Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 12 May 2012

በውጭ የሚገኘው ሲኖዶስ በሙስሊሞች ላይ የተፈጸመውን ግድያ አወገዘ

ግንቦት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅዱስ ሲናዶስ፤  በአርሲ-አሰሳ የመብት ጥያቄ ባነሱ ሙስሊሞች ላይ የኢህአዴግ ታጣቂዎች  ተኩስ በመክፈት  የፈፀሙትን ግድያ አጥብቆ አወግዟል።
ሲኖዶሱ  በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመውን ግድያ እና አሁንም እየተፈፀመ ያለውን  በደል ያወገዘው ሰሞኑን ያካሄደውን 33 ኛ ጉባኤውን ሲያጠናቅቅ ባወጣው የአቋም መግለጫ ነው።
ሲኖዶሱ በዚሁ የአቋም መግለጫው በአሰሳ-መስጊድ የተፈፀመውን ግድያ ከማውገዝ በተጨማሪ፤ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ህገ-መንግስቱ በፈቀደላቸው መሰረት  ሀይማኖታቸውን በነፃነት እንዳይከተሉ መንግስት ጣልቃ እየገባ በተለያዬ መንገድ ከሚያደርግባቸው ጫና በአስቸኳይ እንዲቆጠብ ጠይቋል።
ሀይማኖታዊ መብትን ከማስከበር እንቅስቃሴው ጋር ተያይዞ የታሰሩት ሙስሊም ወንድሞችና እህቶችም ፤ በቶሎ እንዲፈቱ ሲኖዶሱ አሣስቧል።
ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች ተዋደው እና ተከባብረው ከሚኖሩባቸው የዓለማችን አገሮች ኢትዮጵያ በግንባር ቀደምነት የምትጠቀስ እንደሆነች መረጃዎች ያሳያሉ።
ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን- በቅጽል ስሙ ቴዲ አፍሮ በምርጫ 97 ዋዜማ ባሰማው “ሸመንደፈር”የተሰኘ ሙዚቃው፦
“ሸገር አዲሳባ-አንች ያለሽበቱ፣
ራጉኤል አይደል ወይ-የአንዋር ጎረቤቱ፣
ቅዳሴ እና አዛኑን-አጥር ቢለያቸው፣
ፈጣሪ ከሰማይ-ባ’ንድነት ሰማቸው” በማለት፤ በኢትዮጵያ በሁለቱ እምነት ተከታዮች ዘንድ ያለውን ተከባብሮ እና ተዋዶ የመኖር ታሪክ እና እውነታ ይታወሳል።
ህዝባዊ ተቀባይነቱ በመሟጠጡ ከፍ ያለ ፖለቲካዊ ኪሳራ ውስጥ የሚገኘው ገዥው ፓርቲ፤ በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሁለቱን እምነት ተከታዮች ለማጋጨት፣  በጥርጣሬ ለማስተያዬት እና በዚህም ህዝቡ በአገራዊ ጉዳዮች ላይ አንድ ላይ እንዳይቆም ለማድረግ በተደጋጋሚ አደገኛ ቅስቀሳዎችን ሲያደርግ መቆየቱን ብዙዎች ይናገራሉ።
በቅርቡ ብዙሀን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መብታቸውን ለማስከበር እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ተከትሎ ፦አንድ ጊዜ “አክራሪዎችና አሸባሪዎች እየተስፋፉ ነው”  በማለት የነዛው ፕሮፓጋንዳ ህዝባዊ ተቀባይነት ሊያገኝለት እንዳልቻለ የተገነዘበው ኢህአዴግ፤ ከሰሞኑ ደግሞ ተቃውሞ ያሰሙትን ሙስሊሞች፦ “ሀሳባቸው የሸሪአ መንግስት ለማቋቋም ነው”በማለት በሌሎች እምነት ተከታዮች ዘንድ በጥርጣሬና በፍርሀት እንዲታዩ ቅስቀሳ መጀመሩ ይታወቃል።
የብዙሀኑ ሙስሊም አስተባባሪ ኮሚቴ ፦”በሀሰት ፕሮፓጋንዳ የመብት ጥያቄን ማዳፈን አይቻልም” በሚል ርዕስ ሰሞኑን  በበተነው ወረቀት ፤ መንግስት የዚህ ዓይነት ቅስቀሳ የጀመረው ፤የሙስሊሞች መብት የማስከበር እንቅስቃሴ በክርስቲያን ወንድሞቻቸው ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይና ድጋፍ እንዳያገኝ ለማድረግ መሆኑን በመጥቀስ፤ ከዚህ አይነት አደገኛ የውሸት ቅስቀሳ እንዲቆጠብ ማሣሰቡ አይዘነጋም።
