Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 15 September 2012

አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ሆኑ: የሕወሓት ሊቀመንበርነት እስካሁን ምርጫ እልተካሄደበትም

Sat Sep 15, 2012 4:19 pm
በዘካርያስ ስንታየሁ

(Reporter) - ባለፈው ዓርብና ቅዳሜ በዝግ የተካሄደው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ የግንባሩን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር በሙሉ ድምፅ በመምረጥ ተጠናቀቀ፡፡

ከአራቱ አባል ድርጅቶች የተውጣጡ 180 አባላት ያሉት የኢሕአዴግ ምክር ቤት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን በሊቀመንበርነት ሲመርጥ፣ አቶ ደመቀ መኮንን ደግሞ ለምክትል ሊቀመንበርነት ተመርጠዋል፡፡ በድርጅቱ ልምድ መሠረት ሊቀመንበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ምክር ቤቱ ሲስማማ፣ ምክትል ሊቀመንበሩም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ መወሰኑ ታውቋል፡፡

ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የግንባሩን ሊቀመንበር አቶ መለስ ዜናዊን እንዲተኩ በኢሕአዴግ ሕገ ደንብ መሠረት በምክር ቤቱ አባላት የተመረጡት አቶ ኃይለ ማርያም፣ የደኢሕዴን ሊቀመንበርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመሆን በማገልገል ላይ ነበሩ፡፡ ለግንባሩ ምክትል ሊቀመንበርነት የተመረጡት አቶ ደመቀ የብአዴን ሊቀመንበርና የትምህርት ሚኒስትር ናቸው፡፡

Thursday 13 September 2012

SVT released additional video exposing the orchestrated arrest of two Swedish journalists in Ethiopia


(SVT) — Yesterday SVT showed video as an evidence that the arrest of Swedish journalists in Ethiopia was staged. Now we can show even more pictures from the interrogations. (Warning: GRAPHIC IMAGES)

In the new the latest video, one can see how Martin Schibbye during a hearing was forced to show the contents of his luggage item by item: vitamin-c tablets, mobile phones, batteries, passport, camera equipment, press card …

“This is a bag to carry things in. This is my Swedish passport. This is my mobile phone” … he says in the film.

It is unclear how long after the arrest of the two Swedish journalists the video was recorded, but according to SVT’s source, the two were in custody for several days before the video was recorded.

የተሰጠው ወታደራዊ ሹመት በመከላከያ ውስጥ ያለውን ቅሬታ ተጠቆመ

መስከረም ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- በምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት ማክሰኞ ዕለት የተሰጠው ወታደራዊ ሹመት ከብሔራዊ ተዋጽኦ አንጻር በመከላከያ ውስጥ ያለውን የቆየ ቅሬታ ማባባሱን ምንጮች ጠቆሙ፡፡
ትላንት ከሕመማቸው በማገገም ላይ ባሉት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የተሰጠው ወታደራዊ ሹመት 34 የመከላከያ ኮሎኔሎችን ወደ ብርጋዴር ጄኔራል ያሳደገ ሲሆን ከነዚህ ሹማምንት መካከል ከግማሸ በላይ የሚሆኑት የቀድሞ የህወሃት ታጋዮች መሆናቸው ከብሔር ተዋጽኦ አንጻር ወትሮም የነበረውን ውጥረት እንዳባባሰው ምንጫችን ጠቁመዋል፡፡

በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ከፍተኛ አመራሩን የተቆጣጠሩት የህወሃት ታጋዮች መሆናቸው ለረዥም ጊዜ ቅሬታ ሲቀርብበት የነበረ ጉዳይ ከመሆኑም በላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ የነበሩት ሟቹ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ችግሩን ለመፍታት አለመሞከራቸው በሰራዊቱ ውስጥ የጎሰኝነት ስሜት ሥር ሰዶ እንዲቆይ ምክንያት መሆኑን ምንጫችን አስረድቶአል፡፡ በዚህም ምክንያት በሠራዊት ውስጥ ዋንኛ መለያ ማዕረግ ወይም የሥራ ብቃት ሳይሆን ጎሳ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ሰራዊቱ አሁን ድረስ “እሱ እኮ ህወሃት ነው፣እገሌ ብአዴን ነው…”በሚል የሚታወቅበት አሳዛኝ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ፤ ይህ ደግሞ ወቅቱን ጠብቆ መፈንዳቱና ዋጋ ማስከፈሉ እንደማይቀር ምንጫችን ተናግረዋል፡፡

ጠ/ሚኒስትር ባልተሰየመበት ሁኔታ ተጣድፎ ለመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች ብቻ ሹመት መስጠቱ አዲሱ የአገሪቱ አመራር የሰራዊቱን ድጋፍ ከወዲሁ ለማግኘት የታለመ ሳይሆን እንደማይቀር የጠቆሙት ምንጫችን ይህ እርምጃ የቀድሞ የህወሃት ታጋዮችን ብቻ መጥቀሙ ግን መካከለኛና ዝቅተኛ አመራሩን ጨምሮ በርካታ የሠራዊቱን አባላት ማስከፋቱ ሌላ ችግር ሆኖ ብቅ እንዳይል ሥጋቱን ገልጻል፡፡

