Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 7 April 2012

ትንሽ ፉገራ፤ ተዋናይ እንፈልጋን…

ይህው እንግዲህ ፆም ሊፈታ ነው። ተስፋዬ ካሳ በአንድ ቀልዱ ላይ ሁለት ችግር ያላቸው…! (“ር”ን ረዘም ያድርጉልኝ) እናም ሁለት ችግርርርር … ያላቸው ባልና ሚስቶች ብላችሁ አንብቡልኝ፤ ስለ ፆም ፍቺ ያወሩትን እንዲህ ነግሮን ነበር፤
ሚስት “እንግዲህ አሁን ፆሙ ሊፈታ ነው። ምን ይሻለናል?” ብላ ትጠይቀዋለች።
ባል ታድያ ምን አላት፤ “አይዞሽ ሌላ ፆም እንይዛለን” ብሎ “አፅናናታ”
ተስፋዬን ደግሞም ደግሞም ነብሱን ይማርልን!
አሁንም ፆም ሊፈታ የቀሩት ጥቂት ቀናት ናቸው። ገና አመት በዓሉ ሳይቃረብ የጀመረው አስማታዊ የዋጋ ውድነት አሁንም ከልካይ አላገኘም። ከሳምንት በፊት የአዲሳባ ወዳጆቼ እንደነገሩኝ ከሆነ ዶሮ፣ ቅቤ፣ በግ እና አጠቃላይ የአመት በዓል “አክሰሰሪዎች” ዋጋ ሰማይ ነክቷል።
ለምሳሌ ዶሮ አንድ መቶ ሰማኒያ ብር ቅቤ አንድ መቶ ስድሳ ብር ከገቡ ቆይተዋል። አሁን ደግሞ በዓሉ ሲቃረብ  ስንት ይገባሉ የሚለውን ሸማች ይወቀው።
እንግዲህ አመት በዓልን አመት በዓል የሚያደርጉት በርካታ ነገሮች አሉ። እንደ አስተያየት ሰጪዎች ከሆነ “በአሁኑ ግዜ ከአመት በዓል እሴቶቻችን ውስጥ የቀረን “ሞቅታ” ብቻ ነው” ሲሉ ይደመጣሉ። እርሱም በማር ጠጅ የመጣ ሞቅታ አይደለም፣ በገብስ ጠላም የተፈጠረ አይደለም… (እነርሱማ የት ተገኝተው…!?) እንግዲያስ ከወዴት የመጣ ሞቅታ ነው…? ያሉ እንደሆን፤ እንክርዳድ የበዛው ኑሯችን ያመጣብን፤ በዓል አዘቦት የማይለይ ሞቅታ ነው ይሉዎታል።
እናም የዘንድሮን በዓል በርካቶች ሳይበሉ ሳይጠጡ ብስጭት ባመጣው ሞቅታ ለማለፍ ተገደዋል እያሉ የሚያወጉ በርክተዋል።
“ማማረር ምናባቱ!” ያሉ የፈጠራ ክህሎት የታደሉ ነዋሪዎች ደግሞ የአመት በዓል ደስታዎችን ለማግኘት የሚያስችል ዘዴ ሲያስቡ ሰንብተው አንድ ማስታወቂያ ማውጣታቸውን ሰምቻለሁ። የስራ ማስታወቂያ ነው ነገሩ። እንዲህ ይላል።
የስራ ማስታወቂያ
የስራው መደቡ መጠሪያ ….. ተዋናይ
የትምህርት ደረጃ…….  የፈለገው ይሁን
የስራው መግለጫ አንድ
እንደ ዶሮ እና በግ የሚተውን፤ መኖርያ ቤታችን እስከ ዛሬ ድረስ መጣ የተባለውን አመት ባዕል በሙሉ በተቻለ አቅም፤ ዶሮ ሳይታረድ ጠቦት ሳይጣል አልፎ አያውቅም ነበር። ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን እነዚህን ማሟላት አልተቻለም። ቢሆንም ግን፤ በመኖርያ ቤታችን ቢያንስ ቢያንስ  የዶሮ እና የበግ ድምፅ መሰማት አለበት ብለን ቆርጠን ተነስተናል። ስለሆነም አመልካቾች የዶሮ እና የበግ ድምፅን አመሳስሎ በመጮህ ለመሮሪያ ቤቱ ድምቀት መስጠት ይጠበቅባቸዋል።
(ስራው ትልቅ የማስመሰል ጥበብ የሚፈልግ በመሆኑ ባለፈው ግዜ በልማታዊው እግር ኳስ ላይ የተሳተፉ አርቲስቶች ይበረታታሉ!)
የስራ መግለጫ ሁለት
እንደ ዘመድ ሆኖ የሚተውን፤ ከዚህ በፊት በነበረን ልምድ ለአመት ባዕል በመኖሪያ ቤታችን ዘመድ ተሰባስቦ በልቶ፣ ጠጥቶ ሙያችንንም አድንቆ ይሄድ ነበር። ዘንድሮ ግን ዋናዎቹ ዘመዶቻችን በቤታችን ምንም እንደሌለ እና ገበያውንም ደፍረን እንደማንሸምት ይረዱታል ብለን እናምናለን! ይህንን ሁሉ ችላ ብለው እንኳ ቢመጡ ተሳቀው ከመመለስ ውጪ ቀድሞ የለመዱት አይነት መስተንግዶ ለማድረግ አቅም የለንም።  በመሆኑም እንደ ዘመድ ሆኖ የሚጫወት ተዋናይ ማግኘት አስፈላጊ ሆኗል። አመልካቾች ምንም ሳይበሉ ሰይጠጡ ጎረቤት ጉድ እስኪል ድረስ የቤታችንን ሞያ እያደነቁ ድምፃቸውን ከፍ አድወርገው ማውራት ይኖርባቸዋል። ከቤት በሚወጡ ግዜም አረማመዳቸውም ሆነ ጨዋታቸው “እሁድ የቁብ ጠላ ስለጋ ስለጋ…” እንደሚለው ዘፋኝ መሆን ይጠበቅበታል።
አመልካቾች ለመመዝገብ በሚመጡበት ግዜ ለበዓሉ ማድመቂያ የማይመለስ፤ ቄጤማ፣ ጠጅ ሳር፣ እንዲሁም እንደ እጣን የመሳሰሉ ጢሳጢሶችንም ይዘው እንዲመጡ ይመከራሉ።
የደሞዝ ሁኔታ…
ውይ ለካ ይሄም አለ… በቃ ተዉት እንደሚሆን እንደሚሆን እናልፈዋለን!

Amhara expelled from southern Ethiopia

by Argaw Ashine

Ethiopia’s Southern Region government has over the past two weeks expelled more than 20,000 ethnic 

Ethiopia's Southern Region government has over the past two weeks expelled more than 20,000 ethnic Amhara settlers, it can be revealed. Amhara settlers, it can be revealed.
The regional authorities reportedly ordered the settlers to return to their ‘home’ in Bench-Maji Province.
Southern Region Governor Shiferaw Shigute declined to comment on the issue, while his aide said the regional government was not aware of the expulsion.
However, a letter obtained by this reporter indicated that Mr Shiferaw had ordered the eviction to prevent the Amhara from dominating the region.
The local government also confiscated the Amhara’s farmland and property and paid them a meagre $3 (50 Birr) for lunch during their departure.
Thousands of evicted residents arrived in Addis Ababa and the authorities kept them on separate compounds, while some 600 others were taken to a location some 130km out of the capital.
Ethnic Amhara settled in the Southern Region 20 years ago, mostly as labourers, but were later permitted by the local government to own land and property.
The Amhara, reputed as a powerhouse of Ethiopian politics, form about 26 per cent of the country’s population and are estimated to be around 20 million.
Ethiopia’s Southern Region is home to over 50 minority groups and often experiences sporadic ethnic tensions over resources and power.

እስቲ ወደኋላ በትዝታ ልመልሳችሁ………..

ያልተላከው ደብዳቤ
በተወዳጁ አደም ሁሴን

እስቲ ወደኋላ በትዝታ ልመልሳችሁ………..መቼም በወጣትነት በተማሪነት ወቅት እንደየ ጊዜና ዘመኑ የማይረሳ ጣፋጭና አስገራሚ የህይወት ገጠመኝ እንደምናሳልፍ እገምታለሁ ወይም ብጠረጥ የሚደንቅ አይመስለኝም፡፡
የኔን የተማሪነት ዘመን እናውጋ……አንድ ገርል ፍሬንድ እንዲኖርህ ትፈልጋለህ እንበል ቀትታ ሄዶ ማነጋገር ነውር ነው ወይም ደግሞ የሚደፍርም የለም እሷስ ብትሆን ስታናግርህ አይደል……….! እናም እንዴት እንደምታናግራት ሊጨንቅህ ይችላል እናም በወቅቱ በሰፊው የተለመደው ደብዳቤ መጻፍ ነው የፍቅር ደብዳቤ እሱንም ቢሆን አዋቂ፤ምርጥ ጸሀፊ መሆን ይጠይቃል፡፡ማንም ተነስቶ ደብዳቤ አይጽፍም……የወደድካት ልጅ ልቧ እንዲራራ፤ያንተ እንደስትሆን ከፈለክ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ቃላት መምረጥ አለብህ፤ጥቅስ መደርደር፤አባባሎችን መጠቀም ፤አበባ መሳል ፤ልብ ቅርጽ ላይ ጦር ሰክተህ ደም ማንጠባጠብ አለብህ ቢቻል ከደብዳቤው ጋር ደስ የሚል የህንድ ፖስት ካርድ ይሄ ሀሚት አፕ አቻ ከቆንጆ ሚስቱ ጋር ያለበትን ከጀርባው ከ ኤስ ለ ቲ ብለህ ጽፈህ…… ፡፡ በቃ ምን አለፋህ ጥንቃቄ የተሞላበት ጽሁፍ ካልሆነ የልጅቷን ልብ አራራለሁ ብለህ ጭራሽ ልቧን አምርረኅው ቁጭ ትላለህ፡፡
አንድ የትምህር ቤት ጓደኛ ነበረኝ የፍቅር ደብዳቤ በመጻፍ የሚታወቅ እሱ የጻፈው ደብዳቤ የደረሳት ተፈቃሪ ልቧ የማይራራ የለም እውነት ይገርመኛል ሀሪፍ ጸሃፊ ነው በቃ ፍቅር ሲይዝህ እሱ ጋር መሄድ ነው፡፡ ከዛ ልክ ሀኪም ዘንድ ወይም አጥፍተህ ዳኛ ዘንድ እንደቀረበ ጥፋተኛ ትናዘዛለህ ውይም ችግርህን ታወያየዋለህ፡፡
#ምኗን ነው የወደድካት?; ይልሃል ፡፡ በቃ ትንሽ ማፈርህ አይቀርም ትሽኮረመማለህ….ግን ፍቅረኛህን ከማጣት አይበልጥምና ትናገራለህ፡፡ ይገርመኝ የነበረው ይሄ ጓደኛዩ ሲጠይቅህ ኮስተር ብሎ ነው በስሜት ተውጦ ያዳምጥሃል፡፡ አንተም ትናዘዛለህ…………
#እሷን እያየሁ እያሰብኩ ምግብ አልበላ ውሃ አልጠጣ አለኝ አማርኛ ትምህርት አረብኛ ሆነብኝ፤ እሷን ሳይ መራመድ አቃተኝ ትንሽ ጠጠር እንቅፋት እየመታኝ ይህው እግሬ ተላላጠ
ወዘተ…..; ትነግረዋለህ እሱም አዳምጦህ ሲጨርስ የራሱን ጥበብ መጠበብ ይጀምራል፡፡
(እናንተስ የፍቅር ደብዳቤ ጽፋቹ አታውቁም?)…….. በነገራችሁ ላይ አንድ የተባረከ ዳዊት ዋሲሁን የተባለ ወዳጄ እዚሁ ፌስ ቡክ ላይ ነሸጥ ሲያደርገኝ የምለጥፈውን ሙከራዎች እያደነቀ እያደነቀ ቆየና
#በዚህማ መቅረት የለመትም;
ብሎ ዌብ ሳይት ከፈተልኝ መቼም እውቀትህ ይባረክ በሉልኝ አንድ ቀን ስለዚህ ሰው አንድ ነገር ማለቴ አይቀርም የሆነው ሆኖ መልካም ፈቃዳቹ ከሆነ እንዲህ በትነሽ በትንሹ ቡጭቅ ቡጭቅ እያደረኩ ከማሰቃያቹ እዛ ላይ ሙልውን እንድታነቡ ልጋብዝ adamhussen.blogspot.com ብላችሁ እዩት ፡፡
! ! !
ደረጀ ፍቅሩ የሚባል ወዳጅ አለኝ መቼም ታውቁታላችሁ (ስርየት) የሚባል ፊልም ደራሲ ነው (ጋጋ) የሚባል አስፈሪ ገጸ ባህሪ የሚተውንበት
#አዲስ አበባ ደበረኝ;
ሲለኝ ና እለውና ይመጣል ያለሁበት ሀገር እንገባበዛለን ቀዝቀዝ ያለ ቢራ እየጠጣን እንጨዋወታለን የማይነሳ የማይጣል ነገር የለም ሲበዛ ቀልደኛ ነው ጨዋታ ያውቃል የደረስኩትን የተወንኩበትን ፊልሜን እይልኝ አለና ጋበዘኝ በደስታ አየሁት፡፡ በቃ ከዛን ጊዜ በኋላ የአማርኛ ፊልም አይቼ አላውቅም የራሴ ምክንያት አለኝ በቀደም ግን እንዲሁ ከአንድ ወዳጄ ጋር በዚሁ ጉዳይ ስንነጋገር (ውይይታችን ይቆይ………. ፊልሞችን ግን ልጋብዛችሁ)
 