የብዙሀኑን ሙስሊም አስተባባሪ ኮሚቴ እና በስደት የሚገኘው ሲኖዶስ ያወጧቸውን መግለጫዎች የተመለከቱ አንድ አባት፦” በሁለቱም ወገን የወጡት መግለጫዎች ፤መንግስት ተከባብረውና ተዋደው የኖሩትን ህዝቦች በእምነት ምክንያት ለማናቆር እና ለማጋጨት ለዓመታት ቢደክምም፤ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች  አንድኛቸው ለሌላው ያላቸው አክብሮት እና አስተሣሰብ ዛሬም እንደ ጥንቱ በፍቅር ላይ የተመሰረተ እንደሆነ  የሚያመለክቱ ናቸው”ብለዋል።

የድጋፍ ማሰባሰቢያ ሩጫው ተቃውሞ ያሰከትላል በሚል የመርሀ ግብር ለውጥ ተደረገበት

ግንቦት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ እሁድ  ለአባይ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ታስቦ በተዘጋጀው የሩጫ ፕሮግራም ላይ ገዥው ፓርቲ ከፍተኛ ተቃውሞ ሊገጥመው ይችላል የሚል ሥጋት መፈጠሩን የኢሳት ምንጮች ጠቆሙ፡፡
የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሩጫ ፕሮግራሙ ቀደም ሲል ከመስቀል አደባባይ፣ በታላቁ ቤተመንግስት በኩል በፍልውሃ አድርጎ ወደ መስቀል አደባባይ ለመመለስ መርሃግብር ወጥቶለት የነበረ ቢሆንም ከጸጥታ ሥጋት ጋር በተያያዘ መነሻው መስቀል አደባባይ ሆኖ በቄራዎች ድርጅት በማድረግ ተመልሶ መስቀል አደባባይ እንዲያበቃ ተወስኗል፡፡የተሳታፊዎች ቁጥሩንም በተመለከተ ከ30 ሺ በላይ የአ/አ ነዋሪ ይሳተፋል ተብሎ መርሃግብር ከወጣ በኃላ አሁንም በተለይ ሙስሊሞች ሊረብሹ ይችላሉ ተብሎ በመሰጋቱ ነዋሪውን ለማሳተፍ የነበረው እቅድ እንዲሰረዝና በየአካባቢው የተመረጡ አባላትና ደጋፊዎች ብቻ በሩጫው እንዲሳተፉ በመወሰኑ የተሳታፊዎች ቁጥር ወደ 12 ሺ ዝቅ ይላል ተብሏል፡፡
ምንጮቹ አያይዘውም የሩጫው ዓላማ ለግድቡ ቀጣይ ድጋፍ ማሰባሰበብ ሆኖ ሳለ በተፈጠረው የጸጥታ ሥጋት ምክንያት ሕዝቡ ባለመሳተፉ ዝግጅቱ ዓላማውን መሳቱን ተናግረዋል፡፡
በተያያዘ ዜና ሙስሊሙ ህብረተሰብ በነገው ሩጫ ላይ በመሳተፍ ሠላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞውን ለመግለጫ እንዲጠቀምበት የሚጠይቅ ወረቀት እየተበተነ መሆኑን ምንጮቻችን ቢጠቁሙም ወረቀቱን ለማግኝት ግን ያደረግነው ሙከራ ለግዜው አልተሳካም፡፡
በሌላ በኩል ዓርብ ዕለት ሙስሊሙ ህ/ስብ እንደተለመደው በተቃውሞ የታጀበ ጁምአ ያካሄደ ሲሆን ከወትሮው ለየት ያለ ግልጽና ሰውር ጥበቃ ተጠናክሮ ታይቷል፡፡መንግሥት ከሙስሊሙ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የሆነውን “መጅሊስ ይውረድ” የሚለውን ተግባራዊ ለማድረግ  ቀን ቆርጦ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም ምርጫው ጥያቄ ያቀረቡ ወገኖችን ባሳተፈና በራሱ በሙስሊሙ ሕዝብ መካሄድ ይገባዋል በሚል ጥያቄ ባቀረቡ ወገኖች ዘንድ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡ጥያቄያአቸውን ሲያቀርቡና ከመንግስት ጋር ሲደራደሩ የቆዩት ወገኖች ባወጡት መግለጫ ሕዝበ ሙስሊሙ ላነሳው  ጥያቄ ምላሸ የሚያሰገኝ ሒደት መጀመሩን በአዎንታ እንደሚያዩት ጠቁመው የሥልጣን ሸግግሩ ግን ሕዝባዊነት በሌለውና አሁን በሥልጣን ላይ ባለው የመጅሊስ መዋቅር አጋር የሆነው የኡላማዎች ም/ቤት መሰጠቱን ተቃውመው፣ ሙሉ ሒደቱን ሕዝበ ሙስሊሙ በንቃት እንዲከታተለው ጥሪ ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡
መግለጫው አያይዞም ከሠላማዊ የሙስሊሙ ትግል ጋር በተያያዘ በመላ አገሪቱ የታሰሩ ወገኖች እንዲፈቱ ለመንግስት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ ቀዳሚ ትሆናለች ተባለ

ግንቦት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ሪፖርተር አይኤም ኤፍን ጠቅሶ እንደዘገበው ኤርትራ በማእድን፣ በመሰረተ ልማት እና በእርሻው መስክ ባስመዘገበችው ውጤት ከምስራቅ አፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ ቀዳሚ አገር ትሆናለች። ኤርትራ በ7.5 በመቶ እንደምታድግ የተነበው አይ ኤም ኤፍ፣ በአንጻሩ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 5 በመቶ ብቻ ያድጋል ብሎአል።
የመለስ መንግስት 11 በመቶ የኢኮኖሚ እደገት ማግኘቱን በተደጋጋሚ ሲገልጽ፣ የኤርትራ መንግስት በአንጻሩ ስለ አገሪቱ እድገት ምንም አይነት የፕሮፓጋንዳ ስራ ሲሰራ አይታይም። መገናኛ ብዙሀን ኤርትራ በኢኮኖሚው የደቀቀች፣ ልትፈራርስ የቀረበች አገር አድርገው በተደጋጋሚ ይዘግባሉ።  የአይኤም ኤፍ ሪፖርት እንደሚያሳየው ግን ኤርትራ ድምጿን አጥፍታ ከኢትዮጵያ የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑዋን የሚያሳይ ነው።  ባለፈው አመት ከፍተኛ እድገት እንዳመጡ የሚወራላቸው ኢትዮጵያ እና ኬንያ በረሀብ መጠቃታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የምግብ እርዳታ ከአለማቀፍ ለጋሾች ሲቀርብላቸው ኤርትራ ምንም የውጭ እርዳታ ሳታገኝ አመቱን አገባዳለች። አለማቀፉ ማህበረሰብ በበኩሉ ኤርትራ የረሀብተኛውን ቁጥር ሆን ብላ ትደብቃለች በማለት ሲከስ ይሰማል። ይሁን እንጅ የኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ዜና በተለይም የግብርናው ምርት ያለ ውጭ እርዳታ በከፍተኛ ሁኔታ እንዳደገ በአለማቀፍ ተቋማት መመስከሩ፣ ለመለስ መንግስት እና በኤርትራ መንግስት ላይ ማእቀብ እንዲጣል ሲወተውቱ ለነበሩ የምእራብ መንግስታት የፕሮፓጋንዳ ስራ ትልቅ ጋሬጣ እንደሚፈጥርበት አንድ የተቃዋሚ አባል ተናግረዋል። የኤርትራ መንግስት በራስ መተማመን በሚል ፖሊሲው የውጭ እርዳታ አይቀበልም። በአንጻሩ የመለስ መንግስት በእየአመቱ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ በእርዳታ መልክ ያገኛል።

እየሩሳሌም ሆይ ተነሽ!!!....ተላከ ከእስራኤል

እምነቴና ዘሬም በሙሉ ይሁዲ፡ ሙሉ በሙሉ እሥራኤላዊ ብሆንም፡ ምንም ቢሆን 2500 ዘመንም የአያት
የቅድመ አያቴ አጽም፤የእኔም ሆነ የልጆቼ እትብት የተቀበረባት ሃገረ ኢትዮጵያ በመሆኗ ፤"ባይቆጭ
ያንገበግባል" ይሉ የለም አበው !!!
ምንም እንኳን አንድ ቀን ከፈለስንባት ቅድስት ሃገራችን እንመለሳለን የሚለው ህልም ዕውን እስኪሆን ድረስ!