አቶ አባይ ወልዱ አቶ መለስ ዜናዊን በመተካት ሊቀመንበር ሆኑ::

መስከረም ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- የህወሃት ሥራ አስፈጻሚ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ በሟቹ በአቶ መለስ ምትክ በአሁኑ ወቅት የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት የሆኑትንና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር የነበሩትን አቶ አባይ ወልዱን ሊቀመንበር አድርጎ ሲመርጥ ኦህዴድ በበኩሉ ከህመም ጋር በተያያዘ የመልቀቂያ ደብዳቤ ባስገቡት አቶ አለማየሁ አቶምሳ ምትክ የአ/አ ከተማ ከንቲባ የሆኑትን አቶ ኩማ ደመቅሳን መምረጡን ምንጫችን ጠቁሟል፡፡
አዲሱ አመራር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን ጠ/ሚኒስትር፣አቶ ኩማ ደመቅሳን ምክትል በማድረግ ከስድስትወር በኃላ እስከሚካሄደው የግንባሩ ጉባዔ ድረስ እንዲያገለግሉ በቅርቡ ይሾማቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አውራምባ ታይምስ እንደዘገበው፤ አቶ ሀይለማርያምን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከማስቀጠል ውጪ ሌላ አማራጭ ያጣው ኢህአዴግ፤ በአቶ ሀይለማርያም ሥር ሦስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ለመሾም ወስኗል።

ሪፖርተር በበኩሉ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ይመረጣሉ ተብለው የሚጠበቁት አቶ ሀይለማርያም የአቶ መለስን ያህል አቅም ስለማይኖራቸው ፤ ኢህአዴግ ከአንድ በላይ  ምክትል  ጠቅላይ ሚኒስትሮችን ሊሾምላቸው  እንደሚችል ዘግቧል።
ይሁንና የሚሹሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሁለት ይሁኑ አለያም ሦስት ጋዜጣው በትክክል ያስቀመጠው ነገር የለም።

አውራምባ እንዳስነበበው፤ሦስቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችም፤ አንዱ ከኦሮሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ)፣አንድ ከብሔረ-አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ብአዴን) እና አንድ ከሕዝባዊ ወያነሀርነት ትግራይ(ህወሀት) የሚውጣጡ ናቸው።

Wednesday 12 September 2012

በቁማቸው ከገደሉት በሞታቸው የገደሉት -በፍቃዱ ዘ ኃይሉ

Befekadu Zehailu




 አገር ቤት እንዳትታተም ከተከለከለችው ፍኖተ ነጸነት የተወሰደ!!!!
 
የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ሞት በብዙዎች ጉንጭ ለሁለት ወር ሲጉላላ ቆይቶ በኢትዮጵያ መንግስት ከተረጋገጠ ይኸው ሁለት ሳምንት ሊሆነው ጥቂት ቀናት ቀሩት፡፡ መንግስት ብሔራዊ የሐዘን ቀናት እስከዕለተ ቀብራቸው በማወጁ ባንዲራም ዝቅ ብሎ እየተውለበለበ ነው፣ መገናኛ ብዙሐንም ሙሉ ትኩረታቸውን በዚያው በሐዘኑ ጉዳይ ላይ እንዳደረጉ ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ የጡረተኛ ሚኒስትሮችን ጥቅማጥቅም የሚዘረዝረው የ2001 አዋጅ ላይ [አንቀጽ 11/1/ለ] ብሔራዊ የሐዘን ቀን አንድ ቀን እንደሆነ ይደነግጋል፡፡)
ኢትዮጵያውያን ወትሮም ቢሆን ሐዘን የማክረር ባሕላችን የተጋነነ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሠልስት ሳይቀር እየተሰረዘ የሦስቱ ቀን ሐዘን ወደሁለት ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡ በነገራችን ላይ የሐዘን ቀናት ወደሦስት ቀናት ዝቅ እንዲሉ የተደረገው በአፄ ምኒልክ አዋጅ የዛሬ መቶ ዓመት ገደማ ነበር፡፡ እንግዲህ በሰሞኑ፣ ሁለት ሳምንታት የዘለቀ የሐዘን ግዜ መቶ ዓመት ያህል ወደኋላ ተመልሰናል ማለት ይቻላል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር የሞተበት አገር ሕዝብ ማዘኑ አስገራሚ ላይሆን ይችላል፤ ነገር ግን በውዴታም ይሁን በግዴታ ይህንን ያህል ቀናት ማዘኑ ወይም እንዲያዝን ማድረጉ ብዙ ጥያቄዎችን ያጭራል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የምናውራውም ከዚህ ፈር ከለቀቀ የሐዘን ግዜ በስተጀርባ ስላሉ ጉዳዮች ነው፡፡
አንድ፤ ችግር ይኖር ይሆን?
አገሪቱ አሁን እየተመራች ያለችው በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ነው ቢባልም፣ ያንን የሚያስመሰክር ነገር አላየንም፡፡ የመንግስት ልሳን የሆኑት እነ አዲስ ዘመን ሳይቀሩ ‹‹ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር›› እያሉ ነው የሚጠሯቸው፡፡ ከዚያም በላይ አሳሳቢው ግን በቶሎ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ማዕረግ በፓርላማ ምርጫ እንዲቀበሉ አለመደረጉ አጠያያቂ ነው፡፡ ምንም እንኳን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት በታወቀ በሦስተኛው ቀን ተመርጠው፣ ቃለመሓላ እንደሚፈጽሙ ቃል ተገብቶልን የነበረ ቢሆንም፣ መጀመሪያ ‹‹በአቡነ ጳውሎስ ቀብር›› በኋላም ደግሞ ‹‹የፓርላማ አባላት ሐዘናቸውን ይወጡ›› በሚሉ የማያሳምኑ ምክንያቶች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል፡፡ ይሄ ቁርጥ ያለ ቀን ለማስቀመጥ ያለመወሰን ጉዳይ አሁንም በአቶ ኃይለማርያም ተተኪነት ላይ በግንባሩ ውስጥ (ከምስጢር ወዳድነቱ አንፃር) ስምምነቶች አለመኖራቸውን የሚያጠራጥር ነው፡፡