Friday 6 April 2012

UDJ says political repressions escalated

April 04, 2012 (ESAT News):
Even though Ethiopian Federal Democratic Unity Forum (UDJ) called a meeting for March 31, 2012 in a pre arranged hall of Mugger Cement Factory near Gotera, the party was denied the use of the hall at the last minute. Since the owner refused to rent the hall, the scheduled discussion regarding the ever rising cost of living and the new lease proclamation has been cancelled.  The chairperson of UDJ, Dr. Moga Ferissa indicated that the meeting was approved by the government and the rent for the hall paid, but the meeting could not go ahead due to orders of government higher authorities.
When responding to the question, “If you are struggling peacefully and unable to rent a hall, how would you able to keep struggling?”, Dr. Moga Ferissa responded as follows: (2፡25-2፡56)
Since UDJ did not sign the election protocol, it is considered as a terrorist organization. However, the organizations that are party to the election protocol did not get any benefit. Therefore signing the election protocol does not make any sense.
In related news, the court has decided the leader of Oromo Federal Democratic Movement, Mr. Bekele Gerba, as guilty and has been asked to defend his case of terrorism charges.
Mr. Bekele Gerba was imprisoned following the Arab Spring in the Middle East Countries fearing that he may insight similar uprisings. Mr. Bekele Gerba has consistently said his accusation is politically motivated.

Loving Ethiopia to death – the Doctors.

April 5th, 2012 | 
Loving Ethiopia to death – the Doctors. By yilma Bekele On November 11, 2011 Yenesew Gebre was driven to kill himself on behalf of all suffering Ethiopians. He killed himself out of love for his people and country. He made the ultimate sacrifice to wake us up so we can see what it means to be humiliated in your own home. Love can be expressed in so many different ways. Yenesew’s method was that of a teacher. That is what he was in real life. Yenesew was a shepherd and an example setter to his people.
On March 24, 2012 Ethiopian Review reported about exiled Ethiopian physicians holding a meeting in Virginia, US to raise money to invest in a referral hospital in Ethiopia. A very laudable act you might say. They must love their country and people so much that even after being kicked out, exiled or driven off from their homeland they were willing to help. Isn’t that a sign of generosity and love? I agree. There is nothing like giving. Aren’t we such a blessed people to have caring individuals among us?
Wait a minute, let us not put the cart in front of the horse please. Everything has a context otherwise it is meaningless. Our physicians ‘love’ for country has to be put in its context so we can really understand and appreciate their ‘selfless’ act. This is where the problem rears its head. They say the devil is in the details and it is nowhere true than in this instance. Our physician’s act is nothing more than a cheap trick to pad their bank account while looking selfless and honorable. Their act is that of a charlatan. They are trying to get advantage using deception. It is petty theft and nothing more than the act of a common criminal. How sad coming from people of such high knowledge that have taken the oath to do good. Well they are Ethiopians aren’t they; the rules don’t work in the land of TPLF Ethiopia. Being a physician is a sign of high achievement. It requires sacrifice, dedication and plenty of work. It is an honorable profession. Doctors are held in high esteem and it is every mother’s dream for her baby. They teach you how to cure the sick in medical school. They make you a technician of the human body. The engineer build bridges, the architect designs house, the mechanic fixes engines, the chauffer drives a car, the physician cures people, the politician leads and the shoeshine cleans shoes. All are expert in their field. It is the contribution of each that makes a society work in harmony.
We put physicians on a pedestal. We ascribe a certain amount of higher intelligence to the doctor. That is more so in a backward society like ours. It is not healthy. We confuse education with common sense. One might be trained to be nuclear scientist but the possibility is there that the individual might be void of common sense or social grace. Those that have spent a major portion of their life pursuing a single goal can sometimes loose sight of the bigger picture.
When it comes to our learned compatriots we are dealing with two aspects of this myopic situation. There are some that are truly attracted to do good and help their people. At he same time there are those that will betray their people for thirty pieces. Isn’t that the situation we got here? That is what I believe. In a country where one man surrounded with his ethnic group and lords it over eighty million others, in a place where one is judged by his blood line instead of his deeds, in a location where no none is allowed to speak or associate freely and in a land where the young and able are forced to leave due to lack of opportunity our esteemed doctors are collecting money to enable the evil doer. None other than Ato Girma Birru – our Oromo Ambassador, called them into a meeting. I know it is rude to identify an individual by his ethnic affiliation on the other hand Ato Girma owes his position due to his ethnic identity. He was the token OPDO Minster in the TPLF cabinet and today he is the token representative in the US. Before his assignment to his new job he was Minster of Industry and Commerce in emerging democratic Ethiopia. Makes you wonder what he did all day doesn’t it? When you consider that he was a simple student like the rest of us before the arrival of TPLF and today he counts as one of the richest individuals in the country you know what he was busy at in his position. The well-dressed and manicured Ambassador is a picture of well-fed and modern Ethiopian. Our physicians are the symptom of the disease afflicting our country. We focus on them because they are an easy target to identify. But this disease of discounting Ethiopia is nothing new. It has been going on for so long that it has become part of us. We all have become numb to being humiliated, trampled upon and discarded. No need to point our fingers at the greedy doctors when every house is a source of this virus of selfishness and greed. I do not mean to insult you my dear Ethiopian but isn’t time we reflect on our actions? Tell me who buys stolen plots of land? Who flies Ethiopian Airlines? Who party’s in Addis among the starving? Who invests in hotels and brothels from Mekele to Moyale? Who turns a blind eye when the Anuaks are massacred in Gambella, the Amharas displaced from Benji Maji, the Oromos imprisoned in mass, the little girls sold into slavery in the Middle East? Don’t tell me you did not know. You knew but you choose to keep silent.
We choose to be upset because Hillary Clinton sat with the monster in Arat Kilo. We seethed with anger because the little dictator inserts himself in every international meeting, we blow our tops when Gambella is leased to grow rice, Professor Asrat was murdered, teacher Assefa Maru is gunned down, Kinijit is imprisoned and elections are stolen. It took all five minutes to cool as down. Our anger was not real. It did not come from deep. Surface anger is so pathetic don’t you think so?
Our esteemed physicians came to the west because they could not serve the people that paid for their training working under the existing regime. Unfortunately they forget why they were driven away. They are just showing us how self-centered and idiots they are. Doctors without borders are in Ogaden tending to the deliberately starved, they are in the rift valley helping the intentionally marginalized and our doctors were assembled in Virginia to serve the less than one percent. Shame is an understatement. When did we loose our moral compass is a valid question?
You know what it took me along time to push send after I wrote this piece. I was worried offending you. I felt like I am not a good ‘chewa’ Ethiopian, rude and confrontational is not our style. Then the picture of the displaced came to me. I saw the children from Benji Maji left to be homeless. I remembered my sister Alem Dechasa alone and helpless in Lebanon. I thought of my people in the jungles of Central Africa to be eaten by wild animals or drawn into harms way in other peoples’ conflict or imprisoned in Yemen and I said enough is enough. I have no reason to please no one.
I have bad news for you my people. Freedom cannot be outsourced. The Americans, the British nor the Norwegians are going to liberate you. Liberation comes from deep inside. It comes from being true to your self. It comes from caring for other as you care for yourself. How could you save others when you are sinking your self? As for our physicians that are deluding themselves about helping our people I have one message for them-kindly shove your PhD’s where the sun does not shine and take two aspirins for the pain. The physical pain will go away but the mental anguish caused by your betrayal will never leave you, ever. As for me my friends, I am working overtime to bring this nightmare to an end. I support Ginbot 7, I am energized by the new OLF, I help ESAT and I am always there to expose Woyane atrocity every chance I get. I teach people on the goings in my homeland. I write my Congress representative to remind them of the plight of my people and I will never rest until this cancer is wiped out from my body politic. Sometimes the going gets rough, the road seems impassable but no one promised me a jolly ride. The fact that some individuals or groups betray our trust is no reason to resign and go home. I just reengineer and thrust on because the liberation of my country and people cannot be dumped onto others. What about you are you just complaining insistently, blaming others or are you becoming part of the problem like our educated but reality challenged physicians? It is a choice you have to make.

Why the U.N.’s Silence on Ethiopia’s Attacks in Eritrea?

by Michael Abraha

April 6, 2012

Addis Ababa — Eritrean President Isaias Afewerki has fastened the blame on the US for ‘organizing’ the recent Ethiopian military incursions, which he says is aimed at diverting world attention from his country’s border row with Ethiopia. Speaking on State TV in late March, Isaias said the Ethiopian attack had its roots in Washington’s “failed agendas” and “wrong calculations”.  Whether his assertions are shared by the rest of the country is hard to fathom as people are not free to offer opinions and criticizing the government is unimaginable.
The Security Council has simply ignored President Isaias’s concern, which meant for the UN bending its Charter principles of the sanctity of the idea of territorial integrity of UN member states.
The Eritrean government is not helped by its isolationist, defiant behavior which has led to debilitating UN sanctions imposed on charges of fueling violence and terrorism in the Horn of Africa Region. Its miserable human rights record has also earned her no friends.
Under these circumstances, the Security Council was inclined to treat the Ethiopian incursion the same way it treated the Kenyan invasion of Somalia last October in pursuit of Al-Qaeda linked Al-Shabab operatives who attacked tourists inside Kenya. A UN sanctions monitoring team determined in July that both Somalia and Eritrea were serving “as platforms for foreign armed groups that represent a grave and increasingly urgent threat to peace and security in the Horn and East Africa region”.
Ethiopia said it was acting in self-defense when it invaded up to 18kms into Eritrea in mid-March overrunning three of its military garrisons at Gibina, Gelehibe and Ramid in South Eastern Eritrea, where Asmara was “arming and training…hit-and-run terrorists” such as the anti-Ethiopia Afar rebels who attacked 27 European tourists in January, murdering 5 and kidnapping two others. A government statement warned of additional operations if Eritrea failed to stop being a “launching pad for attacks against Ethiopia.”
In a statement after Ethiopia announced its operations, the Eritrean government dismissed Ethiopian accusations that it supported the Afar Revolutionary Democratic Unity Front or ARDUF to attack the tourists. Avoiding a retaliatory response, it urged the UN to denounce the Ethiopian action which it claimed was aimed at diverting attention from its border dispute with Ethiopia.
Suggestive of its continued relationship with Al-Shabab as underlined by the UN Sanctions Monitoring Group, the Eritrean government rejects AU military intervention in Somalia as amounting to “meddling” in the internal affairs of the troubled Horn of Africa country. The UN regards Eritrea’s attitude and support of Al Shabab as a cynical plan that only encourages extremism and terrorism which has so far claimed the lives of over 21,000 Somalis.
The UN thus concludes that “Eritrean involvement in Somalia reflects a broader pattern of intelligence and special operations activity, including training, financial and logistical support to armed opposition groups in Djibouti, Ethiopia, the Sudan.” Added to this was the UN report of a foiled Eritrean attempt to blow up an AU summit in January 2011 in Addis Ababa.
The Security Council imposed a stricter second round of sanctions on Eritrea in December targeting its lucrative mining industry and its “Diaspora taxes” believed to be collected through methods of intimidation, blackmail and extortion from hundreds of thousands of Eritrean refugees and other expatriates. The UN says impoverished Eritrea is using these sources of revenue to destabilize the Horn Region. Eritrea has denied the UN charges.
UN-Eritrea relations are at their lowest point. They started deteriorating in 2008 when Eritrea expelled UN Peace Monitoring troops from areas on the Eritrean side of the border with Ethiopia, which Addis Ababa now says are being used as safe haven for ‘insurgents and terrorists” preparing to launch subversive missions in Ethiopia. The UN presence on the border was meant to discourage the kind of military action Ethiopia took inside Eritrea on March 15 – an action which could lead to Eritrean reprisals, thus sending the two nations to yet another bloody war.
By kicking the UN peace forces out, Eritrea wanted to remind its citizens that the war was not over until the border was demarcated. In so doing it was also putting pressure on the UN to force Ethiopia to abide by a “final and binding” demarcation resolution adopted in 2002 by The Hague based Ethiopia-Eritrea Border Commission. The resolution puts the contentious village of Badme inside Eritrea.
Ethiopia has since decided to accept the Commission’s ruling unconditionally but says it wants negotiations with Eritrea on how to implement it. Eritrea wants physical demarcation first and then it will decide if it wants to talk. Thus the impasse continues.
Human Rights Abuses  
The Eritrean government’s reported destabilizing role in the Horn Region is indefensible. Equally reprehensible is its shocking human rights violations which the international community needs to urgently tackle if the regime is to be humanized. Simon Tisdall of The Guardian has described Eritrea as “hell on earth.”
Thousands of young men and women keep fleeing the country knowing they may be abducted by human traffickers and end up in the Sinai Desert with the possibility of being raped, tortured, and killed for their internal organs to be sold to the highest bidder.
A UN report links the regime to “people trafficking” involving despairing Eritreans trying to get out of the country. At home, citizens face arbitrary arrests, torture and detention in life-threatening conditions for indefinite periods of time. For many rotting prisoners, the only way out has been to commit suicide if they can find the means to do so.
The government allows no freedoms of speech, press or of movement or travel abroad. The system is totalitarian which means the people have no right to change their rulers through democratic means.
The government says it needs a firm control over the people until its border issues with Ethiopia are settled. But it has also given no hint that there will be democratization and respect for human rights once its border problems are solved. Additionally, there are no indications that the government will introduce changes in its dangerous foreign policy.
As is often the practice in times of Eritrean national crisis, the government has accused Washington for being behind the Ethiopian action. The American Embassy in Asmara has put out a statement dying the charge.
The fact remains that the Security Council’s inaction in the wake of Ethiopian attacks inside Eritrea was a rebuke and a warning against the Red Sea state. What political impact these developments will have on the people and government of Eritrea is yet to be seen. It is clear however that the country will continue to face more humiliation and sanctions unless the government stops brutalizing its people and learns how to live in peace with its neighbors.