የእኛም አያት ቅድመ አያት፤ አባቶች፤እናቶች፤ወንድሞች፤ እህቶችና ልጆች ለዚህች ኢትዮጵያ ለምትባል ሃገር
እንደማንኛውም የሃገር አንድነት ወዳድ ኢትዮጵያዊ አብሮ በመዝመት ከውጭ ወራሪና ከውስጥ ቦርቧሪ ጋር
በመፋለም፤ ክቡር ህይወቱን አሳልፎ አንገቱን ለሰይፍ ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ ህይወቱን ሰውቷል!! ከዚያም
ባሻገር፤ ከኋላ ደጀን በመሆን የተበላሹ የጦር መሳረያዎችን እየጠገነ ለተዋጊው የህዝብ ሰራዊት በመመለስ
ተዋግቷል! አዋግቷል !!
ታዲያ ከዚህ ከወደ እሥራኤል ስለ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ይዘት፤ የማህበራዊ ኑሮና የኢኮኖሚ ሁኔታ ግድ የለሽ
መሆን ስላስገረመኝ ነው። እኔ ከፍ ብየ እንደገለጽኩት አንድም የኔ ዘመድ የሆነ ሰው በኢትዮጵያ ምድር
አልቀረም። ምንም እንኳን በተለያዩ ነገሥታትና መንግሥታት ለህዝቧ ነጻነትና መብት ብዙም ግድ
ባይኖራትም፡ ይሁዳውያን ግን ድርብ ተደራራቢ በሆነ ጭቆና ከሌላው ኅብረተሰብ ተለይተው ተዋርደውና
ህልውናቸው ተረግጦ ይኖሩ ከነበረው ወጥተው፤ አሁን እዚህ እሥራኤል በነጻነት ሲኖሩ፤ እንዴት ነጻነት
ለጠማው ህዝብ ጩኽቱን ማሰማት ተሳናቸው?! የመብት ረገጣና የነጻነት ማጣት ሰቆቃው ምን ያህል አስከፊ
መሆኑን! አሁን ከዚህ በነጻነትና ሙሉ መብቱን ለማስጠበቅ የተመቻቸ የዲሞክራሲ መርህ ካለው ህዝብ የበለጠ
ማን ይረዳዋል !!
እንደ ኢሮ.አ.ቆ በ-1991 በኦፕሬሽን ሽልሞ(የሰለሞን ዘመቻ) በሚባለው ቢያንስ በግምት ወደ አንድ እጅ
ከመቶው የመጣው ከይሁዳውያን ጋር የተጋቡና የተዋለዱ በመሆናቸው፤ ከዚያ በኋላ እስካሁን የሚመጣው
አብዛኛው በስመ ይሁዲ ሲሆን የሚበዙት ምንም የይሁዲ ዘር የሌላቸው በተለያየ አጋጣሚ የሚመጡ ዜጐች፡
ግን መላው ቤተሰባቸው ኢትዮጵያ የሚገኝ ናቸው። ታዲያ እነሱ እንኳን ተነስተው ጩኽታቸውን የማያሰሙት
ለምን ይሆን?! ስለራሳቸው እንጂ ስለ ወገናቸው ግድ የላቸውም ማለት ነው !!
እንደ ኢሮ.አ.ቆ በ-2003 እና 2005 መለስ ዜናዊ መጥቶ በነበረበት ጊዜ እውነተኞቹ የኢትዮጵያ ስደተኞች
መለስ ዲክታተር! መለስ ሌባ! መለስ ነፍሰ ገዳይ!...ወዘተ እያሉ መፈክሮችን በመያዝ እየሩሳሌም በአረፈበት
"ኪንግ ደቪድ" በተባለው ሆቴል ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ በማድረጋቸው ሳቢያ በመናደድ፤ ከመንግሥትም ሆነ
ከእሥራኤላውያን ጋዜጠኞች ለቀረበለት ጥያቄ ሲመልስ፦"ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እንጅ የፖለቲካ ችግር የለም፡
ሁሉም ወደ ሃገሩ በመመለስ መኖር ይችላል ማንም አይፈልጋቸውም!!” ብሎ ከሄደ በኋላ፤ የሰላማዊ ሰልፉ
አስተባባሪ የሆኑት በጥቆማ ተይዘው በመታሰር፤ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ የተወሰኑትን የበላ ጅብ እስካሁን
አልጮህ እንዳለና፤ የተወሰኑት እንደታሰሩ ወዲያውኑ በ human rights በኩል ሲሰማ፤ በተለይ በደርግ
መንግሥት ወታደር፤ የተለያዩ መኰንኖች እና አንዳንድ ከተለያዩ የሥራ ሃላፊነት በፖለቲካው ምክንያት
የተባረሩ ደግሞ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተብሎ የታመነባቸው ኢትዮጵያውያን
በየዓመቱ፤ የአንዳንዶች ደግሞ በየስድስት ወሩ የሚታደስ መታወቂያ ብቻ ተሰጥቷቸው የሚኖሩት በጣም በጣት
የሚቆጠሩ ናቸው።
እነዚህስ ኢትዮጵያ የሚሰቃዩትን ወገኖቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ሰቆቃ ምነው መጮህ ተሳናቸው?! እነዚህ
ቢዎጡ ለሰላማዊ ሰልፍ ደጋፊያችቸው ብዙ ነበር!! እዚህ ሃገር እኮ አንድ ሰውም ይሰማል ብቻውን ቢጮህ!