በሞታቸው ዴሞክራት የሆኑ መሪ – በብስራት ወ/ሚካኤል





   እውነት ለመናገር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህይወት እያሉ አምባገነን መሆናቸውና በርካታ ጥፋቶችን በዜጎች ላይ መፈፀማቸው ከማንም የሚሸሸግ አይደለም፡፡ አብዛኛውን ህዝብ ባያስደስትም የተወሰኑ በጎ ተግባራትም ነበሯቸው፡፡ ይሁን እንጂ ከፈፀሟቸው ጥፋቶች አንፃር በየመንደሩ፣ በየትራንስፖርት አገልግሎቱ፣ በየመስሪያ ቤቱ፣ በየቤተክርስቲያኑና በየመስጊዱ ስለሳቸው ጥሩ ነገር አይወራም ነበር፡፡ ይሄን ደግሞ ጆሮ ጠቢዎቻቸው ገልብጠው ተቃራኒውን ካልነገሯቸው በስተቀር እርሳቸውም ያውቁት የነበረ ይመስለኛል፡፡ 
ለዚህም ነው አንድም ቀን በአዲስ አበባም ሆነ በክልሎች በነፃነት ሳይንቀሳቀሱ ስንቱን ንጹህ እስር ቤት እንዳላጎሩ እርሳቸውም ራሳቸውን በቤተ መንግስት በፈቃዳቸው አስረው በሞት የተለዩት፡፡ እኚህ ሰው በነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም መሞታቸው የተነገረው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ናቸው፡፡    ሞታቸው ሲሰማ ግን በካድሬዎቻቸው ፕሮፖጋንዳ ስንቱ እንዳዘነላቸው ላየ ምነው ተነስተው ባዩ ያሰኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያዝንለትና የሚያከብረው መሪ አጣ እንጂ በባህሪው ሩህሩህና አዛኝ ነው፡፡ በአቶ መለስ ሞት ይህንን የታዘብኩ ቢሆንም ከየቀበሌው( ከየወረዳው) እና ከየመስሪያ ቤቱ በግድ ቤተ መንግስትና በተለያዩ የተዘጋጁ ቦታዎች ሄደው ልቅሶ እንዲደርሱ የተደረጉ የአዲስ አበባና አጎራባች ከተሞች ነዋሪዎችን ላየ ይሄ ሁሉ ህዝብ ይወዳቸው ነበር እንዴ? ያሰኛል፡፡
ያልተደፈረው ገነት
     አዲስ አበባ አራት ኪሎ ያለው የኢትዮጵያ ታላቁ ቤተ መንግስት ለዜጎች “ያልተደፈረ ገነት ነው” ይባላል፡፡ አንዳንድ ሰዎች የዚህን ምክንያት ሲገልፁ አዳም እጸ – በለስ በልቶ ከገነት ሲባረር፤ የኢትዮጵያ ታላቁ ቤተ መንግስት ለመግባት ግን ያቺን፣ እፀ በለስ መብላት ግድ ይላል ይላሉ፡፡ ምክንያቱም በሀገራችን ቤተመንግስት ገብቶ ስልጣን ላይ ያለ እስካሁን በህዝቡ መሃል በነፃነት ተንቀሳቅሶ እንደተወደደ ከስልጣን የወረደ የለምና፡፡ በአሁን ሰዓት ደግሞ ማንም ሰው ለመሞትና መከራ ለመቀበል እፀ በለስ የሚበላ የለምና፡፡ በዚህም ያልተደፈረው ገነት ተደፈረ፤ ስንቶች በአጠገቡ ሲያልፉ እንኳ ፊታቸውን ወደግቢው እንዳያዞሩ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረግባቸው እንዳልነበረ ሁሉ ዛሬ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሰልፍ ተጎበኘ፡፡ በዚህም ሞተው ዴሞክራት የሆኑ ይመስላል፡፡