ነፍስህ በሰላም ትረፍ ! እኛ አንረሳህም ! ትሩፋቶችህ ይኮረኩሩናል


,,,,እነሆ በረከት ወ ስበሃት ,,,,,,,
         አስራ አራት ዓመት ወደኋላ ልመልሳችሁ ነው……. ጨርቆስ አካባቢ አንዲት ውብ ጓደኛችን ቤት ታድመናል ሁላችንም አንድ አይነት ፍላጎት ፤አንድ አይነት አስተሳሰብ እና ለኪነ-ጥነብ ልዩ ፍቀር ያለን ጓደኞች፡፡ አንድ ትልቅ እንግዳ ልንቀበል ነው፡፡ ነገሩ ምን መቀበል ብቻ ምናልባት ስለሱ ተሰምቶ፤ተወርቶ የማያልቀውን ዝናውን እውቀቱን ህይወቱን ብቻ ሁሉ ነገሩን ለመቋደስ፡፡ ቤቷ ጠባብ ነች ግን ትበቃናለች፡፡ ቆይ ስንት ነን ዳንኤል፤ ዳዊት፤አለም፤ እኔ…….. ማ ቀረ? እንግዳው ጋሽ ስብሃት እንግዳውን ይዞት የሚመጣው ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ፡፡
      አዎ በህይወቴ እጅግ ደስ ያለኝ ቀን ቢኖር ስብሃትን የዛን ቀን በአካል ያገኘሁት እለት ነው፡፡ሁሉ ነገር ተዘጋጅቷል፡፡ ምሳ ፓስታ ነው የተጋበዘው ደስታው ወደር አልነበረውም፡፡
ምግብ ሰሪዋን ምን ብሎ እንዳመሰገናት ልንገራችሁ፡፡ "አለም" ጠራት ፡፡ "እኔና ቤቴ ግን አግዚያብሄርን እናመሰግናለን"፡፡
ሁላችንም የቻልነውን፤ውስጣችን የሚመላለሰውን ነገሮች ሁሉ መጠየቅ ጀመርን ሰውየው ይመልሳል……….
                 "እስቲ ስለ ኤሚ ዞላ አጫውተን"
     ዳዊት ነው ጠያቂው ስለፈረንሳዊው ታዋቂ ደራሲ በደስታ ይመልሳል የደራሲውን ግልጽነት፤ደፋርነት አነጋጋሪነት የቃላት አመራረጥ ዘዴውን…….. እኔም ቀጠልኩ
                       "ጋሽ ስበሃት"
                             "ለበይክ" አለኝ
              "ስለ ቼኮቬራ አውርተህ አትጨርስም  ለኔም ብታካፍለኝ" ፡፡ ጠየኩት፡፡                                                
              ድንገት ከተቀመጠበት ፍራሽ ላይ ብድግ ብሎ ቆመ፡፡
    " ጥሩ ጥያቄ ነው ቼኮቬራን ግን ቁጭ ብዬ አይደለም የማወራልህ አጥንቱ ይወጋኛል"
       አለና "ቼ..ለኔ ልዩ ሰው ነው መልዓክ አይነት…. ግን ቆይ ሃኪም እንደነበር የሚያውቅ ሰው አለ ከመሃላችሁ?" ጠየቀን….. መልስ የለም፡፡ የሚመስጥ ታሪኩን አውርቶ ሲጨርስ እ….እፎይ ብሎ ተቀመጠ፡፡ መልሶ እኔን ጠየቀኝ
                         "አንተ ግን ሙስሊም ነህ ?"
                               "አዎ ነኝ"
                          "ቁርአን አንብበሃል?"
                             "አላነበብኩም"
                       "ቀረብህ ኢቅራ….." አለኝ፡፡
     እሱ ኮ…ቁርአንን ፉት አደርጎ አንብቦታል ማንበብ ብቻ ሳይሆን የእስልምናን አመጣጥ የነብዩ መሀመድን፤ገድል፤ስርአት፤አስተምሮት፤ጠንቅቆ እንደሚያውቅ፤ እንደሚወደው፤ ታሪኩ እንደሚመስጠው አጫወተኝ ተገረምኩ፡፡ ዳንኤል ሰለሰ………
 "ጋሽ ስበሃት"
                                 "አቤት ወዳጄ"
                  "ስለ ውበት ያለህን አመለካከት እባክህ ጀባ በለኝ"
         "መረሃባ ዳኒ ቆይ የሴት ጡት ጫፉን ትኩር ብለህ አይተህ ታውቃለህ?"
                               "ኧ…..ረ አላውቅም"
     ደነገጠ …. እኔም ደንግጫለሁ…. ሁላችንም ፊታችንን ወደ ቤቷ ባለቤት ጓደኛችን አለም አዞርን ሴት እሷ ብቻ ነች……..ጋሽ ስብሃት ግን አልገረመውም ፤አልደነቀውም ፤ አልደነገጠም ፡፡ ቀጠለ…..
 "በቃ ውበት ማለት በተወጠረ የሴት ጡት ጫፍ ላይ የምታየውን አይበገሬነት ይመስላል "
    ነጻነቱ ገረመኝ በወሬ የሰማሁትን በአይኔ አየሁት፡፡ አንድ ጥያቄ መጠየቅም ፈለኩ
                               "ጋሽ ስበሃት"
                                 "ለበይክ"
    "ለበይክ" ማለት ( አቤት) እንደማለት ነው በአረብኛ፡፡
                     "አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ነው"
                                 "ማለፊያ ጠይቃ"
       "ብዙ ጊዜ ስለ ውቤ በረሃ አንስተህ አትጠግብም ደግሞ ወቤ በረሃን እንደወረደ ማውራት፤ማንሳት ትወዳለህ ምንድነው ሚስጥሩ?"፡፡ አልኩት መልሱን እየጓጓሁ፡፡
                       "መርሃባ ና እጅህን አምጣ"
          አለኝና የመጨረሻ ጣቱን ቀስሮ ሌሎቹን አጥፎ ወደኔ ዘረጋቸው፡፡እኔም እሱ እንዳደረገው ተከተልኩት፡፡ የመጨረሻ ጣቶቻችንን እንዳቆላለፍን ከሰኮንዶች ቆይታ በኋላ አላቀን ሳም አደረግናቸው እንደልጅነታችን……
            "አሁን የምወደውን ጥያቄ ጠየክ ይኅውልህ ውቤ በረሃ ለኔ ገነት እንደማለት ነው፡፡ የዋህነትን ፤ቀጥተኛነትን ፤የምታውቅበት የሚገባህ ዘመን ነው፡፡ ያኔ ደንሰህ፤ጨፍረህ፤ሀጢያትህን አስነጥሰህ የምትመለስበት ቦታ ፡፡ ብር የለም ያኔ የፈለከውን ግን ታገኛለህ መደነስ ካማረህ ደንሰህ፤መጠጣት ካማረህ ጠጥተህ፤ሴት ማቀፍ ካማረ አቅፈህ ትመለሳለህ በነጻ፡፡ እኔማ በዚህ እታወቃለሁ፡፡ መንግስት የሚከፍለኝ ብር አይበቃኝማ ታድያ እሞታለሁ ፡፡ አንድ ባለ ሱቅ ነበር..ቆይ ስሙ ጠፋኝ እንዴ……? አዎ ፈድሉ ይባላል ባለ ሱቅ ነው ደንበኛዬ፡፡"መቶ ብር አበድረኝ" እለዋለው ድፍኑን ነው ታድያ ይሰጠኛል እሷን እይዝና አንዷ ኮማሪት ቤት እገባለሁ "ስጪኝ" እላታለሁ "እሺ" ትልና ትሰጠኛለች ተኝተን ስናበቃ ድፍን መቶ ብሩን እሰጣታለሁ፡፡ የእንትን ዋጋ እኮ አንድ ብር ነው፡፡
                                 "ዝርዝር የለህም?"
                          ትለኛለች፡፡ ከፈለግሽ ዘርዝሪው እላታለሁ፡፡
                          "በቃ ነገ ስትመጣ ትሰጠኛለህ ሂድ"
ትለኛለች ሌላ ቤት እገባለሁ ተመሳሳይ ዘዴ እጠቀማለሁ ፡፡ በአንድ ምሽት ሶስት አራት ቤት ገብቼ እወጣለሁ፡፡ መቶ ብር እኮ የአንድ ባለስልጣን የወር ደሞዝ ነው እንዴት ያለ ወርቅ ዘመን መሰላችሁ መጠጥ ብትፈልግ በቅምሻ ትጠግባለህ….፡፡ በመጨረሻ በዛኑ ምሽት መቶ ብሩን ለፈድሉ እመልሳለሁ፡፡" በትዝታ እሩሩቅ ተጓዘ………፡፡
                       *     *     *
         ከውስጤ ልውጣ አልውጣ እያለ የሚተናነቀኝን የኪነ ጥበብ ዛር ሰክኖ እንዳይ እፎይ ብዩ እንድተነፍስ በተለይ ስነ-ግጥም ስሞነጭር በርካታ ጊዜያትን አሳልፌያለሁ፡፡ ማንበቡ፤መወያየቱ እንዳለ ሆኖ የደረጃዬን ልክ ሚዛን ማወቁ ግን ተስኖኛል እርዳታ የምፈልግበት ወቅት ነው፡፡ ሰውየውን አንድ ጥያቄ ልጨምርለት፡፡
                              "ጋሽ ስብሃት"
                                "ለበይክ…….."
                  "ደራሲ መሆን እፈልጋለሁ ምን ትመክረኛለህ?"
            ከት ብሎ ሳቀ ሳቁ ግን አይሰማም ……..
                "በቃ ዝም ብለህ ጻፍ ጻፍ የተሰማህን፤ያየህውን፤ስለገርል ፍሬንድህ ቁጣ፤ቀጥረሃት ስለጠፋህበት ሁኔታ፤ስለ ንጭንጭኗ ፤ሳቅና ፈገግታዋ፤ እንዲህ ስለ ዛሬ ውሎአችን ፤ ስለዚህች መልካም ልጅ " ፡፡ እጁን ቀስሮ አለምን  እያሳየኝ፡፡
                      " ጻፍ ጻፍ ጻፍ…….."፡፡
          "ግጥም መጻፍ ይመቸኛል ነው ያልከኝ? በጣም ከባድ እኮ ነው፡፡ እንካማ…… አንድ ቲያስ አሌዮት የተባለ ፈላስፋ የተናገረውን ላቀብልህ "ማንም ታማኝ ገጣሚ ስለጻፈው ግጥም ዘላቂ ጥቅም እርግጠኛነት ሊሰማው አይችልም፡፡ጊዜውን ያባከነውና ህይወቱን ያመሰቃቀለው ያለአንዳች ፋይዳ ሊሆን ይችላል " ይላል፡፡ ስለዚህ ግጥም ሙያ አይደለም እጣ ፈንታ ነው" ፡፡
        አለና ትንሽ እንደማሰብ ብሎ………
    "ግን ለዝና ብለህ አትጻፍ ሲፈልግ አይታተም ፤ ብር አያምጣ ዘነበ ፤እኔ፤ እሱ ፤ እሷ ካነበብን ይበቃል"፡፡ ጨረሰ፡፡
                   በትንሽዬ ኮዳ የሚወዳትን ነገር ይዟል ከጠበሏ ፉት አለ፡፡
                        ዳንኤል ብእርና ወረቀት አስጠጋለት
                                 "ምን ላድርገው?"
                                  "ፈርምልኝ"
                           "ለምንድነው የምፈርምልህ?"
                             "አድናቂህ ስለሆንኩ ነው"
                  "እሺ… ካልህ የራስህ ጉዳይ ነው፡፡ ሌላ ቀን ደግሞ ሌላ እንዳትለኝ"
አለና ብእርና ወረቀቱን ተቀብሎ የሆነ ነገር ጻፈና ፈረመ ፡፡ እኔም ከዳንኤል ተቀበልኩና አነበብኩት፡፡