በተለይ በዚህ 15 ዓመታት እየሩሳሌምን ለመሳለም እየተባለ በፋሲካ የሚመጡት በአብዛኛው ወጣቶቹ ትግርኛ
ተናጋሪዎችና ትግሬዎች ሲሆኑ፤ አማርኛ ተናጋረዎቹ ግን ቁጥራቸው አነስተኛ ከመሆኑም ባሻገር እድሜዓቸው
ከ-55 በላይ የሆኑ ሽማግሌዎች ብቻ ናቸው።ይገርማል !!
መንግሥተ ሰማያትንም ትግሬዎችና ትግርኛ ተናጋሪዎች ብቻ እንዲገቡባት መለስ አዘዘ?!ጉድ ይሏል!!
ይገርማችኋል፤ እነዚህ ትግርኛ ተናጋሪዎች ወዲያው ጊዜ ሳይፈጅ የስደተኝነት የመኖሪያ ፈቃድ ተሰጥቷቸው
ታያለህ ትሰማለህ፤ በዚያ ላይ ይሁዳውያን የትግርኛ ተናጋሪዎች ጋር ግንባር ፈጥረው ማህበር በማቋቋም
የተለያዩ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ሲመጡ፤ በይሁዳውያኑ ትግሬዎች ስም ስብሰባ ይደረጋል። ከዚያ
ለልማት፤ለድርቅ፤ለደን መራቆት፤በጦርነት ለተጐዱ...ወዘተ እና በቅርቡ ደግሞ በየከተማው
በአሽቃቫጮቻቸው በኩል ይህን የዋህ ይሁዲ ይሰበስቡና የቦንድ አውጡ በማለት የዋሁ ይሁዲ በቅንነት
እውነትም ለኢትዮጵያ ልማት የሚውል እየመሰለው ያዋጣል።
ማን ያስረዳው!! ሬዲዮውም ሆነ ቴለቪዥኑ የአማርኛው፤ ሰኞና ማክሰኞ አምባሳደሩን ነው ቃለ መጠየቅ
የሚያደርጉ።ታዲያ ህዝቡ እውነቱን እንዴት ይወቅ?! አንዳንዶች ደፋሮች ደፍረው ሲናገሩ አንተ ስለኢትዮጵያ
ምን አገባህ ይባላሉ!! አንተ እሥራኤላዊ ነህ!ቅስማቸው ይሰበራል!! ዝም!! ዝም !!
የስደተኝነት መታወቂያ ያላቸው ትግሬዎችም ከአምባሳደሩ ጋር እየተገናኙ፤ህዝቡን እንዲቀሰቅሱ ይላካሉ።
እያንዳንዱ ምን ያህል ገንዘብ ሰበሰበና እንዴት መሰብሰብ እንዳለበት ይወያያሉ። ከዚያ በዚያ መከረኛ ራዲዮና
ቴሌቪዥን ይህን ያህል ዶላር እሥራኤል ከሚገኙት ቤተ-እሥራላውያን ተሰበሰበ ነው ቅስቀሳው!!
እውነተኞቹ ስደተኞች ደግሞ ተደብቀውና እነዚህን የመለስን ተላላኪዎች እንዳይጠቁሟቸው በመስጋት
በፍርሃት ይኖራሉ። አያሳዝንም!! የተገላቢጦሽ መሆኑ !!