የመርዶው ሕዝባዊ ምላሽ – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

Dr. Dagagnachewየዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጂ  በኢትዮጵያ እንዳይነበብ በታገደው የዞንዘጠኝብሎግ ላይ ይገኛል፡፡እኛም ለጋዜጣ በሚመች መልኩ አሰናድተነዋል
የዞን ዘጠኝ ጦማር ጽሁፉን የሚጀምረው በዚህ መልኩ ነው፡፡ በአዲስ አበባ ዪኒቨርስቲ የፍልሰፍና መምህርና ከጥቂት የአደባባይ ምሁራን አንዱ የሆነውን ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋን አነጋግረን ስለወቅቱ ማሕበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የተለያዩ  ሐሳቦችን ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ አሁን ደግሞ የአቶ መለስን ‘ድንገተኛ!?’ ሞት  ተከትሎ በድኅረ-መለስ  አትዮጵያና በሌሎች ተያያዥ ጉዳየች ዙሪያ እንደተለመደው ገዢ ሐሳቦቹን ሰጥቶናል፡፡ መልካም ንባብ
የመርዶው ሕዝባዊ ምላሽ
እንደሚታወቀው ለሀያ አንድ ዓመታት በሙሉ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥኑን መስኮት አጣበው  የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ናቸው፡፡ እንዲሁም በከፍተኛ ሁኔታ ተክለ ስብዕናቸውና ስራቸው በሚዲያው ሲገነባላቸው ከቆዩ በኋላ የጠቅላይ ሚኒስተሩን ድንገተኛ  ህልፈተ ህይወት ህዝቡ ሲሰማ  ድንጋጤና ሀዘን ተፈጥሮበታል፡፡ ይህንንም የህዝብ  ሀዘን በሁለት አቅጣጫ ልናየው እንችላለን፡፡ የመጀመሪያው አስከሬናቸው ከውጭ ሀገር በገባበት ምሽት ከተጠበቀው በላይ ህዝብ ወጥቶ ብሶቱንና ሀዘኑን የገለፀበት ነው፡፡ ምናልባትም ህዝብ ላሳየው የሐዘን ጎርፍ አንድ ወሳኝ የሆነ ነገር መገንዘብ የምንችለው ህዝቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ፓርቲው ከሚያራምደው የጎሳና የነገድ ፖለቲካ ውጪ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊና እንደግለሰብ አይቶ እንዳዘነላቸው ለመረዳት አያስቸግርም፡፡ በተጨማሪም  እሳቸው በህይወት እያሉ ለያይተው ያዩት ህዝብ ሲሞቱ ግን እርስ በርስ ሳይለያይ በህይወት እያሉ ያላያያዙትን ህዝብ በሞታቸው ሊያያይዙት ችለዋል፡፡

አቶ መለስ ከፍትሕ አመለጡ – ከዳዊት ፀጋዬ

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለፍርድ ቢቀርቡ ኢትዮጵያ ቀን ወጣላት ብዬ አምን ነበር፡፡ የግብፅ ፕሬዘዳንት የነበሩት ሆስኒ ሙባረክ እስከዛሬ ፍርድ ቤት እየተመላለሱ የሚገኙት በ180 ሰዎች ግድያ ተጠያቂ ናቸው በሚል ተከሰው ነው፡፡ እኛም አገር በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ምክንያት በተፈጠረው ቀውስ መንግስት ራሱ ባመነው መሠረት የ200 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡ በእውነት የሕግ የበላይነት ሰፍኖ ቢሆን ኖሮ አቶ መለስ በእነዚህ ሰዎች ግድያ ብቻ ፍትሕ አደባባይ በቆሙ ነበር፡፡ ሕጉ ቢፈርድባቸው ወይም ነፃ ቢለቃቸው እንዴት ደስ በተሰኘሁ፡፡ ምክንያቱም የእኔ ዋናው የደስታዬ ምንጭ የሕግ የበላይነት በአገሬ ተከብሮ ማየት ነው፡፡