                     "ሁለትም ሶስትም ባላችሁበት እኔ እገኛለሁ፡፡"
                                     እየሱስ…………..
                                                ከስር ፊርማ ፡፡
                                        እኔም አስጠጋሁለት
                       "ደራሲ እሆናለሁ ተብሎ ደራሲ አይኮንም "
                                                 ፊርማ…….
                            ቅድም  የሳቀበት ምክንያት አሁን ገባኝ……………..
                                *      *        *
             የቀኗ ጀንበር ማዘቅዘቅ ጀምራለች የማይደክመው ስብሃት የተጠየውን መመለስ ቀጥሏል፡፡ እውነት ለመናገር ስብሃት ትምህርት ቤት ነው ትልቅ ቤተ-መጽሐፍት……. እየተገለጠ የሚነበብ ብዙ ተማርኩበት……. ከሱ ጋር መዋል ሱስ ያሲዛል፡፡ ዘነበ ወላ "ልጅነትን" እየጻፈ ነበር በወቅቱ የደረሰበትን ምእራፍ ለስብሃት ለአብ ያነብለታል ሰውየው ያዳምጣል፡፡
                    "ቆይ እስቲ ያሁኑን አረፍተ ነገር ድገምልኝ"
ደግሞ ያነብለታል ዘነበ፡፡
ልጅ ሆኖ ስለ አበበ በቂላ የሚያውቀውን የሚተርክበት ቦታ ነው ቶኪዮ ላይ ስላስመዘገበው ገድል……………
                  "እዚ ጋር እቺን ቃል አውጣት ይሄን ቃል አስገባው"
       ያርመዋል………
 ዘነበ የተባለውን ይፈጽማል፡፡ አንድ ነገር ግን አልረሳም ከእጁ የማይጠፋውን መቅረጸ ድምጽ ወደ ስብሃት አስጠግቶ ይቀርጻል አምስት የቴፕ ካሴቶች እፍራሹ ላይ ይታዩኛል ስድስተኛው መቅረጸ ድምጹ ውስጥ ተጠምዷል ፡፡
           በዚህ መልኩ የተጠራቀመ የስብሃት ለአብ ልሳን ወደ ሰላሳ ካሴቶች ደረሱ ፡፡ ለጥቆ ዘነበ ላይ አንድ ነገር አጫረ ወደ መጽሃፍ መቀየር………..፡፡ ህልሙን እውን ለማድረግ ብዙ ጣረ አዎ በወረቀት መገልበጥ ጀመረና 345 ገጥ ላይ ደረሰ እናም ብዙ የደከመው ዘነበ በ ወርሀ መጋቢት 1993 ዓም ተሳካለት እና የስበአት ለአብ "ማስታወሻ" ተወለደ………….፡፡ እናም ስበሃትን አነበብነው ተዝናናንበት፤በፍቅሩ የወደቅን ውስጣችን እንዲገባ ፈቀድንለት፡፡ አዎ በርካታ ጸሃፍት እግሩን፤ዱካውን ተከተሉ…….ስለ ነጭ ጢሙ፤ከእጁ ስለ ማትለየው ተአምረኛ ፌስታል፤ትከሻው ላይ ጣል ስለ `ሚያደርጋት ሹራብ ፤ ስለ ንግግሩ ቃላት አጣጣሉ፤ዘገምተኛ አረማመድ(አካሄዱ)፤ስለ በላው ምግብ ስለ ጠጣው ነገር፤ስለ ነካው ስለ ጣለው ነገር ወዘተ…….. በተለያዩ ጊዜ በሚጽፏቸው መጣጥፎች፤ወጎች፤ረጅም ልብ-ወለዶች ማጣፈጫ ቅመም ሆነ…… መሪ ገጸ-ባሕሪ አድርገው ተጠቀሙበት ቆይ እንደውም ከማስታውሰው የበአሉ ግርማ (ደራሲው) ፤የአዳም ረታ (እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ) ሌላም ሌላም መጽሃፎች ውስጥ ታገኙታላቹ ፡፡ ወደፊትም እንደሚጽፉት ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ሰዓሊያንስ ብትሉ ከጀማሪ እስከ አዋቂ የስብሃትን ገጽ (ትልልቅ ዓይኖቹን ያላፈጠጠ) ፤ (ነጭ ጢሙን ያላንዠረገገ) ያልሞነጨረ  ፊት ለፊት እያየው በሃሳብ ያላወራ………..ማን አለ?፡፡ እኔም ሚስጥር ላውጣ በምችለው በተሰማኝ መንገድ በግጥም እፎፎፎፎፎይ ብያለሁ ፡፡
            ስብሃት ለአብ መሆን እንደሚፈልገው ሆኖ ፤ መጻፍ እንደሚፈልገው ጽፎ የሚኖር ደራሲ ነው፡፡ ነጻነቱ እጅግ ያስቀናኛል፡፡ ስንታችን ነን መሆን እንደምንፈልገው ሆነን፤ ማድረግ የፈለግነውን አድርገን፤የኖርን? በአጉል ወግና ስርአት ተሸብበን፤በአጉል ባህልና ስርአት ተወጥረን መሆን ያለብንን ሳንሆን አርቴፊሻል ኑሮ የተፈረደብን? በቤታችን በጉያችን ስንት ጉድ እና አመል ተሸክመን አደባባይ ለመታየት ፤ ለመምሰል የተሰለፍን?፡፡ እናም ከጋሽ ስብሃት ጋር ስትሆን መንፈስህ ይረጋጋል ክብድ ያለው ህይወትህ ቀለል ይልልሀል መኖር ማለት አሁን… ዛሬ… መሆኑን ትረዳለህ እናም ከጋሽ ስብሀት ጋር ስሆን መንፈሳዊ ቅናት ያድርበኛል፡፡
            የቀኑ ውሎአችን ሊገባደድ ነው መሽቷል፡፡ አንድ ጥያቄ ግን ይቀረኛል፡፡
                                "ጋሽ ስብሀት"
                                   "ለበይክ"
             "አንተ ኮ ታዋቂ ደራሲ ነህ ለምንድ ነው የግል መኪና የሌለህ?"
                   አንገቱን አቀርቅሮ ለትንሽ ደቂቃ ቆየ
                                "ምን አገባህ"
       " እንዳልልህ አሳዘንከኝ ጥያቄህ የዋህነት ይነበብበታል ግን እንካ ልንገርህ…… ከንቲባና ደራሲ በእግሩ ነው መሄድ ያለበት፡፡ በህዝብ መሃል መሹለክለክ፤ትንፋሹን መተንፈስ፤ለቅሶውን ማልቀስ፤ሲያስነጥሰው፤ማንጠስ ደስታውን፤መደሰት ወዘተ…..፡፡ እነሱን እየጻፍኩ እነሱን እየኖርኩ ጉሮሮዬን እደፍናለው ከንቲባም ስለነሱ እያወራ ይሰነብታል ሁለታችንንም እሚያኖረን ህዝብ ነው፡፡ ታድያ ይሄን ማግኘት የምትችለው በእግርህ ስትሄድ ነው፡፡ አንተን፤እናንተንስ በእግሬ ባልሄድ አገኛቹ ነበር ? " ጨረሰ፡፡
                      *        *        *
             ሰው ጊዜን ያህል ነገር እንዴት ይረሳል?፡፡ ያውም በልቡ ውስጥ ገብቶ መላው ሰውነቱን ካናወዘው የአንድ ቀን አጋጣሚው እንዴትስ ሊዘነጋው ይችላል?፡፡ እንደው የእህል ውሃ ነገር ሆኖ ውሉን በሳተ ጎዳና ከመክሊቱ ርቆ እሱነቱን አሳልፎ በመስጠት ኑሮን በመግፋት ሲኖር……ሁሌ መብሰክሰኩ፤መቃተቱ አንድ ቀን መዘመሩ፤እህህ ማለቱ የተለመደ ነው፡፡
             ከምኖርበት ከተማ ለስራ ጉዳይ ወደ አዱ ገነት መጥቻለሁ……ረጂም ጊዜ ሆነኝ ከመጣሁ፡፡ ወደ ቦሌ ሽቅብ እየወጣን ነው ደንበል ህንጻ ጋር ስንደርስ ትራፊክ መበራት ያዘን በመስኮት አጮልቄ ግርግሩን እያየሁ ነው ፡፡ ድንገት አንድ ሰው ላይ  አይኔ ተተክሎ ቀረ አልተሳሳትኩም ስብሃት ገብረ እግዚአብሄር ነው፡፡ ከአስራ ሶስት አመት በኋላ……፡፡ አላመንኩም ሰውየው እንዳለ ነው ፌስታሏም አለች……. ሹራቧም ትከሻው ላይ ተንጠልጥሏል፡፡ ማመን አቃተኝ ከሱ እኔ አርጅቻለሁ መንፈሱ ጠንካራ ነው አረማመዱም እንደተጠበቀ፡፡ በትዝታ ወደኋላ ተጓዝኩ………በአካል አይቼው አላውቅም ስለ ጤንነቱ ግን አልፎ አልፎ ከዘኔ ጋር እናወራለን በስልክ… ሲለው ደግሞ ካለሁበት ይመጣል ወሬ ያቀብለኛል መታመሙን፤ሆስፒታል አስገብቶት እንደመጣ ነገረኝ አዘንኩ፡፡ መልካሙን እንዲገጥመው ተመኝተንም ተለያየን፡፡
          ሰኞን አልወዳትም ፈረንጆቹም (black Monday) እያሉ ነው የሚጠሯት፡፡ስራ ለመግባት በግድ ነው የተነሳሁት፡፡ ድንገት ተንቀሳቃሽ ስልኬ ጮኅች፡፡ ዘነበ ነው እንደፈራሁት ዜና እረፍቱን አረዳኝ፡፡ እናም እንዲህ ሲል ጨመረልኝ……………..
                    "አንድ ሙሉ ቤተ-መጽሀፍት ተቃጠለ"
              እኔም እስማማለሁ ስብሃት ከዛም በላይ ነበር ብዙ ጸሀፍት ብዙ እንደሚሉ እገምታለሁ ያልተባለ ያልተነገረለት ብዙ ነው እኔ አንድ ቀን አገኘሁት አንድ ቀን አወራሁለት ሺ ዘመን ግን እንዳነበው ፍቀዱልኝ፡፡
                 *       *       *
                                   13/5/2004 ዓም
                                     አደም ሁሴን
                                         ናዝሬት
                                               Adem_hussen@yahoo.com

Wednesday 4 April 2012

ሕገ መንግሥትና ሕግ የማይስማሙባት አገር

አቶ በላይነህ ተካልኝ (ስሙ ተቀይሯል) ተወልዶ ያደገበትን ደብረ ኤልያስ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር (ምዕራብ ጐጃም ዞን) ለቆ ሥራ ፍለጋ ወደ ደቡብ ክልል የተጓዘው የአሥራ ስድስት ዓመት ታዳጊ ወጣት በነበረበት በ1987 ዓ.ም. ነው፡፡
የተሻለ ኑሮ ፍለጋ የትውልድ ቀየውን ጥሎ የሄደው ይኼው ወጣት ወደ ደቡብ ክልል አምርቶ ለስድስት ዓመታት ያህል በቡና ለቃሚነትና በከብት እረኝነት ተቀጥሮ በማገልገል ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ሕይወት ሲመራ ቆይቷል፡፡ በ1993 ዓ.ም. ግን አቶ በላይነህ ከተቀጣሪነት ወጥቶ የራሱን ሕይወት በራሱ የሚመራበት ዕድል ተፈጠረለት፡፡ እሱና በደቡብ ክልል የሚኖሩ ሌሎች እሱን መሰል የአማራ ክልል ተወላጆች የመሬት ባለቤት መሆን እንደሚችሉ የሚያበስረው ዜና ሲደርሳቸው ዜናውን አምነው መቀበል አልቻሉም ነበር፡፡