ወደ ዋናው ርዕሴ ልመለስ፤ እየሩሳሌም የሚገኘው ገዳማት ይዘቱ የኢትዮጵያውያን ይሁን እንጅ፤ እኔ
እስከማውቀው በ 15ተኛውና በ 16ተኛው ክፍለ ዘመን ከተገነባው የዴሬ-ሱልጣን ገዳም ጀምሮ፤የዛሬ 130
ዓመት ገደማ አጼ ሚኒሊክ አስጀምረውት አጼ ዩሃንስ ያስጨረሷት ኪዳነ ምኅረት ገዳም፤ በኢያሪኮ የሚገኘው
ገዳምና ቤት-ዓልዓዛር የተባሉት ገዳማት የሚተዳደሩት፤ የተለያዩ ነገሥታት በስማቸው ያስገነቧቸውን ህንጻዎች
ለገዳማቱና ለአገልጋይ መነኰሳቱ ይሁን በማለታቸው፤ በአሁኑ ስዓት የእሥራኤል ድምጽ ራዲዮ ጣቢያ
የሚያስተላልፍበትን የእትዬ ጣይቱ ህንጻ ጨምሮ፤የንግሥት ዘውዲቱ ህንጻ፤የአሉላ አባ ነጋ ህንጻ፤....ወዘተ
ኪራይ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገዳማቱ የኪራይ ገቢ አላቸው። በአጭሩ የእየሩሳሌም ገዳማት
እራሳቸውን ችለው የሚስተዳድሩ ናቸው ማለት ነው። የተለያየ ከምዕመናኑ ስለት የሚሰጠውን ጨምሩበት !
ታዲያ ጫካ ቤቴ፤ ቅጠል ልብሴ፤ አውሬ ጓደኛየ ብለው ሁሉም ነገር በቃኝ፤ ዓለም ለምኔ ብለው መንነው
እንጨት ቆርጠው እሳር ነስንሰው ጐጆ ቀልሰው በዱር መሃል ኦሪታቸውን አስቀምጠው ለኢትዮጵያና ለህዝቧ
ሌት ተቀን ሱባየ ገብተው በመጸለይ ባሉት መናንያን ላይ፡ይህ እብሪተኛ!! መናንያኑ የተከለሉበትን ዱር ለስኳር
ብሎ በተደበቁበት ጫካ እርቃናቸውን ሊያጋልጥ ሲመነጥር፤ የእየሩሳሌምን መነኰሳት አይመለከታቸው
ይሆን ?!
የጻድቃን አጽም ተቆፍሮ ማዳበሪያ ሆኖ እዚያ ላይ ስኳር ሲመረት የእየሩሳሌም መነኮሳት እንደ "በጉ" ሥጋ
ተጭኖ በአይሮፕላን ሲመጣላቸው እንደሚበሉት፤ዋልድባ በጻድቃን አጽም ማዳበሪያ የተመረተውን ስኳርስ
ዝም ብለው ይጠጡት ይሆን?! አይሆንም አይባልም ይሆናል!! ዕድሜ ይስጥ ብቻ !!!
የእየሩሳሌም መነኰሳት በዋልድባና በዝቋላ ገዳም መቃጠል አይቆጫቸውም?! ምንስ ቢሆን ከአንድ ሽህ ዘመን
በፈት የተጠበቀ ቅርስ አይደለንም ?!
እሥራኤል እንኳን በምድሯ የሚገኘውን የኢትዮጵያን ሃብትና ቅርስ፤ በታሪካዊ ቅርስነት መዝግባ ምኑንም
ሳትሰርዝና ሳትደልዝ በታሪካዊነት በመጠበቅ፤ ለቱሪስቶች ከምታስጐበኛቸው ከፍተኛና ታሪካዊ ቅርስ አንዱ
የኢትዮጵያውያኑ ቅርስ ነው።
ታዲያ ይህ እኩይ፤ በገዛ ሃገሯ ያሉና ዘመናት ያስቆጠሩ ገዳማትን የእሣት ቋያ ሲለቅበት፤ ዶዘር አስገብቶ
ሲመነጥር፤ የእየሩሳሌም መነኰሳትን ግድ ያልሰጣቸው ለምን ይሆን ?!
እዚህ እሥራኤል ሃገርም እኮ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግና በደልን የማሰማት ሙሉ ነጻነት አለ!፤ እና እነዚህ
የሃይማኖት መነኰሳት ለምን ኢትዮጵያ የሚደርሰውን ሰቆቃ ማሰማት ተሳናቸው?!