ገና በጠዋቱ ጠ/ሚኒስትሩ ታመሙ ሲባል ነበር የፈራሁት፡፡ ከወዳጆቼ ጋር ተቀምጠን ስንጫወት “እኔ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሞቱ በጣም ነው የምናደደው፡፡ በሕይወት ኖረው በፍትሕ አደባባይ እንዳያቸው እናፍቃለሁ ያኔ አገሬ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደተሻገረች አምናለሁ፡፡ መሪዋን በሕግ መዳኘት ችላለችና” የዘንባባ ዝንጣፊ ነበር ያልኩት፡፡ ግና የፈራሁት አልቀረም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞቱ፡፡
ምርጫው ተጭበርብሯል በሚል የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ለተቃውሞ አደባባይ በወጡ ልጆች ላይ ታንክ በማሰማራት በአልሞ ተኳሾች ሕይወታቸው የተነጠቀውን የአገሬ ታዳጊዎችና አባወራዎች ደም ዛሬም ከምድር ወደ ሰማይ ይጮሀል፤ የፍትህ ያለህ ይላል፡፡ የተከበሩ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለአዲስ ጉዳይ መፅሄት በነሐሴ 19 እትም በሰጡት ምላሽ ያንን መራራ ወቅት እንዲህ ነበር ዕንባ እየተናነቃቸው የገለፁት፡፡ “እሳቸውን ሳስታውስ በ1997 የሞቱትን ሰዎች አስታውሳለሁ፡፡ እኔ እንግዲህ ኦሮሞ እንደመሆኔ የመጣሁበትን ሀገርና ሰዎችን ነው የማስታውሰው፡፡ በ97 በወለጋ ጦርነት ነው የተከፈተው፡፡ ይህንን ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡ በዚህም ብዙ ሰዎች ሞተዋል፡፡ ብዙ ሰዎች አዝመራቸው ተቃጥሎባቸዋል፡፡ የሚበሉት ምግብ እንኳ አልነበራቸውም፡፡ የእኛ ፓርቲ መኪናዎችን ተከራይቶ ቦታው ድረስ በመጓዝ ነው ምግብ ያደረሰንላቸው፡፡ ምናልባት ዳቦና ሻይ ከማግኘታቸው ውጭ ፊታቸው አሳዛኝ ገፅታ ለብሶ ነበር፡፡ አሁን የምናገረው ስለማውቃቸው ስለ ኦሮሞ ህዝቦች ነው እንጂ ሌሎች ክልሎችም የዚህ ገፈት ቀማሽ እንደነበሩ ሰምቻለሁ፡፡ በ1997 ዓ.ም የደረሰው መጉላላት ስቃይ እስራትና ሞትን መርሳት አልችልም፤ እስከ ዕለተ ሞቴ፡፡ አንዳንድ ፈረንጆች ውስጣችንን በደንብ የሚያውቁ ስለ ጠ/ሚኒስትሩ መልካም ነገር ሲናገሩ ላዳምጥ አልቻልኩም፡፡ ፓርቲዬም አልቻለም፤ ኦሮሞዎችም አልቻሉም፤ ይህንን ስል ዕንባ እየተናነቀኝ ነው” በማለት ነበር የልብ ስብራታቸውን የገለፁት፡፡

ሀይለማርያም ደሳለኝ የመለስ ዜናዊን ያህል ብቃት ስለሌላቸው ምክትሎች ያስፈልጓቸዋል ተባለ - ሪፖርተር



የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን የቀብር ሥርዓት በብሔራዊ ደረጃ ፈጽሞ በዚህ ሳምንት ለሥልጣን ሽግግር ቀጠሮ የያዘው ኢሕአዴግ፣ የምክር ቤቱን ስብሰባ ሰሞኑን ያደርጋል፡፡ በአገሪቷ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር በሕዝቡና በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጉጉት ፈጥሯል፡፡

በሳምንቱ መገባደጃ ላይ የሚደረገው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ የኢሕአዴግ ሊቀመንበርንና ምክትል ሊቀመንበር የሚመርጥ ሲሆን፣ የግንባሩ ሊቀመናብርት በመንግሥት መዋቅር ደግሞ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ፡፡ በዚህ መሠረት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የግንባሩ ሊቀመንበርና የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆኑ እየተጠበቀ ነው፡፡ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንነት ግን እስካሁን በይፋ አልታወቀም፡፡

EPRDF promotes 37 officers to rank of Major Generals and Birg. Generals


.24 Tigrians the rest 13 dual ethnic

Here is the list of the latest round of appointments.
I. The officers promoted from the rank of brigadier general to major general are:
✪ Brig. Gen. Mehari Zewdie
✪ Brig. Gen. Hassan Ibrahim
✪ Brig. Gen Melese Beleete
II. The officers promoted from the rank of colonel to brigadier general ase:
1. Col.Yayne Seyoum
2. Col. Ataklti Berhe
3. Col. Fesseha Beyene
4. Col. Guesh Tsige
5. Col. Gebrekidan Gebremariam
6. Col. Maesho Hagos
7. Col. Gebru Gebremichael
8. Col. Mashesha Gebremichael
9. Col. Abreha Aregay
10. Col. Degife Bidi

Proof of Hoax in Ethiopia


SVT can now reveal that the videos that the Ethiopian government used as evidence of the arrest of the Swedish journalists is staged. Our sources even claim that the video was shot two days after Johan Persson and Martin Schibbye were arrested.

ወያኔ ለ34 ኮለኔሎችና ብ/ጄነራሎች ከፍተኛ ማዕረግ ሰጠ፤ (የሹመቱ የብሔር ተዋጽኦን ይዘናል)

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ፕሬዚዳንቱ ወታደራዊ ሹመት ይሰጣሉ ይላል። ሆኖም ግን በሞተ ጠቅላይ ሚኒስትር እስካሁን እየተመራን በምንገኝበት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ህገመንግስት መሰረት 34 ኮሎኔሎች በብራጋዴር ጄነራል ማዕረግ ፣ ሶስት ብራጋዴር ጄነራሎች ደግሞ በሜጀር ጄነራል ማዕረግ ተሹመዋል፡፡ በሹመቱ ላይ የተሰተዋወለው የብሔር ተዋጽኦ አሁንም እጅግ አነጋጋሪ እንደሆነ ነው።
በተሰጠው ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት መሰረት



