Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 22 September 2012

ቤተ መንግስቱ ኃይለማርያምን ያሰራ ይሆን?…………..ከፍኖተ ዘመቻ ነጻነት “እናሸንፋለን” we will win (www)



ላለፉት 21 አመታት የምኒሊክ ቤተ መንግስት ለአንድና ለሁለት ቀን ግፋ ሲልም ለአንድ ሳምንት ካልሆነ ጌታውን አጥቷቸው አያውቅም፡፡ አቶ መለስ በግንቦት

ወር በቡድን ስምንት ጉባኤ ከተካፈሉ በኋላ ግን ማንንም አምነው የማይርቁትን ቤተመንግስት በህመም ምክንያት ትተው ብራስልስ ከረሙ፡፡ ህመማቸው እና አማልክቱ ጨክነውም ዳግም ወደ ምኒሊክ ቤተ መንግስት በቁማቸው ሳይመለሱ ቀሩ፡፡ እናም ቤተመንግስቱ ላለፉት ሦስት ወራት ኦና ሆኗል፡፡ ሀገሪቱን ማን የት ተቀምጦ እንደሚመራት ብዙም ግልጽ ባይሆንም፣ ኃለማርያም ደሳለኝ በተጠባባቂነት ሀገሪቱን እየመሩ እንደሆነ ሲገለፅ ሰንብቷል፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ ባለፈው አርብ መስከረም 4 ተጀምሮ ቅዳሜ መስከረም 5 ቀን 2005 . የተጠናቀቀው የገዢው አብዮታዊ ፓርቲ ምክር ቤት ስብሰባ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን በሟቹ ሊቀመንበሩ ምትክ ቢያስቀምጥም፣ ሰውየው እስከወሩ ማገባደጃ ቃለ መሀላ ፈፅመው ወደ ቤተመንግስት አይገቡም፡፡ ሁኔታው ኢህአዴግ ኃይለማርያምን ቤተመንግስት ከማስካባቱ በፊት ማጠናቀቅ የፈለገው ስራ እንዳለ አመላካች ነው፡፡ ኢህአዴግ 21 አመት በኋላ ከህወሓት ውጪ የሆነን ግለሰብ ለፓርቲው
ሊቀመንበርነት በመሾሙ በፓርቲው የውስጥ ፖለቲካዊ የኃይል አሰላለፍ ላይ ለውጥ መጥቷል ለማለት ያስችላል? የአቶ ኃይለማርያም ፖለቲካዊ ተክለ ስብዕናስ እንደ መሪ ውሳኔዎችን ለመስጠት የሚያስች ይሆን? ለእነዚህ ጥያቄዎች ቀጣዩ ፅሁፍ ምላሽ ይሰጣል፡፡

የኢህአዴግ የኃይል አሰላለፍ ለውጥ አሳይቶ ይሆን?

ኢህአዴግ ላለፉት አመታት ከህወሓት ተፅእኖ ስር ተለይቶ አያውቅም፡፡ የአራት ፓርቲዎች ስብስብነቱም አፋዊ ከመሆን ያለፈ አልነበረም፡፡ ህወሓት ያቀደው፣ ህውሓት ያቦካውና የጋገረውን ተቀብሎ ከማስተጋባት ውጪ ህወሓትን የሚገዳደር አንድም አባል ድርጅት ያልነበረው ኢህአዴግ፣ ለህወሓት አንደኛ፣ ለብአዴን ሁለተኛ፣ ለኦህዴድ ሦስተኛ እንዲሁም ለደኢህዴን የአራተኛነት ደረጃ የሰጠ ውስጣዊ የኃይል አሰላለፍ ነበረው፡፡

የህወሓትም ሆነ የኢህአዴግ ጭንቅላት ተደርገው የሚወሰዱት መለስ ዜናዊ ከሞቱ በኋላ ግን የኢህአዴግ ውስጣዊ የኃይል አሰላለፍ እንዲቀያየር የሚያስገድድ ሁኔታ ተከስቷል፡፡ ለፓርቲው ቅርብ የሆኑ ወገኖች እንደሚገልፁት ህወሓት በአቶ መለስ ላይ ከተገቢው በላይ በመተማመመን ተተኪ ሰው ባለማዘጋጀቱ በኢህአዴግ ውስጥ የነበረውን ተፅእኖ በቀላሉ ለማጣት ተገዷል፡፡ በብአዴን ውስጥ አዳዲስ ፊቶች በፊት እንዲመጡ ባይደረግም ቅሉ ፓርቲው ከአቶ መለስ በኋላ አለቅነቱ ለኔ ይገባኛል የሚል የተሳካ እንቅስቃሴ ማድረጉንም እነዚሁ ወገኖች ያስረዳሉ፡፡ ኦህዴዶች በስልጣን ሽኩቻ ላይ ብዙም አልተሳተፉም፤ ከብአዴን ጋር የነበራቸውን ዘመን ያስቆጠረ የመቀናቀን አዝማሚያ ላለማድረግ የተገደዱ ይመስላል፡፡ አሁን ከሞላ ጐደል ኢህአዴግ ውስጥ ብአዴን ጠንከር ያለ ባይሆንም መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል የበላይነት ይዟል፡፡