ከ1993 ዓ.ም. በፊት በደቡቡ ክልል ቤንቺ ማጂ ዞን ውስጥ ጉራፋርዳ ተብሎ የሚጠራ ቦታ አልነበረም፡፡ በአሁኑ ወቅት በጉራፋርዳ ወረዳ የሚተዳደሩት የሚኒጥ ብሔረሰቦች ከ1993 ዓ.ም. በፊት ይተዳደሩ የነበሩት በሸኮ ወረዳ ሥር ነበር፡፡ እነዚህ ብሔረሰቦች ‹‹በሸኮ ወረዳ ሥር አንተዳደርም ራሳችን በራሳችን ማስተዳደር አለብን፤›› የሚል ጥያቄ ሲያነሱ፣ ‹‹ራሳችሁን በራሳችሁ ለማስተዳደር መስፈርቱ የሚጠይቀውን የሕዝብ ብዛት አታሟሉም፤›› የሚል ምላሽ ይሰጣቸዋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ተስፋ አስቆራጭ መልስ የተሰጣቸው የብሔረሰቡ አባላት ግን ሞኞች አልነበሩምና ‹‹ራሳችንን ማስተዳደር አንችልም›› ብለው እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም፡፡ ከዚያ ይልቅ ራሳቸውን ለማስተዳደር የሚያስችል የሕዝብ ብዛት ማግኘት የሚያስችላቸውን ዘዴ ማጠንጠን ጀመሩ፡፡ ብዙም ሳይቸገሩ መልሱን አገኙ፡፡

ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል መጥተው ደቡብ ክልል ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በቡና ለቀማና በተለያዩ የጉልበት ሥራዎች የተሰማሩ በርካታ የአማራ ክልል ተወላጆች መኖራቸውን የሚያውቁት የሚንጥ ብሔረሰብ አባላት፣ ‹‹ወደ እኛ ወረዳ መጥቶ በልማት ሥራ ላይ መሰማራት የሚፈለግ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በሙሉ ይምጣና አካባቢውን ያልማ፤›› የሚል ማስታወቂያ ይለጥፋሉ፡፡ ይህንን ዜና የሰሙ የአማራ ክልል ተወላጆችም ነገ ዛሬ ሳይሉ ወደ ሸኮ ወረዳ አመሩ፡፡ ህልማቸው የሰመረላቸው የቀበሌና የወረዳ አመራሮችም ለልማት የሚውል መሬት በሕጋዊ መንገድ እየሸነሸኑ አከፋፈሉ፡፡ ከሰሜን ክልል የመጡ በርካታ ሰዎችን በአካባቢያቸው ማስፈር የቻሉት የሚኒጥ ብሔረሰቦችም ምኞታቸው ተሳክቶ ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብት አገኙ፡፡ ወረዳቸውም ጉራፋርዳ ተባለ፡፡

በላይነህ ተካልኝ እንደሚለው፣ የጉራፋርዳ ወረዳና የቀበሌ አመራሮች ለእሱና ለሌሎች ሰፋሪዎች የሰጧቸው መሬት በማንም ይዞታ ስር ያልነበረ የበረሃ ሳር የሚበቅልበት ቦታ ነበር፡፡ በአካባቢውም ምንም ዓይነት መሠረተ ልማት አልነበረም፡፡ የራሳቸው መሬት ባለቤት ሆነው በግብርና ሥራ ተሰማርተው ሕይወታቸውን የመቀየር ህልምና ጉጉት የነበራቸው እነዚህ ዜጐች ግን ችግሩን ተቋቁመው በተሰጣቸው መሬት ላይ ቡና፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ሙዝና የመሳሰሉትን ተክሎች በመትከልና የተለያዩ ሰብሎችን በማምረት የሰንበሌጥ ሳር ብቻ ይበቅልበት የነበረውን አካባቢ ወደ ገነትነት ቀየሩት፡፡ አትክልትና ፍራፍሬ በአካባቢው በሽ ሆነ፡፡ በጥረታቸው የራሳቸውን ብቻ ሳይሆን የአካባቢውንም የኑሮ ዘይቤ ቀየሩ፡፡

በወቅቱ 4.5 ሔክታር መሬት የተረከበው አቶ በላይነህም ሁለት ሔክታሩን ለቡና ተክል ቀሪውን 2.5 ሔክታር መሬት ደግሞ ለእርሻ በመጠቀም በቆሎ፣ በርበሬ፣ ሩዝና የመሳሰሉትን ምርቶች በማምረት ሕይወቱን ለወጠ፡፡ ሀብትና ንብረት ማፍራት ሲጀምርም ትዳር መሥርቶ ልጆችን ወለደ፡፡ ጉልበቱን ተጠቅሞ ባፈራው ንብረት ጥቂት የደስታ ዓመታት ያሳለፈው አቶ በላይነህና ሌሎች እሱን መሰል ከሰሜን የአገሪቱ ክፍል የመጡ ሰፋሪዎች ግን የጀመሩትን የደስታ ሕይወት አጣጥመው መቀጠል አልቻሉም፡፡

የደቡብ ክልል መስተዳድር ባስተላለፈው መመርያ መሠረት ከ1999 ዓ.ም. በኋላ በጉራፋርዳ የሰፈሩ የአማራ ክልል ተወላጆች በቀበሌና በወረዳ ኃላፊዎች በሕጋዊ መንገድ ያገኙትን መሬት እንዲለቁና አካባቢውን ጥለው እንዲሄዱ፣ ከ1999 ዓ.ም. በፊት መጥተው በጉራፋርዳ ወረዳ ስር በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች የሚኖሩ ሰፋሪዎች ደግሞ ሁለት ሔክታር መሬት ብቻ ይዘው እንዲቀጥሉ ተደርጓል፡፡ ይህንን ውሳኔ ተከትሎ ጥረው ግረው አካባቢውን ያቀኑ በብዙ ሺሕ የሚገመቱ በርካታ የሰሜን አካባቢ ተወላጆች በኃይልና በጉልበት አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተደርጓል፡፡ አሁንም እንዲወጡ እየተደረገ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን የፌዴራል መንግሥትም ሆነ የአማራ ክልል ባለሥልጣናት አንድም ነገር ትንፍሽ አላሉም፡፡ ለፌዴራል መንግሥት አቤቱታ ለማቅረብ ባለፈው ሐሙስ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ተፈናቃዮችም ከድጡ ወደ ማጡ እንዲሉ በአራት አውቶቡስና በአንድ ሚኒባስ ታጭቀው ባለፈው ሳምንት ዓርብ ወደ ደብረ ብርሃን ተጓጉዘዋል፡፡ እነዚህ ዜጐች አሁን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡

ዜጐች ከቦታ ቦታ ተዘዋውረው የመኖርና ሀብት የማፍራት መብት እንዳላቸው ሕገ መንግሥቱ ቢደነግግም፣ በደቡብ ክልል መስተዳድር የወጣው አዲስ አዋጅ ይህንን መብት በሚጥስ መልኩ እየተተገበረ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ፡፡

መሳይ በቀለ የተባሉ የፖለቲካ ተንታኝ ይህንን ጉዳይ አስመልክተው በድረ ገጽ ላይ ባወጡት ጽሑፍ፣ ‹‹በራስህ አገር ውስጥ እንዴት ስደተኛ ትሆናለህ?›› ሲሉ ከጠየቁ በኋላ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ከዲሞክራሲ ሥርዓት ጋር መተዋወቅ በጀመሩ አገሮች የማይከሰት ነገር እንደሌለ ይገልጻሉ፡፡ ዜጐች የሌላ ብሔር አባላት ስለሆኑ ብቻ ይኖሩበት ከነበረው ቀዬ እንዲለቁ ማድረግ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መሆኑን በጽሑፋቸው ያመለከቱት አቶ በቀለ፣ ከብሔር ጋር በተያያዘ  በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለሚካሄደው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ገዢው ፓርቲ ተጠያቂ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡

ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ብሔርን መሠረት ባደረገ መልኩ የተለያዩ ክልሎች እንዲፈጠር ማድረጉ ዜጐች ለአንድ ዓላማ ከመሥራት ይልቅ እርስ በእርስ በጥላቻ እንዲተያዩ ያደረገ መሆኑን የሚናገሩት እኚሁ ጽሐፊ፣ ‹‹ስለቤንቺ ማጂ ስትሰሙ ምንድን ነው የምታስቡት? ብስጭት? ድብታ? መደናገር? ተስፋ መቁረጥ? በአሁኑ ወቅት ሥልጣን የያዙት የኢትዮጵያ መሪዎች የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ ታያላችሁ፡፡ እነዚህ መሪዎች ከዚህ አድራጐታቸው እንዲቆጠቡ ማድረጊያው ብቸኛው መንገድ ድርጊታቸው ጉዳት እንደሚያስከትል ማሳየት ነው፡፡ ለመጥፎ ድርጊት የሚከፈል ዋጋ አለ፤›› በማለት በደቡቡ ክልል መስተዳደር የተፈጸመው ክስተት አደጋ ሊኖረው እንደሚችል ያስገነዝባሉ፡፡

ኑሮአቸውን በዩናይትድ ስቴትስ የመሠረቱት አቶ መሳይ ከኢትዮጵያ በተለየ መልኩ የህብር መፍጠር (Melting Pot) ጽንሰ ሐሳብ የምትከተለው አሜሪካ የተለያዩ ማኅበረሰቦች ህብር ፈጥረው አንድ የጋራ ባህል ያላቸው ሕዝቦች የሚኖሩባት አገር መሆኗ ለታላቅነቷ መሠረት እንደሆነ ቀጣዩን ምሳሌ በመጥቀስ ያስረዳሉ፡፡ ‹‹በሳምንቱ መጨረሻ የሜዲካል ጉዳይ ስለነበረኝ ወደ ሆስፒታል ሄጄ ነበር፡፡ እኔ ታማሚው ከኢትዮጵያ የመጣሁ ነኝ፡፡ እኔን የተቀበለችኝ ነርስም ኢትዮጵያዊት ነች፡፡ የመረመረችኝ ሴት ናይጄሪያዊት ነች፡፡ ኤክስሬይ ያነሳኝ ሰው ደገሞ ከኤርትራ የመጣ ነው፡፡ የድንገተኛ ሐኪሜ ደግሞ ነጭ አሜሪካዊ ነው፡፡ ከሆስፒታሉ የምወጣበትን ሒደት ያመቻቸችው ሴት ደግሞ ሂስፓኒክ (ከመካከለኛውና ከላቲን አሜሪካ ተወላጅ) ነች፡፡ ሆስፒታሉ የሚሠራው እንደ እንከን አልባ ማሽን ነው፤›› በማለት አሜሪካ የተለያዩ አገር ዜጐችን ‹‹እንኳን ደህና መጣችሁ›› ብላ በመቀበል ለብልፅግናና ለሃያልነት መብቃቷን የሚያስረዱት አቶ ይልማ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን በተቃራኒው የቤንች ማጂ ዞን አስተዳዳሪዎች የራሳቸውን ዜጐች ሀብትና ንብረት በመቀማት ‹‹ወደ መጣችሁበት ተመለሱ›› የሚል ትዕዛዝ ማስተላለፋቸው አገሪቱ ወደ መጥፎ መንገድ እያመራች መሆኑን እንደሚያመላክት ይገልጻሉ፡፡

የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሙሼ ሰሙ በበኩላቸው፣ ዜጐች ከቦታ ቦታ ተዘዋውረው የመኖርና ሀብት የማፍራት መብታቸው በሕገ መንግሥቱ በተደነገገበት ሁኔታ ይቅርና ይህንን መብት የማያጐናጽፍ ሕግ ባይኖር እንኳን በተለያዩ ክልሎች የሚኖሩ ዜጐች እንደዜጋ ህልውናቸውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ይናገራሉ፡፡

‹‹ማንኛውንም ዜጋ ሠርቶ ለመኖር የሚያስችል መብትን የሚያሳጣ ድርጊት በሕግም መልክ ቢሰፍር ስህተት ነው፤ ሊሻሻል ይገባል፤›› የሚሉት አቶ ሙሼ፣ አንድን አገር የሚያስተዳድር መንግሥት ይህንን የዜጎችን መሠረታዊ ፍላጐት የማያስከብር ከሆነ ድርጊቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መሆኑን ይገልጻሉ፡፡

እርሳቸው እንደሚሉት፣ ዜጐች ከአገራቸው ወጥተው በተለያዩ አገሮች በመኖር በነፃነት ሥራ ሠርተው ሕይወታቸውን የሚቀይሩበት ዕድል በተፈጠረበት በአሁኑ ወቅት፣ በራሳቸው አገር ውስጥ ጉልበታቸውን አፍስሰውና ዕድሜያቸውን ጨርሰው ያቀኑትን መሬት ለቃችሁ ሂዱ ማለት ከባድ ስህተት ነው፡፡

‹‹ዜጐቹ ዕድሜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ሀብታቸውን በማፍሰስ የመሬቱን ዋጋ (Value) ጨምረዋል፤›› የሚሉት አቶ ሙሼ፣ ከዓመታት በኋላ ያለሙትን መሬት ትተው እንደገና ሕይወትን ‹‹ሀ›› ብለው እንዲጀምሩ መደረጉ በየትኛውም መንገድ ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይችል ይገልጻሉ፡፡