ብራጋዴር ጄነራል ሆነው የተሾሙት:-
– ብራጋዴር ጄነራል ያይኔ ስዩም፣ – ብሔር ትግሬ
- ብራጋዴር ጄነራል አታክልቲ በርሄ ፣ – ብሔር ትግሬ
- ብራጋዴር ጄነራል ፍስሃ በየነ፣ – ብሔር ትግሬ
– ብራጋዴር ጄነራል ጉዕሽ ፅጌ ፣ – ብሔር ትግሬ
– ብራጋዴር ጄነራል ገብረኪዳን ገብረማሪያም፣ – ብሔር ትግሬ
- ብራጋዴር ጄነራል ማዕሾ ሃጎስ፣ – ብሔር ትግሬ
- ብራጋዴር ጄነራል ገብሩ ገብረሚካኤል፣ – ብሔር ትግሬ

Tuesday 11 September 2012

አንድነት ፓርቲ ብርሃንና ሰላም በህገ ወጥ መንገድ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣን አላትምም ማለቱ ሕገ ወጥ ነው አለ

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት
ከነብዩ ኃይሉ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ፡-
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ልሳን የሆነችው እና በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ የነፃ ጋዜጦችን መታፈን፣ መመናመን እና ድፍረት ማጣት ተከትሎ ዘወትር ማክሰኞ ጠንካራ የፖለቲካ ትንታኔዎችንና ዜናዎችን በመያዝ ለህትመት የምትበቃው ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ብርሃንና ሰላም የህግ አግባብ በሌለው ውሳኔ አላትምም ማለቱ ህገ ወጥ በመሆኑ በአስቸኩዋይ ይታረም ሲል የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አስታወቀ፡፡
ለህትመት ከበቃችበት ጊዜ ጀምሮ በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን በማትረፍ ተናፋቂ ለመሆን የበቃችው ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እንዳትታተም በብርሃንና ሰላም የታገደችበት ሁኔታ ከጠ/ሚ መለስ ሞት ጋር የሚያያዝ ሲሆን ጋዜጣዋ የፖቲካ ፓርቲ ልሳን እንደመሆንዋና ፓርቲው ደግሞ ያለበትን ሃገራዊ ሃላፊነት ለመወጣት የጠቅላይ ሚንስትሩን ሞት ተከትሎ በሃገሪቱ የፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ምን መልክ እንደሚኖራቸው የሚያሳይ የፖለቲካ አመራሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የጋዜጣዋ ክፍል ባልደረቦች የፃፉዋቸውን ትንታኔዎች በልዩ ዕትም ዓርብ ነሐሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም ለንባብ ማብቃቱ የሚታወስ ነው፡፡ በመቀጠልም ማክሰኞ በመደበኛ ቀንዋ ጋዜጣዋ ለአንባቢያን የደረሰች ሲሆን፡፡ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ተከትሎ ጠንካራ ሃሳብ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን ለማስተናገድ እንደገና ዓርብ ነሐሴ 25 ቀን 2004 ዓ.ም  የጋዜጣ ክፍሉ በመረባረብ ስራውን አጠናቆ ነበር፡፡ ይሁን እንጅ እንደተለመደው ገንዘብ ለመክፈል የህትመት ክትትል ሰራኛው ሲሄድ እንዳይታተም ታግዷል በማለት መልሰውታል፡፡