እስካሁን ህዝብ ሲጨፈጭፍና ሲያፈናቅል፤ ሃገሪቱን ለቅኝ ግዛት አሳልፎ ሲሰጥ በፖለቲካ ጣልቃ አንገባም
ብለው ዝም አሉ!! እውነት ሃገር እየሞተ ዝም ማለት ያስፈልግ ነበር?!ሃገር ከሌለ ኩራት በምን ሊሆን?! በተለይ
በእሥራኤል የሚኖሩ መነኰሳት የሚያውቁትና እያንዳንዱ ይሁዲ እንዴት ሃገሩን እንደሚወድ ያያሉ!!
ይሁዳውያን ሀገር ስላልነበራቸው የደረሰባቸውን ጭፍጨፋና ውርደት ያውቃሉ። በዚህ ምክንያት በተቻላቸው
ሁሉ "ሰውን በሰውነቱ" እና በሰብዓዊነቱ መብቱ በማክበር በኩል ከፍተኛ ትኩረት ሲያደርጉ ያያሉ።
ታዲያ እነዚህ የእግዚአብሄር ባሪያና አገልጋይ ነን ብለው ከላይ እስከታች ጥቁር ቀሚስ ለብሰው፤ ጥቁር እሻሽ
!?ጠምጥመውና ጥቁር ነጠላ ደርበው ዓለም በቃን ያሉ!! እንዴት ለወገን መቆርቆር አልቻል አላቸው
ሁሉም ይቅር፤ ለሃይማኖታቸውስ አይሞቱም?! ወይስ እኛ በጥሩ ሁኔታ ስላለን ስለሌላው ግድ የለንም፤የድሉ
!?ጉዳይ ነው ማለታቸው
እስኪ ከወዲህ ከወደ እየሩሳሌም ድምጻችሁን አሰሙ?! እናንተ ብታስተባብሩን እኛ እናግዛችኋለን!! እናንተ
ባለቤቶቹ ተቀምጣችሁ እኛ ማስተባበር አንችል!!
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ዘርግታለች!!!!
ከእሥራኤል

ለጎሳዊ ስነ-ልቦና አናጎብድድ (ዶር አክሎግ ቢራራ)

አክሎግ ቢራራ | May 11th, 2012 at 12:29 pm | |
የታሪክ ተጠያቂዎች ሁነናል (ክፍል ሶስት)

አክሎግ፡ ቢራራ (ዶር)
ይህ፡ በተከታታይ፡ የማቀርበው፡ ሁለ-አቀፍ፡ ትንተና፡ ሶስተኛ፡ ክፍል፤ ካለፉት፡ ሁለት፡ ትንተናወች፡ ለየት፡ ይላል። የሚለይበትም፡ ዋና፡ ምክንያት፤ ባለፉት፡ እንዳስቀመጥኩት፤ የህወሃት፡ ጠባብ፡ ብሄርተኛ፡ ቡድን፡ ፍልስፍና፡ መሰረት፡ መነሻው፡ ባለፉት፡ መቶ፡ አመታት፡ የአማራ፡ ብሄር፡ ህብረተሰብ፡ “ጨቋኝ፤ ነብሰ-ገዳይ፤ ነፍጠኛ፤ የተጠላ፤ ዘራፊ፤ ቅኝ-ገዥ”፤ በሚሉ፡ በመርዝ፡ የተቀባ፡ የዘር፡ መለያ፡የስነ-ልቦና፡ ጦርነት፡ ማካሄዱና፡ በተለይ፡ አብዛኛውን፡ ሃሁ፡ የቆጠረውን፡ ክፍል፤ በዚህ፡ መሰረት፡ በሌለው፡ ክስ፡ተስቦና፡ ተበክሎ፤ እራሱን፡ እንዲጠራጠር፤ በእራሱ፡ እንዳይተማመን፤ ማንነቱን፡ እንዲከዳ፤ በአጎብዳጅነት፡ እንዲኖር፤ ፈሪና፡ አሞት፡ የሌለው፡ እንዲሆን፤ እርስ፡ በእርሱ፡እንዲከፋፈል፡ ማድረጉ፡ ከባድ፡ ሸክም፡ ሆኖ፡ ቆይቷል። ይህን፡ ሸክም፡ ማስወገድ፡ ያለብን፡ እኛ፡ እንጂ፡ህብረተሰባዊ፡ ምሰሷችን፡(the pillars of community and affinity)፤ ታጥቆ፤ እያናጋው፡ ያለ፤ ህወሃትና፡ደጋፊወቹ፡ ሊሆኑ፡ አይችልም።