የዜጐቹ በአካባቢው መኖር በአገር ደኅንነት ችግር የሚያስከትል ወይም ደግሞ ግጭት የሚፈጥር ሆኖ ቢገኝ እንኳን ሰፋሪዎቹ ተገቢው ካሳ ተከፍሏቸው እንዲሁም ተለዋጭ ቦታ ተሰጥቷቸው በተገቢው መንገድ አካባቢውን እንዲለቁ መደረግ እንዳለበት አቶ ሙሼ አክለው ያስረዳሉ፡፡

‹‹የአካባቢ ተወላጅ ያልሆኑ ዜጐችን የማፈናቀሉ ዕርምጃ ከየአካባቢው የሚመነጭ ከሆነ የኢትዮጵያዊነት ትርጉሙ ምንድነው?›› ሲሉ የሚጠይቁት አቶ ሙሼ፣ በመሬት ባለቤትነት ከመኖር መብት ጋር በተያያዘ በክልሎች ከሚወጡ ሕጐች ይልቅ ሕገ መንግሥቱ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ይናገራሉ፡፡

በጉራፋርዳ ወረዳ የተወሰደው ዜጐችን የማፈናቀል ዕርምጃ በየትኛውም ክልል የሚኖሩ ዜጐችን የመኖር ሥነ ልቦና የሚያዳክም መሆኑን ሲያስረዱም፣ ‹‹ሁኔታው በዚህ መልኩ ከቀጠለ ነገ አዲስ አበባ የእኔ ነው የሚል አካል ተነስቶ የአካባቢው ተወላጅ ያልሆኑ ዜጐች ይውጡ ቢል ምን ሊከሰት ይችላል፤›› ሲሉ የጉዳዩን አሳሳቢነት ይገልጻሉ፡፡ አያይዘውም ጉዳዩ ከዚህም አልፎ ሉዓላዊነትን በማስከበር ረገድ ከፍተኛ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ይናገራሉ፡፡

‹‹አንድ ዜጋ እንደ ዜጋ ዳር ድንበርን የማስከበር ጥያቄ ሲቀርብለት ጥሪውን ተቀብሎ የሕይወት መስዋዕት የሚከፍለው በማንኛውም ክልል ላይ የመኖርና ሀብት የማፍራት መብት አለኝ ብሎ ስለሚያምን ነው፡፡ አለበለዚያ ጉዳዩ የተወረረው ክልል ጉዳይ ብቻ ይሆናል፡፡ ወደ ፊት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ የራሱን ችግር ይፈጥራል፤›› ሲሉ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ይገልጻሉ፡፡

በጉራፋርዳ ይኖሩ የነበሩ አብዛኛዎቹ ሰፋሪዎች በቀበሌና በወረዳ አመራሮች በሕጋዊ መንገድ መሬት ተሰጥቷቸው በግብርና ሥራ ላይ ተሰማርተው የቆዩ ናቸው፡፡ የክልሉ ኃላፊዎች ራሳቸው በፈቀዱላቸው ቦታዎች ላይ የሰፈሩትን እነዚህን ዜጐች ሕገወጥ ናችሁ የሚሉበት ምክንያት ጉዳዩን ለሚከታተሉት ዜጐች አሁንም እንቆቅልሽ ነው፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ራሳቸው ከ1999 ዓ.ም. በኋላ በቤንች ማጂ ዞን ኑሮአቸውን የመሠረቱ ሰፋሪዎች መሬቱን በቀበሌም ይሁን በወረዳ ኃፊዎች ፈቃድ ያገኙ ቢሆንም፣ ከአካባቢው መልቀቅ እንዳለባቸው ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ‹‹ሕገወጡ ማነው?›› የሚል ጥያቄ የሚያስነሳው፡፡

ወይ ጉድ እህህህህ


ወዳጄ ሰለሰኝ

ማን ነው የሚጠበቅ የሞተ ወይስ የሚተነፍስ



Ethiopia resettlement plan falls short on development

Employees of Saudi Star rice farm work in a paddy field in Gambella, western Ethiopia (© AFP)
By: Jenny Vaughan
Office: GAMBELLA, Ethiopia
04/04/2012 10:49 GMT

When the Ethiopian government asked Thwol Othoy if he wanted to be resettled, he agreed, attracted...


When the Ethiopian government asked Thwol Othoy if he wanted to be resettled, he agreed, attracted by promises of a better life - a clinic, school for his children and land to farm.
But he now struggles to feed his family. After moving from western Ethiopia to the tiny town of Abobo in the Gambella region, he was allocated less than half his previous two acres on which he used to grow maize.
"The food is not enough," said Thwol, 35, sitting by his thatched hut, barefoot and in tattered shorts with an open shirt exposing his bony chest.
Thwol and his family were moved off government-owned land under the east African nation's two-year-old commune programme, which pools scattered rural residents into new communities, ostensibly to provide them better access to services.
But some rights groups and observers fear the programme has another goal: to shove farmers aside for eager -- and often foreign -- investors who cultivate land for crops that will be exported to fuel rocketing food demand in China and other developing nations.
"Livelihoods and food security in Gambella are precarious, and the policy is disrupting a delicate balance of survival for many," Human Rights Watch said in a January report.
The government aims to resettle 1.5 million of its approximately 82 million people by next year. Officials say there is nothing sinister about the plan.
"Any society that's scattered, there's no way you can hear their voice or ensure social and economic services," Federal Affairs Minister Shiferaw Teklemariam said. "It is better to (create) organised set-ups."
Ethiopian land is wholly owned by the socialist-leaning government, which leases it out to companies and individuals for farming or livestock grazing.
In the Gambella region -- dense with vegetation and blessed with regular rain and a large river -- 200,000 people, or just over half the region's entire population, are due to be resettled over the next three years. Close to 90,000 people -- or 20,000 households -- have already been moved.
The fields along the river in Gambella are vibrant green and brim with rice husks, but in Kir, a nearby resettlement village, resident Obuk Ojulu said the land was not as fertile and that he had to rely partly on state grain handouts.
"Where we were before, there was good land," said Obuk, 25. "Here it is not good."
Kir has a small clinic, though its supplies are usually low and a nearby school has no teachers, just rows of kids flipping idly through tattered and outdated textbooks.
Regional agricultural department head Ahmoud Oto denied food shortages and insisted villagers are better off.
"Previously, where they were living, they were not benefiting from services," he said. "Now they are beneficiaries of clean water, health and education."
Human Rights Watch has accused the government of pushing communities off the land to make way for investors, who already occupy 500,000 hectares (2,000 square miles) of land in the region.
As incentives, the government offers tax breaks, pools of cheap labour and long-term leases of fertile land at affordable rates.
An additional 1.2 million hectares (4,600 square miles) is earmarked for agricultural investors in Gambella over the next three years.
Authorities insist investment boosts development by creating jobs and spurring economic growth, but Human Rights Watch senior researcher Ben Rawlence said residents' needs are being overlooked.
"Everybody wants better access to services, the problem is how it happens," he told AFP by phone from London.
"The right of development is not just the right of the state to bulldoze land. It's also the right of the people to choose how they want to develop."
Human Rights Watch warns the resettlement programme is reminiscent of the "collectivisation" drive by the authoritarian military regime in the 1970s that forcibly relocated 13 million people -- often violently -- but ultimately failed because no services were provided. Thousands died as a result.
Milkesa Wakjira, processing coordinator for the Ethiopian-owned Saudi Star company, which rents a 10,000-hectare (40-square-mile) plot near Abobo, defended the leasing of land.
"This is not a question of land grabbing," he said, standing before a sprawling green rice paddy as tractors trundled by. "If the land belongs to the government, no one is in a position to grab it because if the government wants the land, they can take it back."
Wakjira said the community welcomes the new jobs and the company's efforts to pave the area's jumbled dirt tracks. Saudi Star has also given two cars to the local district and donated 200 beehives to local farmers.
But more than 50 percent of the rice Saudi Star grows here is exported, mainly to Saudi Arabia, Wakjira said.
Opening its doors to foreign investors is part of the government's ambitious Growth and Transformation Plan, which aims to boost Ethiopia's economic growth and reach middle-income status by 2015.
The International Monetary Fund says Ethiopia's economy is growing at a rate of 7.5 percent, though the government pegs growth at 11 percent. The country's main exports are livestock, coffee and agriculture.
Despite the scarcity of food and land, Thwol says he will tough it out in Abobo for now.
"School is here, clinic is here and small water is here," he said.
Even though his plot of land has shrunk, he prefers to be near these services, no matter how under-resourced they are.

የወዳጄ ምኞት እኔም የምጋራው

ይህ ወዳጄ ደጋገመኝ እኔም ለጠፍሁ ማንበብ የርሶ ነው

የተባረከው ወዳጄ ጩኸት

Blogger fights terror charges as Ethiopian leader praised

U.S. Secretary of State Hillary Clinton meets Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi at a conference in London in February. Western governments are hesitant to press Ethiopia on human rights abuses. (AP/Jason Reed)U.S. Secretary of State Hillary Clinton meets Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi at a conference in London in February. Western governments are hesitant to press Ethiopia on human rights abuses. (AP/Jason Reed)
[By Tom Rhodes/CPJ East Africa Consultant]
Last week in the Ethiopian capital, Addis Ababa, while Prime Minister Meles Zenawi was making a speech about Africa’s growth potential at an African Union forum, a journalist who his administration has locked away since September on bogus terrorism charges was presenting his defense before a judge. Eskinder Nega has been one of the most outspoken critics of Meles’ domestic leadership over the past two decades and has suffered imprisonment, intimidation, and censorship for it.
The veteran, dissident blogger has been jailed at least seven times by Meles’s government over the past two decades. He isn’t alone. Including Eskinder, there are five journalists imprisoned on politicized terrorism charges in Ethiopia. The threat of prison has induced many independent journalists to flee the country — the highest number of exiled journalists in the world, according to CPJ research.
Eskinder is facing a life sentence if convicted on terrorism charges for allegedly supporting a banned opposition party, Ginbot 7. Ethiopia’s antiterrorism law criminalizes reporting or publication of information the government deems favorable to groups designated as terrorists, which include opposition movements such as Ginbot 7.
The tiny, drab courtroom in Lideta High Court where Eskinder appeared Wednesday was one of the smallest in the building, eyewitnesses told me — a purposeful move to allow only 25 or 30 people to attend. Still, Eskinder’s supporters managed to cram into the room and noticed a more gaunt, pale
colleague whose sharp black suit and tie hid little of his deteriorating condition.
A three-judge panel listened as Eskinder described himself as a prisoner of conscience and rejected accusations that he had conspired to overthrow the government through publishing “inciting” articles and interviews to local
and international media houses. “I wrote about human rights and democracy and used my right to free expression to fulfill my duties as a concerned citizen,” Eskinder told the three judges. According to those in the courtroom, Eskinder went on to say he would accept any torture and imprisonment imposed by the state as “part of the price for fulfilling my duties.” He said the final judgment of the court is “being eagerly and curiously awaited by the public and history.”
One of the last columns Eskinder wrote before his arrest hinted at the fact that freedom from political tyranny was only a matter of time, citing the Arab Spring in North Africa as an example. Many local journalists suspect it was his repeated call for social change that incurred his arrest and led government spokesman Shimelis Kemal to accuse Eskinder and others in an Agence France-Presse interview of plotting “a series of terrorist acts that would likely wreak havoc.” But Eskinder, in his defense, insisted that he has always wanted political change through peaceful, democratic means since change through war would only lead to further dictatorship.
Eskinder’s wife, also an accomplished journalist who was jailed after the disputed 2005 elections, told Voice of America that Eskinder had been pleased with his defense but discouraged at having to battle the terrorist label. “He’s a journalist, not a member of a political party,” Serkalem Fasil told the U.S. government-backed broadcaster. Local journalists told me that VOA, one of the few stations reporting on the trial, was blocked the day after Eskinder’s hearing.
Fellow journalists and rights activists across the globe have organized a petition calling for the release of Eskinder; signees include the heads of the U.S. National Press Club, the Open Society Foundations, Human Rights Watch, and the Committee to Protect Journalists.
But will all this local and international support for a press freedom advocate be enough to sway policy? Ethiopia is viewed as a strategic partner for the West in combating terrorism and instability in the Horn of Africa, so Western governments are unlikely to press Meles on human rights abuses.
As Eskinder made an impassioned plea for his innocence, Meles Zenawi was honored across town as the AU
trade meeting
‘s special guest, a “leading advocate of the development state in promoting effective inclusive growth in Africa” and a champion of “development effectiveness.” But can you really be crowned a “champion of development” if you lock up all your critics? Ethiopians and the international community will never be able to truly determine whether the prime minister is an “advocate of the development state” if only yes-men and blind supporters are allowed to speak of his achievements.