“ማኅበረ ቅዱሳን” ፓትሪያሪክ መርቆሪዮስን እንደማይቀበል አቋሙን በይፋ አሳወቀ

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል 
ያለውንበመቅበር የሌለውን በመጥራት የሚታወቀው የጥቁር ራስ ስብስብ የሆነውን “ማህበረ ቅዱሳን” በጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲሁም በቤተ መንግሥት አከባቢ የታየውን ድንገተኛ ክስተት አጥፍቼም ብሆን እጠፋለሁ እንጅ ይህን ወለል ብሎ የተከፈተ በርስ ሳልጠቀመት አያልፈኝም!የሚል ሞፈክር አነግቶ በሀገሪትዋ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ እንደቀዳዳ በማየትና ቀዳውን በማስፋት በዚህ ማኸልም ሸልኮ በመውጣት ያልተጠራበት ዙፋን ለመጠቅለል በስውርም በይፋም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቀን ከሌሊት ሴራውን እየሸረበና እየዶለተ እንደሚገኝ ምንም አያጠያይቅም።
ባሳለፍነው ሳምንት ሽብርና ህውከት በሚነዛባቸው መካነ ድሮቹ አመካኝነት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ የት ነዎት?ሲል ሳይጠራ አቤት ሳይላክ ወዴት አንደማለት ያልተጠየቀውን ሲያመናታ ሲሳለቅ በሌላውኛው እጁ (በህጋዊው ድረ ገጾቹ) በኩል ደግሞ ቤተ ክርስቲያንና የፓትርያርክ ምርጫ” በሚል ርእስ ቀደም ሲል ማኅበሩ አሁን በሚጥራበት ማኅበረ ቅዱሳንየሚለው ስያሜ ከመያዙ በፊት አጠቃላይ ጉባኤ ተብሎ ይታወቅበት በነበረበት ዘመን ገድሎ የቀበራቸው ፓትሪያሪክ ቴዎፍሎስ እንዲሁም ያለ አንዳች ተጨባጭ ማስረጃ ርዕሰ መናፍቃን በማለት የሚወቅሳቸውን ፓትሪያሪክ መርቆሪዮስ አሁን ደግሞ ሆን ብሎ ቀድሞም በእግዚአብሔር ፈቃድ ያልተሾሙ ናቸውሲል በመዋቹ ቅዱስ ፓትሪያሪክ ጳውሎስ ምትክ መንበሩ የሚገባው ለፓትሪያሪክ መርቆሪዮስ ነው! የሚል ከየአቅጣጫው እየገፋ እየመጣ ያለውን የአብያተ ክርስቲያናት ድምጽና ለቤተ ክርስቲኒቱ ሰላም: ለተከታዮችዋ ምእመናን ደግሞ አንድነትንና ፍቅር በብርቱ የሚሹ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ምልከታ ለማሳጣት ብሎም ዕርቀ ሰላሙንም ለማደናቀፍ ይህን አደረገ።
ከእኛ ፓትርያርኮች ሁለቱ ከምንኩስና አንዱ ከአጠቃላይ ጳጳስ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ሀገረ ስብከታቸውን ትተው የተሾሙ ናቸው። እነዚህም አቡነ ቴዎፍሎስና አቡነ መርቆሬዎስ ሲሆኑ በጣም የሚያስገርመው በእነዚህ በሁለቱም ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ፈተናዎች ከማስተናገዷም በላይ የሁለቱም ዘመነ ፕትርክናቸው አጭር ነበረለራሳቸውም ሆነ ለቤተክርስቲያኒቱ ጥቁር ነጥቦች የተቀመጡትም በእነርሱ ዘመን ስለሆነ ከትውፊት መውጣታችን ባናስተውለውም እግዚአብሔር አምላካችን አልፈቅድላችሁም ያለን ይመስላል1

በኢትዮጵያ ባንኮች በጠቅላላ የውጭ ምንዛሪ እጥረት በከፍተኛ ደረጃ በመከሰቱ ደንበኞቻቸውን ማስተናገድ እንደተሳናቸው ተዘገበ

ጳጉሜን ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ሪፖርተር፦”የዶላር ያለህ!” በሚል ርዕስ ባጠናቀረው ዘገባ የውጪ ምንዛሬ እጥረቱ ከተከሰተ የሰነበተ ቢሆንም፤ በአሁኑ ጊዜ ግን ችግሩ የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱን አመልክቷል።
ከወራት በፊት በቂ የውጭ ምንዛሪ ያለ መሆኑ ቢገለጽም፣ አሁን በተጨባጭ የሚታየው እውነታ ግን በተቃራኒው ሆኗል-ብሏል ጋዜጣው።
የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት የባንኮችን ደጃፍ የሚረግጡ  አስመጪዎች፤ <ሌተር ኦፍ ክሬዲት> ለመክፈት እና
ማስመጣት የሚገባቸውን ምርት ለማምጣት ባለመቻላቸው፤ ሥራችን እየተስተጓጐለ ነው በማለት እያማረሩ ነው::
ባንኮች ደንበኞቻቸውን ማስተናገድ ባለመቻላቸውም ዶክመንቶቻቸውን ተቀብለው <ወረፋ ጠብቁ> ከማለት ወጪ ወረፋው መቼ እንደሚደርሳቸው እንቆቅልሽ ሆኗል ያለው ጋዜጣው፤ ችግሩ ቀስ በቀስ ከፍተኛ የሆነ ተፅዕኖ እያሳረፍ ለመሆኑ አንዳንድ ምልክቶችም እየታዩ ናቸው”ብሏል።
ትልቁ የአገሪቱ ባንክ  የሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሳይቀር፤ ከግል ባንኮች የተሻለ የውጭ ምንዛሪ አለው ቢባልም፣
ለግለሰቦች የውጭ ምንዛሪ ጥያቄ አዎንታዊ መልስ ሊሰጥ አልቻለም።
ጋዜጣው እንዳለው፤በግል ባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሪ ድርቅ ፤ለባንኮቹ ሳይቀር ራስ ምታት ሆኗል::
ረዥም ተራ በመጠበቅ በሚገኘው ዕድል እንኳን  የሚሰጠው የውጭ ምንዛሪ አነስተኛ በመሆኑ፣ ለዕለት ፍጆታ የሚሆኑና አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ምርቶችን አስመጥቶ ወደ ገበያ ለማስገባት አልተቻለም::
<በዚህን ወቅት ለምን የዶላር እጥረት እንደተፈጠረ  ግልጽ አለመሆኑም ብዙ ሊያነጋግር ይችላል፤ ችግሩ
በግልጽ የመታየቱን ያህል -መፍትሔ ለመስጠት እየተደረገ ያለው ጥረት ምን እንደሆነ አይታወቅም::”ብሏል ጋዜጣው።
አክሎም፦”ችግሩ ጊዜያዊ ነው እንዳይባል፤ ችግሩ ማጋጠም  ከጀመረ ሳምንታት ሳይሆን ወራት ተቆጥረዋል። መቆሚያው መቼ እንደሆነም ለመተንበይ እንኳን አልተቻለም:: ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የመንግሥት አካልም በውጭ ምንዛሪ ዙሪያ የተፈጠረውን ክፍተት  አስመልክቶ ምንም ዓይነት መረጃ እየሰጠ አለመሆኑ፣ ችግሩ ነገም ሊቀጥል ይችላል የሚል ስጋት እያሳደረ ነው::”ብሏል።

