/ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሴ ብቁ አይደለም የሚል ነበር። ማን ይሆን፣

Sunday 28 October 2012

Sibhat Nega’s controversial statement “If you claim Assab; you are Dergue” (VIDEO)


አርበኞች ግንባር በሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ የተሳካ ወታደራዊ ማጥቃት አካሄደ



የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በጥቅምት 15-2005 ዓ.ም ከወያኔው የመከላከያ ሰራዊትና ሚሊሻ ጋር በሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ልዩ ስሙ ዳንጉራ በሚባል ስፍራ በወሰደው ድንገተኛ ወታደራዊ ማጥቃት አስር(10) የስርዓቱን ቅጥረኛ ወታደሮች በመግደልና አምስት (5) በማቁሰል በአናሳው ቡድን የሃይል ጣቢያ ላይ ከፍተኛ ድልን ተጎናጽፏል።

በእለቱ በአካባቢው ሲንቀሳቀስ የነበረው ነበልባል ሻምበል በወሰደው ድንገተኛ ማጥቃትና በተመዘገበው ድል በአካባቢው የሚኖረው ማህበረሰብ አንጀቱ መራሱንና ወያኔው በአሁኑ ወቅት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ እያወረደ በሚገኘው የጅምላ ጭፍጨፋና እስራት በንፁሃን የሙስሊም ሃይማኖት ተከታዮች ውስጥ በሃይማኖት ጉዳዮች በመግባት የእምነቱ መሪዎችን ፣ የእምነቱ አግልጋዮችና አዳሪዎች ሳይሆኑ በሃይማኖት ሽፋን የአገዛዙ የፕሮፓጋንዳ አስተጋቢዎችና የፖለቲካ ሹሞች መሆን ይኖርባቸዋል በማለት እብሪተኛው ቡድን የራሱን ሰዎች የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች እንዲሆኑ ያለ የሌለ ሃይሉን በመጠቀም የሃይማኖት ነፃነት ያስጠብቃል ተብሎ የወጣው የይስሙላ ሕገ-መንግስት የሰጠውን መብት እንኳን ሕዝበ-ሙስሊሙ ሊከበርለት አልቻለም።

ይህን ጉዳይ ሕዝበ-ሙስሊሙንም  ሆነ የሌላ ሃይማኖት ተከታይ የሆነው ኢትዮጵያዊ ሁሉ አግባብነት የሌለው ጭፍን እርምጃ መሆኑን በአደባባይ እየመሰከሩና ከአምባገነኑ ስርዓት ጋር በተቃውሞ ትዕይንት ፊት ለፊት እየተጋፈጠ በሚገኝበት በዚህ ወቅት ነበልባል በመባል የሚታወቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ከሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ በወያኔው መከላከያና ሚሊሻ ታጣቂ ሃይል ላይ ከወሰደው ወታደራዊ ማጥቃት ባሻገር በአካባቢው ለሚገኘው ማህበረሰብ በወቅታዊ የወያኔው የግፍ አገዛዝን አስመልክቶ እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማና እንቅስቃሴ ገለፃ አድርጓል።

በእስራኤል የተደበደበው የሱዳን ሚስጢራዊ የጦር መሣሪያ ፋብሪካ ለኢትዮጵያ ሥጋት መሆኑ ተጠቆመ

በጋዜጣው ሪፖርተር
ባለፈው ማክሰኞ ሌሊት ከሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በስተደቡብ የሚገኘው ሚስጥራዊ የጦር መሣርያ ፋብሪካ በእስራኤል የሚሳይል ጥቃት እንደተፈጸመበት ከታወቀ በኋላ፣ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ሥጋት መሆኑን ዜጎችና የፖለቲካ ተንታኞች እያስረዱ ነው፡፡
እስራኤል በዚህ እጅግ ሚስጥራዊ ነው በተባለለት ወታደራዊ የጦር መሣርያ ፋብሪካ ላይ ጥቃቱን የፈጸመችው በቅርቡ በሒዝቦላህ የተላከባት ሰው አልባ የጦር አውሮፕላን (Drone) ግዛቷ ውስጥ መትታ ከጣለች በኋላ መሆኑ ታውቋል፡፡ የእስራኤል ወታደራዊ ባለሥልጣናት ሰው አልባው የጦር አውሮፕላን የተመረተው በካርቱም የጦር መሣርያ ፋብሪካ ውስጥ መሆኑን፣ በግብፅ በኩል ተጓጉዞ ለኢራን ከደረሰ በኋላ ሊባኖስ ውስጥ ለመሸገው ሒዝቦላህ መሰጠቱን መግለጻቸው በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኅን ተገልጿል፡፡

ምንም እንኳን እስራኤል የጦር መሣርያ ፋብሪካውን በሚሳይል ማጥቃቷን በቀጥታ ባታስተባብልም፣ የሱዳን መንግሥት ከጠላቶቿ ጋር እያሴረባት መሆኑን ወታደራዊ ባለሥልጣናቷ እየገለጹ መሆናቸው ተሰምቷል፡፡ የሱዳን መንግሥት ጥቃቱን የፈጸመችው እስራኤል መሆኑን አስታውቆ፣ ጉዳዩን ወደተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት እወስዳለሁ ብሏል፡፡ በተጨማሪም ለጥቃቱ አፀፋ ምላሽ እንደሚሰጥ ዝቷል፡፡ የሱዳን መንግሥት የካርቱም የጦር መሣሪያ ፋብሪካው መደብደቡን ማረጋገጡ ለኢትዮጵያና ለአካባቢው አገሮች ጭምር ሥጋት መሆኑን የሚገልጹት ተንታኞች፣ በተለይ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ትኩረት ሰጥታ ልትከታተለው ይገባል ይላሉ፡፡

ለዚህ አባባላቸው ዋቢ የሚያደርጉት ከካርቱም በስተደቡብ ከዋናው አውራ ጎዳና ሁለት ኪሎ ሜትር ገባ ብሎ በአደገኛ የሽቦ መከላከያ የታጠረው ሚስጥራዊ የጦር መሣርያ ፋብሪካ፣ በኢራን ድጋፍ ሰው አልባ የጦር አውሮፕላኖችንና ረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳይሎች ስለሚመረቱበት ነው፡፡ በአፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ምርምር የሚያካሂዱ አንድ ስማቸው ያልተገለጸ ተመራማሪ፣ በሱዳን ውስጥ የተገነባው ሚስጥራዊ የጦር መሣርያ ፋብሪካ ኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ላለችው የህዳሴ ግድብ ጠንቅ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