Tuesday 3 April 2012

UN experts urge probe of Ethiopian maid suicide in Lebanon

UN human rights experts on Tuesday urged the Lebanese government to investigate the death of an Ethiopian housemaid, who commited suicide a few days after she was beaten by a man in Beirut.
Alem Dechasa, 34, hung herself with a bed sheet on March 14 at a psychiatric hospital east of Beirut, where she had been taken by police after the February beating that was aired on Lebanese television.
"Like many people around the world I watched the video of the physical abuse of Alem Dechasa," said Gulnara Shahinian, the UN expert on contemporary forms of slavery, in a statement.
"I strongly urge the Lebanese authorities to carry out a full investigation into the circumstances leading to her death," she added.
UN officials including anti-torture rapporteur Juan Mendez, migrant expert Francois Crepeau, rapporteur on violence against women Rashida Manjoo as well as a member of the working group on discrimination against women Kamala Chandrakirana echoed the call.
They also demanded that results of the investigation be made public.
The video footage showing a man dragging Dechasa by the hair and kicking her outside Ethiopia's consulate had sparked national outrage.
The man owned the employment agency that recruited the Ethiopian woman, according to local news reports.
Shahinian said the footage "reminded me of the many migrant women workers I met in Lebanon during my official visit to the country" in October 2011.
"Women who had been victims of domestic servitude told me they had been under the absolute control of their employers through economic exploitation and suffered physical, psychological and sexual abuse," she said, calling on the Lebanese government to enact legislation to protect the 200,000 domestic workers in the country.
"States are under an obligation to ensure the realization of the right to truth about violations in order to end impunity and promote and protect human rights and provide redress to victims and their families," she added.

Monday 2 April 2012

(እግር ኳስን በብሎግ ይመልከቱ) by Abe Tokechaw

ኢህአዴግ አታሎ ለአባይ አሻማ! (እግር ኳስን በብሎግ ይመልከቱ)
ውድ ተመልካቾቻችን ጨዋታው ከተጀመረ ሃያ አመት ሞልቶታል። እስከ አሁን ድረስ ኢህአዴግ በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የማጥቃት እርምጃ ወስዷል። በእውነቱ ህዝቡ ዘንድ ኳስ ሊደርስ አልቻለም።

እስከ አሁን አስደንገጭ የሚባል ሙከራ የተሞከረው በ1997ኛው ደቂቃ ነበር። በእውነቱ ይህ ሙከራ ሙከራ ብቻም አልነበረም። እኛ ራሳችን በአይናችን እንዳየነው ጎሉ ገብቶ ነበር። ነገር ግን ለኢህአዴግ ተከላካይ ሆኖ ሲጫወት የነበረው ፌደራል እና አጋዚ የተባለው እውቅ በረኛ ኳሷን ከገባችበት አውጥተዋታል። እውነቱን ለመናገር ህዝቡ በህብረት እና በቅንጅት ማራኪ የጨዋታ እንቅስቃሴ ካደረገ በኋላ፤ ወደ ጎል የመታት ኳስ ከመርብ ጋር ተነካክታ ነበር። ምን ዋጋ አለው ዳኛው አልገባም አሉ። የሚገርም ነው!

ህዝቡ በዳኛው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰማ ነበር። በዚህ ግዜ የኢህአዴግ አምበል የሆኑት መለስ ዜናዊ ፊሽካውን ከዳኛው ተቀብለው “ጎሉ አልገባም ብያለሁ አልገባም” ብለው ህዝቡ ተቃውሞውን እንዲያቆም አስጠነቀቁ። ይሄ በእውነቱ በየትኛውም ጨዋታ ታይቶ የማይታወቅ ክስተት ነው። ዳኛ እያለ የተቃራኒ ቡድን አምበል ማስጠንቀቂያም ሆነ ፍርድ አይሰጥም። የ… ሚገርም ነው።

በነገራችን ላይ በዚች ጎል የተነሳ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ የኢህአዴግ ተጫዋቾች በመቶዎች የሚቆጠሩ የህዝቡ ደጋፊዎችን ገድለዋል። ኦ… በጣም ዘግናኝ ነበር። ይሄ በአለም የጨዋታ ህግ ክፉኛ የሚያስጠይቅ ነው።

ለማንኛውም አሁንም ጨዋታው ቀጥሏል። ህዝቡ እስከ አሁን ድረስ ይሄ ነው የሚባል ሙከራ አላደረገም። ኢህአዴግ ግን ተደጋጋሚ የማጥቃት እርምጃዎችን እየወሰደ ነው። የሚገርም ጨዋታ ነው።

በአሁኑ ሰዓት ኳስ በህዝቡ ሜዳ ላይ ብትሆንም ኳሷን የያዙት የኢህአዴግ አጥቂዎች ናቸው። ትንሽ ግራ የተጋቡ ይመስላል።

በነገራችን ላይ ተመልካቾቻችን ከኢህአዴግ ጋር ተመሳሳይ የጨዋታ ስልት ሲጠቀሙ የነበሩ በርካቶች በቅርብ ግዜያት በተጋጣሚዎቻቸው ተሸንፈው ከሜዳ ወጥተዋል። በቤን አሊ የሚመራው የቱኒዚያው ቡድን በህዝቡ ክፉኛ ከተሸነፈ በኋላ የግብፁ ኦስኒ ሙባረክ እንዲሁም የሊቢያው ጋዳፊ ቡድንም በተጋጣሚያቸው ህዝብ ሽንፈትን ቀምሰዋል።

እንግዲህ ተመልካቾቻችን ይህ በኢህአዴግ ላይ ትንሽ ግራ መጋባት ሳይፈጥርበት አይቀርም የሚል ግምት አለ።

ሆኖም ኳስ አሁንም በኢሀዴግ እጅ ነች። የኢሃዴግ ሰዎች በህዝቡ ሜዳ ኳሷን ይዘዋታል። እያታለሉ ነው። (…. ተመልካቾቻችን አጠገቤ ያለው ባልደረባዬ እያጭበረበሩ ነው በል ነው የሚለኝ…. ኦ….ያያያያ… እያጭበረበሩ ነው….የሚገርም ገለፃ ነው)

ተመልካችቻችን ጨዋታው ከተጀመረ ሃያ አመት አልፎታል። አንዳንድ የህዝቡ ደጋፊዎች “ኢህአዴግ ደክሞት ኳሱን ካላቆመ ጥቃቱ የሚቻል አይደለም ” የሚል አስተያየት እየሰጡ ነው። ሌሎች ደግሞ ከመቼውም ግዜ በተለየ ጥቃቱን ለመከላከል ብሎም ለማጥቃት ቁርጠኛ አቋም ይዘዋል።

አረረረ… አህአዴግ አልተቻለም ኳሷን ለኑሮ ወድነት አቀበላት። በእውነቱ ይሄ ከባድ ጥቃት ነው። ኦያያያ… ይሄ አደገኛ ኳስ ነው።

በኢህአዴግ ዘመነ መንግስት እያደገ የመጣው፤ ቁመተ ዘላጋው እና አረበ ሰፊው የኑሮ ውድነት በተደጋጋሚ ኳስ ያየዘ ቢሆንም የአሁኑ ግን የከፋ አያያዝ ነው። ኳሱን ለማንም አልሰጠም እንቅ አድሮጎ ነው የያዘው። ኦያያያ… ኢህዴግ ሌላ ኳስ ወደ ሜዳው አስገባ የሚገርም ጨዋታ ነው።

በእውነቱ ህዝቡ በተጫዋቾቹ ተስፋ እየቆረጠ ነው። እስከ አሁን ይሄ ነው የሚባል ጥቃት ማድረስም ሆነ መከላከል አልቻሉም። ስለሆነም ህዝቡ እንደ አረቡ አገራት ህዝቦች ወደ ሜዳ ለመግባት ያቆበቆበ ይመስላል። ኢህአደግ ኳሷን አሁንም ይዟል። እያታለለ ነው።

ኳስ በህዝቡ ሜዳ ላይ ነች ኢህአዴግ የህዝቡ አሳብ ሳይገባው አይቀርም። ህዝቡ ወደ ሜዳው ከገባ ከባድ ችግር ላይ ይወድቃል። ከሷን እያንከባለለ ነው። የሚያሻማ ይመስላል። አሻማ! ኦያያያያ… ኳስ በቀጥታ የህዝቡ ተጫዋች ወደ ሆነው አባይ ደረሰው።

የሚገርም ነው የኢህአዴግ ተጫዋቾች የህዝቡ አዝማሚያ የገባቸው ይመስላሉ። በተለይ ኳስ ለኑሮ ውድነት በተደጋጋሚ ከደረሰች በኋላ ህዝቡ የደረሰበትን ጥቃት መቋቋም አልቻለም። በመሆኑም ህዝቡ የአረቡን ሀገር የጨዋታ ስልት ይጠቀማል የሚል ስጋት በኢህአዴግ ተጫዋቾች ዘንድ ተፈጥሯል። ለዚህም ይመስላል ምንም ባልታሰበ መልኩ በድንገት ኳሷን የህዝቡ ተስፋ በመባል ለሚታወቀው እና ለግብፅ ብሄራዊ ቡድን በመጫወት ከፍተኛ ቁጭት ሲፈጥር ለነበረው የህዝቡ ወሳኝ ልጅ አባይ ሰጥተዋል። ምን ነካቸው። በእውነቱ ግራ የሚያጋባ ጨዋታ ነው። አባይ ከዚህ በፊት ለኢህዴግ እንደሚጫወት ውልም፣ ፊርማም፣ ሃሳቡም አልነበረውም። የኢህአዴግ ተጫዋቾችም አስበውት አያውቁም ነበር።

ኦያያያ… አባይ ምንም ባልተዘጋጀበት ሁኔታ ኳስ ደርሶታል። የሚገርም የጨዋታ ስልት ነው። አሁን ህዝቡ በተደበላለቀ ስሜት ውስጥ ይገኛል።

ኢሀዴግ በዚህ በኩል ህዝቡን በኑሮ ውድነት እያጠቃ ነው። በተጨማሪም የህዝቡ ተከላካይ የሆኑ ሀይማኖት የተባሉ እውቅ “ዲፌንሶች” ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው።

አዎ… ሌላም አለ። ኢህአዴግ ለሽብርተኝነት ባቀበለው ኳስ በርካቶችን ከጨዋታ ውጭ ኦፍ ሳይት ለማድረግ ሞክሯል። ኢህአዴግ “ይህንን ተጫዋች የገዛሁት ምርጥ ተሞክሮ ካላቸው አገራት ነው” ቢልም ይህ ሽብርተኝነት የተባለው ተጫዋች ግን እጅግ በጣም ያልተገባ ጨዋታ እየተጫወተ ይገኛል። በርካቶች “እርሱ እያለ መጫወት አልቻልንም” ብለው ከጨዋታ ሜዳው እርቀዋል። በነገራችን ላይ ይህ ተጫዋች አንዳንዴ ኳስ ወደ “ኮሚታተርስ” ወይም የጨዋታው ዘጋቢዎች ሳይቀር እየለጋ የዘገባ ስርዓቱን አስተጓጉሏል። አንዳንድ የኳሱ ዘጋቢዎችም መዘገብ አልቻልንም ብለው ትተውታል። ሆኖም ኢሃዴግ “ምርጡ ተጫዋቼ ነው” እያለ ይገኛል። እርሱም ማጥቃቱን ቀጥሏል።

ተመልካቾቻችን አሁን ኳስ ለአባይ ደርሳለች። አባይ ኳሷ ድንገት ስለደረሰችው የተደናገጠ ይመስላል። ኳስ ከያዘ በኋላ ሜዳው ላይ ባልተለመደ መልኩ ሚሊኒየም የሚል መለያውን ቀይሮ ህዳሴ የሚል ሌላ መለያ ለብሷል። በእውነቱ ይሄ የሚያስቅ ነው። ኳስ አመታቱም ግራ የሚያጋባ ነው አንድ ግዜ አምስት ሺህ ሌላ ግዜ ደግሞ ስድስት ሺህ ይለጋል። ኦያያያ… አባይ ምንም አልተዘጋጀም። ኢህአዴግ አሁን አባይን እንደ ራሱ ተጫዋች እየቆጠረው ነው። አታለል… ኢህአዴግ አታለል!!! ህዝቡም በአባይ አጨዋወት ግራ ቢጋባም ተወዳጅ ተጫዋች በመሆኑ እየዘመረለት ይገኛል። ኦ ያያያ… የኢህአዴግ አጨዋወት ግራ ነው የሚያጋባው።

ተመልካቾቻችን ጨዋታው እንደቀጠለ ነው። የኑሮ ውድነቱ ኳሷን እንደያዘ ነው። በመከላከል ረገድ የህዝቡ አለኝታ የሆኑ ሃይማኖቶች አሁንም ከኢሃዴግ አጥቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል። ከህዝቡ ወገን የነበሩ አንዳንድ “ሀብቴ የህዝብ ፍቅር ነው” ሲሉ የነበሩ አርቲስቶች ከኢህአዴግ ጎን ተሰልፈዋል።