ሀገሪቱን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋራ ይመሯታል ተባለ

ጳጉሜን ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በመስከረም ወር 2005 ዓ.ም የኢህአዴግ ምክር ቤት በአቶ መለስ ዜናዊ ምትክ በሚያካሂደው ምርጫ የሚመረጠው
ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ድርጅቱን ለስድስት ወራት ብቻ በጋራ እንደሚመሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን የግንባሩ
ጽ/ቤት ኃላፊ አስታወቁ፡፡
አቶ ሬድዋን ዛሬ ከወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የግንባሩ መተዳደሪያ ደንብ ቀጣዩ ጉባዔ
ከሁለት እስከ ሁለት ዓመት ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ ይካሄዳል በሚለው መሰረት ቀጣዩ ጉባዔ ከስድስት ወራት በኃላ
እንደሚካሄድ ጠቁመው እስከዚያ ከአራቱም አባል ድርጅቶች 45 ሰዎች በድምሩ 180 አባላት የተወከሉበት የግንባሩ
ም/ቤት በተጓደሉት አባላት ምትክ ግንባሩን “በጋራ የሚመሩ” ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ይመርጣል
ብለዋል፡፡
“ከስድስት ወራት በኃላ የግንባሩ ጉባዔ ሲካሄድ ሊቀመንበሩና ምክትል ሊቀመንበሩ ብቻ ሳይሆን የሥራ አስፈጻሚና
የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትም ሥልጣናቸውን ያስረክባሉ፡፡ከማንኛውም አባል ጋር ወርዶና የጉባዔው አባል ሆኖ ከተመረጠ
ይመረጣል፡፡እስከዚያው ግን የሊቀመንበርነት ቦታ ተጓድሎአል፡፡ተጓደለውን ቦታ የሚመርጠው ጉባዔው ሳይሆን ምክርቤቱ
በመሆኑ በዚሁ መሰረት በመስከረም ወር ይመርጣል፡፡ቀጣይ ስድስት ወር ሲሞላ አዲሱ ሊቀመንበር ሌላ የጉባዔ አባላት
ይሆኑና እንደገና ምርጫ ተደርጎ የሚመረጡ ከሆነ ይመረጣሉ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

Sunday 9 September 2012

በከፍተኛ ደረጃ በሙስና የሚታማው ያራ ለአቶ መለስ የሰጠው ሽልማት እየተጣራ ባለበት ሰአት ለዶክተር እሌኒ ሸለመ!!! ጉድ ነው

 ዶክተር እሌኒ ከያራ ያገኙትን ሽልማት ለበጐ አድራጐት ድርጅት ማቋቋሚያ ሊያውሉት ነው
በዳዊት ታዬ
የኢትዮጵያ የምርት ገበያ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር እሌኒ ገብረ መድህን በግብርና ግብዓት አምራችነቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚታወቀው ያራ ፋውንዴሽን የዘንድሮ ተሸላሚ በመሆን የተበረከተላቸውን 30 ሺሕ ዶላር ለታዳጊ ሴቶች በጐ አድራጐት ድርጅት ማቋቋሚያ እንደሚያውሉት ገለጹ፡፡
ዶክተር እሌኒ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ 30 ሺሕ ዶላሩን ለታዳጊ ሴቶች ድጋፍ ለማድረግ እንዲወስኑ ያደረጋቸው በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል ታዳጊ ሴቶች ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳይሸጋገሩ ትምህርታቸውን የሚያቋርጡባቸው አጋጣሚዎችን በመመልከታቸው ነው፡፡

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ታዳጊ ሴቶች የወንዶችን ያህል ዕድል ኖሯቸው ትምህርታቸውን ለመግፋት ብዙ ሳንካ ያለባቸው በመሆኑ፣ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊገቡ ይችሉ የነበሩ ሴቶች ቁጥር እንዲቀንስ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ እንዳለውም ያስታውሳሉ፡፡

ለታዳጊ ሴቶች ሊሰጥ የሚችለውን ድጋፍ በቋሚነት ለማስቀጠልም 30 ሺሕ ዶላሩ እንደመነሻ በማድረግ አንድ የበጐ አድራጐት ማዕከል የሚያቋቁሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉም በተመረጡ የክልል ከተሞች ውስጥ ጽሕፈት ቤት ኖሮት የሚሠራ ሲሆን፣ ሥራው በቋሚነት እንዲቀጥል ለማድረግ ደግሞ ሌሎች ዕርዳታ ሰጪና ስፖንሰሮች እንዲካተቱበት ይደረጋልም ብለዋል፡፡