የአቶ መለስ መቃብር በልዩ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው…………..ከፍኖተ ዘመቻ ነጻነት “እናሸንፋለን” we will win (www)



አስከሬኑ ከነሰንደቅ ዓላማው መቀበሩ አነጋጋሪ ሆኗል


አራት ኪሎ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የተቀበሩት የኢፌዲሪ / ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ መቃብር ልዩ ጥበቃ እየተደረገለት እንደሆነ ተገለፀ፡፡
ምንጮቻችን እንደሚሉት አቶ መለስ ከተቀበሩ በኋላ ባልተለመደ ሁኔታ የቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በሮች የተቆለፉ ሲሆን መቃብሩ በተለየ ኃይል ልዩ ጥበቃ እየተደረገለት ነው፡፡ የመረጃ ምንጮቹ ጨምረው እንደገለፁት ከቀብሩ በኋላ በወክማ ወይም በመንፈሳዊ ኮሌጁ አቅጣጫ ያለው በር ሙሉ በሙሉ ተቆልፎ የሚውል ሲሆን ቀን ቀን በዋናው በር ወደ ቤተክርስቲያኑ የሚገባ ካለ የት እንደምሄድ ለምን መግባት እንደፈለገ ተጠይቆ ከታመነበት ብቻ እንደሚገባና ሲገባና ሲወጣም ከትትል ይደረግበታል፡፡

ምሽት ላይ የዋናው በር የሰው መግቢያ ብቻ የሚከፈት ሲሆን በርካታ ሰው ለፀሎት የሚገባ ቢሆንም የአቶ መለስ የቀብር ቦታ በልዩ ጥበቃ እየተጠበቀ ነው፡፡ በቀብሩ ዕለት አስክሬኑ የለበሰው የሰሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ አብሮ መቀበሩ በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ቅሬታን የፈጠረ ከመሆኑም በላይ የተለያዩ ትርጉም እየተሰጠው ይገኛል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ከአስክሬን ጋር ይቀበራልን በማለት የጠየቅናቸው አንዳንድ ሰዎች በሰጡን አስተያየትየኢህአዴ መንግስት በአገር ሰንደቅ ዓላማ ላይ ሲፈጽም ከቆየው ጥፋት አሁንም አለመላቀቁን ያሳየበት ነው፡፡ የአንድ ሉዓላዊ አገር ባንዲራ አይቀበርም፡፡

ሰንደቀ ዓላማ ከማንም በላይ ነው፡፡ ማንም ይሙት ማን የአገር ባንዲራ አብሮ የሚቀበርበት ህግ የለም፡፡ ታሪካዊ ወንጀል ተፈጽሟልሲሉ ተችተዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አቶ መለስ ከሁለት ወር በላይ ያሉበት ሁኔታ አለመታወቅና ሞቱ ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ አስክሬናቸው እንደ አንድ የአገር መሪ በግልጽ በመስታወት አለመታየቱ በህብረተሰቡ ዘንድ አነጋጋሪ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች እደሚሉት ኢህአዴግ የአቶ መለስን መታመም ለብዙ ጊዜ ደብቆን ቆይቷል፡፡ ሞቱ ብሎ ከነገረን በኋላ ህክምናቸውን ሲከታተሉበት የነበረውን ሆስፒታል ደበቀ፡፡ የህክምና ማስረጃቸውንም ይፋ አላደረገም፡፡ከዚህም አልፎ ተርፎ
አስክሬናቸውንም አላሳየንም፡፡ ከተቀበሩም በኋላ አስክሬኑን አሁን ባለው ሁኔታ መጠበቅ ለምን አስፈለገ ከአስክሬኑ ሳጥን ጀርባ ምን ሚስጥር አለ?” በማለት ያላቸውን ጥርጣሬ ገልፀዋል፡፡

በተለይ የመቀሌ ነዋሪዎች የአቶ መለስ አስክሬን አለመታየት በግልጽ ሚስጥሩ ምንድ ነው የሚል ጥያቄ አንስተው እንደነበረ የመረጃ ምንጮቻችን ከሥፍራው ገልፀዋል፡፡ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጆች በቀብሩ እለት በሥፍራው ተገኝተው የቀብሩን ሥነ ሥርዓት እንዳይዘግቡ በመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የተከለከሉ በመሆናቸው በሥፍራው ተገኝተው መዘገብ አልቻሉም፡፡ ከቀብሩ በኋላም በህዝብ የሚነሱትን ጥያቄዎች ለማጣራት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