አሁን ኳስ በአባይ እጅ ትገኛለች። ህዝቡ በጣም የሚያደንቀው ተጫዋች አባይ ኳስ የደረሰው ምንም ባልተዘጋጀበት ሁኔታ ስለነበር፤ የተለያዩ አስገራሚ ትዕይንቶችን እያከናወነ ነው። ለህዝቡ በአጥቂነት የሚጫወቱ ተጫዋቾች አባይ ላይ እያጉረመረሙበት ይገኛሉ። አጥቂዎቹ እንደሚሉት ከሆነ “አባይ በደንብ ተዘጋጅቶ መጫወት አለበት!” ሳይዘጋጅ የሚያደርገው ጨዋታ መልሶ ህዝቡ ላይ ጉዳት ሊያመጣ ይችላል በሚል ስጋታቸውን እየገለፁ ነው። በእውነቱ አባይ ኳስ ይዞ እያሟሟቀ ነው። ወደ ሜዳ ሳይገባ በፊት ነበር ማሟሟቅ የነበረበት። ይሄ ጡንቻ መሸማቀቅም ሊያመጣ ይችላል እያሉ የህዝቡ ወጌሻዎች እየተናገሩ ነው።

ተመልካቾቻችን ጨዋታው ከጀመረ ሃያ አንድ አመት ሊሞላው ነው። ኢህአዴግ አሁንም በጥቃቱም በማታለሉም አልተቻለም።

የህዝቡ እውቅ አጥቂ የነበሩት ቅጅት እና ህብረት የተባሉ ታዋቂ ተጫዋቾች በወቅቱ በደረሰባችው ጉዳት በአሁኑ ግዜ በሜዳው ላይ አይታዩም። አሁን ለህዝቡ ትንሽ እንቅስቃሴ የሚያደርጉት ከመሀል መድረክ እና መኢአድ የተባሉ ተጫዋቾች ናቸው። ህዝቡ ተናበቡ እያለ እያጉረመረመ ይገኛል።

ራቅ ብሎ የኢህአዴግን ማጥቃት ለመከላከል አዲሲቷ ኢትዮጵያ ንቅናቄ እና ዲያስፖራው ማህበረሰብ በመባል የሚታወቁት ተከላካዮች በሰላማዊ ሰልፍ እና በማመልከቻ ጥቃቶችን ለመከላከል እየሞከሩ ይገኛሉ።

እንዲሁም በክንፍ በኩል ራቅ ብለው ለማጥቃት የተዘጋጁ ግንቦት ሰባት፣ አርበኛ እና ኦነግ የተባሉ አጥቂዎች አሉ። በነገራችን ላይ እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ ኦነግ ለራሴ ብድን ነው የምጫወተው ብሎ የቆየ ቢሆንም በቅርቡ ግን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የሆነውን የህዝቡን መለያ ለብሶ ከህዝቡ ጎን ለመጫወት ፈርሟል። ይህ ተጫዋች በተለይ በማጥቃቱ የረጅም ግዜ ልምድ ያለው መሆኑ ይታወቃል።

የሆነ ሆኖ ኢህአዴግ እያታለለ ነው።

ጨዋታው መቼ እንደሚያልቅ እኔንጃ እኔም ደከመኝ!

መልካም ውጤት ለብዙሃኑ እመኛለሁ አረፍ አረፍ እያልኩ ዘገባውን አቀርባለሁ መልካም ዕድል!

ኃይሌ የወርቃማው እግሮችህ ውለታ በምላስህ እንዳይደበዝዙ!

ኃይሌ የወርቃማው እግሮችህ ውለታ በምላስህ እንዳይደበዝዙ!
ሙያን ለባለሙያ አለመተው የሀገራችን ዋነኛ ችግሮች አንዱ ነው።በጨረባ ለብለብ ሰርተፊኬት፣ በፓርቲ አባልነት፣በሬድዮ አንድ ዙር ድራማ አርቲስት የሚለውን ታፔላ የለጠፉ ሞራልም ብቃትም የሌላቸው ጋዜጠኛ ብጤዎች እንደ ኢትዮፒካው ብርሃኔ ንጉሴ (በአማርኛ ዝግጅት አቅራቢ አማርኛን አስቦ የሚያወራ) ሰይፉ ፋንታሁን (የሸገር አራዶች ሰፊአፉ ይሉታል)የሀገራችንን ወግና ባህል
በ፵ዓመቱ ያልገባው የትልቅ ቀላል የሆነ ጎርፍ ያመጣው ጋዜጠኛ ኃይሌን ይዞት ገደል ገብቷል።በዓለም ላይ ቀላሉ ነገር ምክርና ቦክስ ነው፣ለሰጪው እንጂ ለተቀባዩ ከባድ ነው።የኦሎምፒክ ሻምፒዮኑ ኃይሌ፣ ሰንደቃችንን ከፍ አድርጎ ሀገራችንን ያስጠራት ኃይሌ፣ድህነትን ጣዕሟን ቀምሷት ያደገው ኃይሌ በመምህራኖች ጉዳይ ላይ አስተያየት መጠየቅም አልነበረበትም፣ቢጠየቅም ስለ መምህራን የሚያገባው ነገር፣የሚመለከተው ጉዳይም አይደለም።ኃይሌን አዘንኩበት።
ዛሬ መሞዳሞድ መሸፋፈን የለብንም አካፋን አካፋ ማለት አለብን።ኃይሌ ስለ መምህራን ከሚዘባርቅ፣ የመለስ መንግስት ከሱ ክብረወሰን በፈጠነ ማይክሮ ሰከንድ ልማቱን አፋጥኖ ሀገራችንን እንደሚያሳድግ ከሚሰብከን፣ባደገበት የአርሲ ገጠር መንደር ውስጥ ሌት ከቀን የሚማስኑ ታታሪ አርሶ አደሮችን ስራ የማይወዱ ህዝቦች ብሎ በጅምላ ከሚፈርጅ የሀይማኖት ሊቅ ይመስል ዐመት በዐላት በዙ ብሎ በማያገባው ጥልቅ ከሚል ለምን ስለ እራሱ በትክክል አይመልስም?
ስለ ኃይሌ ወደዳችሁም ጠላችሁም እውነታውን እነግራችኋለሁ።መርማሪ ጋዜጠኞች፣የታሪክ ተመራማሪዎች ፍንጩን ይዛችሁ ድረሱበት ኃይሌ ሆላንድ ውስጥ ወጣት ሆኖ ለተወሰነ ጊዜ ኖርዋል በወቅቱ ከታላቅ ወንድሙ ጋር ሆላንድ ውስጥ ሲቀመጥ የነበረውን የሩጫ ብቃት ሲያየው ለሆላንድ ቢሮጥ ከፍተኛ ቀረጥ(ግብር)መክፈል፣የማስታወቂያ ገቢዎች ማሳወቅ፣ሀብት ማስመዝገብ፣የገንዘብ ዝውውርና የስጦታ ሽልማቶችን ማስመዝገብ፣ለታዋቂ ሰዎች የሚጣለው የማህበራዊ አገልግሎት ወጭዎች ወዘተ...እጁ ለማይፈታው፣ወርቃማ እግሮች እና ረዥም ምላስ ለታደለው ኃይሌ አልተዋጡለትም። ሆላንድን ትቶ ለሀገራችን የሮጠው በነደደ የሀገር ፍቅር ስሜት ብቻ ነው ብላችሁ አታስቡ(ግን እንኳን እሮጠልን)በዓለም አቀፍ የስፖርት ህግ የሚገዛ ሰው ቢሆንማ ኖሮ ስለ አለው ሀብት ሲጠየቅ የወንድ ልጅ ደመወዝና የሴት ዕድሜ አይነገርም የሚባለውን የባልቴት ተረት ባልተረተብን ነበር፣ ከማስታወቂያ ስንት ታገኛለህ? ሲባል የሀገር ውስጡ ብዙ አይደለም የውጭው ይሻላል ግን ምን ያረግልሀል? አይልም ነበር።ገቢን ማሳወቅ ግዴታ ነው፣የዴቪድ ቤክሀም፣የሊዮነል ሜሲ፣የሁሴን ቦልት፣የኖቫክ ጆኮቪች የታላላቅ ስፖርተኞች ሳምንታዊ ዐመታዊ ገቢያቸው ይታወቃል።ኃይሌም ገቢውን ማሳወቅ አለበት ኢትዮጵያም ከዓለም አቀፉ የስፖርት ስነምግባር መርሆዎች ውጭ መሆን የለባትም። ስለ መምህራን ሳይሆን ስለ እራስህ ንገረን ኃይሌ፣ስንት ገንዘብ በባንክ አለህ?ምንያህል መዋዕለ ንዋይህን አፍስሰሀል?ከማስታወቂያ ገቢ ስንት ይደርስሀል?ምን ያህል በመቶኛ ግብር ትከፍላለህ?እነዚህንና ተዛማጅ ጥያቄዎችን ካንተ መልስ እንሻለን።የመምህራኖችን ጉዳይ የትምህርት ሚንስቴር ከመንግስት ጋር የሚወጣው ጉዳይ እንጂ አንተንም ሰፊአፉን ይቅርታ ሰይፉን ማለቴ ነው አያገባችሁም። አሁንም ለሀገራችን የዋልከውን ውለታ ዘንግቼ አሊያም፣በጥላቻ ውስጥ በስሜት ተመርቼ አስተያየቴን እንዳልሰጠሁኝ ልነግርህ እወዳለሁ።አንተን ጠርተው ነው ሀገራችንን የሚጠሩት፣አንተን ጠርተን ነው ደረታችንን የምንነፋው ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ እንዲል ይደረክ ብሔራዊ ጀግናችን ነህ አሁንም የአደባባይ ጀግናችን ነህ።የራሴን ፌስቡክ ገብተህ ብታየው ምስልህን ታየዋለህ።ነገር ግን ባንዴራችንን ከሚዘቀዝቁት ጎራ አትሰለፍ።የወርቃማው እግሮችህ ውለታ በምላስህ እንዳይደበዝዙ።ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

As separatists in Ethiopia disarm, a new chapter for D.C.’s Oromo community


(Jonathan Newton/ The Washington Post ) - Taha Tuko, the local leader of the Oromo Liberation Front, is calling for unity with other Ethiopians in Washington and back home.
On a windy Saturday afternoon at a small Petworth cafe, Taha Tuko orders a round of celebratory macchiatos for three of his countrymen and tells them their 38-year armed struggle for secession from Ethiopia is over — fighters back in Africa have laid down their arms.
The dream of an independent Oromia long cherished by Tuko and other Oromo Ethiopians might never be realized. Their revolution is being repurposed with a new goal: uniting with other Ethio­pian opposition parties in the Washington region against the regime of Prime Minister Meles Zenawi, which they all accuse of being autocratic and corrupt.

“The violence is over, and this is good news!” insists Tuko, the Washington region leader of the now retooled Oromo Liberation Front (OLF), one of the factions that fought for an independent Oromia. “But our mission is no longer for independence. We’ll be one with the Ethiopian community now. Both back home and here in Washington.”
Washington is home to an estimated 100,000 Ethio­pian immigrants — the largest concentration in the United States — including ethnic Oromos such as Tuko, from central and southern Ethi­o­pia, as well as a half-dozen other ethnic groups, such as the Amharas from the eastern and central highlands and the Tigrayans from the northern highlands.
But what happens to diasporas of this kind when a revolution or a political movement dies? Does everyone just go out for coffee, become friends, start working together? Sometimes. Older political factions from Washington’s Salvadoran diaspora, for example, still come together every year to honor the end of the Central American country’s civil war 20 years ago because it was so powerful in uniting the community here.
* * *
The Oromo countrymen, a cook, a cab driver and a teacher, pull off chunks of injera, Ethiopia’s crepelike flatbread, and use it to sop up a traditional lunch of goat and vegetables, washing it down with the customary glass of milk. The Georgia Avenue cafe is called A Land of Medicine, after an Oromo city. Grainy Oromo music videos play on a beat-up television — flashing images of Oromia’s lush barley- and coffee-growing regions — as each of Tuko’s guests share harrowing stories about friends and relatives hauled off to jail in the middle of dinner or found dead after being assaulted. Oromos, 50 percent of whom are Muslim, are Ethiopia’s largest ethnic group, and the men and women talk about religious persecution and attempts to limit their political power in the majority Christian Ethio­pian Orthodox country.
The OLF, one of the world’s long-running insurgent groups, was so active in Washington that it had offices in a Takoma Park bungalow, a U Street rowhouse and a commercial building in Petworth that now has a “For Rent” sign out front. The group organized Howard University political rallies, functions at Oromo churches and mosques and high-level meetings with Congress — even a Miss Oromo-North America beauty pageant.
Those events will continue, Tuko promises the crowd, just with a different spin.