የህወሃት፡ ፈጣሪወች፤ ህዝብን፡ ከህዝብ፡ ጋር፤ ሃይማኖትን፡ ከሃይማኖት፡ጋር፡ ካላጋጩ፤ ሰውን፡ለጥቅም፡ ፍላጎት፡ ካልሳቩ፤ ተቃዋሚ፡ የሆነውን፡ ካላሳደዱ/ካላሰሩና፡ ሁሉ፡በፍርሃት፡ በእራሱ፡ ላይ፡ ያለውን፡ እምነት፡ ካላስካዱ፤ በስልጣን፡ እንደማይቆዩ፤ ለጠባብ፡ አዲስ፡ “ከኪራይ-የሚገኝ፡ ሃብት፡ ፈላጊወች (new rent-seekers)፤ ጋር፡ በጥቅም፡ ተደጋግፈው፡ ሃብት፡ እነደማያካብቱ፡ያውቁታል። ጽንሰ-ሃሳቡን፡ ከውጭ፡ ቀድተው፡ ስራ፡ላይ፡ ያዋሉት፡ የበላዮች፤ የአማራ፡ ህብረተሰብእ፡ ለትግራይ፡ ብሄረሰብ፡ “አጥፊና፡ አቆርቋዥ” መሆኑን፡ ቀስ፤ በቀስና፡ በዘዴ፤ እኛንና፡ ሌሎችን፡ አሳምነው፡ የፖለቲካ፤ የባህል፤ የኢኮኖሚ፤ ወዘተ፡ ስልጣንና፡ አቅም፡ ከአማራውና፡ ከሌሎች፡ ነጥቀው፡ ወደ፡ ትግራይ፡ ጠባብ፡ ቡድን፡ በዘዴ፡ ማሸጋገሩን፡ በተናጥል፤ ማለትም፤ ከእኛ፡ ባህርይና፡ አሰራር፡ ለይተን፡ መመልከት፡ አንችልም፡ እላለሁ። ምክኒያቱም፤ ውሸት፡ በህወሃት፡ ተደጋግሞ፡ ከተነገረ፡ እውነት፤ እውነት፡ ይሸታል። ይህን፡ ውሸት፡ ህወሃትና፡ ደጋፊወቹ፡ ብቻ፡ ሊያሰራጩት፡ አይችሉም። ለምሳሌ፤ ሌላውን፡ ለማሳመን፡ የተቀነባበረ፡ ፕሮፓጋንዳ፡ ደጋግመው፡ ማስተጋባት፡ አለባቸው። የኢትዮጵያ፡ ምጣኔ፡ ሃብት፤ በድርብ፡ አያደገ፡ ፍትሃዊ፡ ውጤት፡ አሳይቷል፡ የሚለውን፡ እንይ።
በዚህ፡ ሳምንት፡ በአሜሪካ፡ ድምጽ፡ ሬዲዮ፡ ተጋብዠ፡ ከአንድ፡ በ ኢትዮጲያ፡ ከሚኖሩ፡ ባለሙያ፡ ጋር፡ “ፍትሃዊ፡ እድገት፡(equitable growth) አለ፡ ብለው፤ በአንድ፡ የአለም፡ አቀፍ፡ ስብሰባ፡ ላይ፤ ጠቅላይ፡ ሚኒስትር፡ መለስ፡ ስለተናገሩት፡ ያደረግነውን፡ ክርክር፡ ለአንባቢ፡ አቀርባለሁ። እኒህ፡ ባለሙያ፤ ጠቅላይ፡ ሚኒስትሩን፡ ደግፈው፡ የኢትዮጵያ፡ በአመት፤ አስራ፡ አንድ፡ በመቶ፡ እድገት፡ ያሳየው፡ እኮኖሚ፡ (ምጣኔ፡ ሃብት)፤ “ፍትሃዊ” መሆኑ፡ የሚታየው፡ “የገጠሩ፡ሰማንያ፡ አምስት፡ በመቶ፡ የሚሆነው፡ ገበሬ፡ ሕዝብ” በአገራችን፡ “ያልታየ፡ የኑሮ፡ መሻሻልን፡አስመስክሯል፤ ይህን፡ ባይናችን፡ እያየነው፡ ነው፡” ያሉት፡ ነው። ተናጋሪው፡ ይህን፡ ማቅረባቸው፡ አላስገረመኝም፤ ስርአቱን፡ ከደገፉ፡ ተጻራሪ፡ ሃሳብ፡ ለማቅረብ፡ አይችሉም። መብታቸውን፡ አከብራለሁ። እኔ፡ የማየው፤ ከአብዛኛው፡ ድሃ፡ ህዝብ፡ ድህነት፤ በምግብ-የዋጋ፡ ግፍሸት፡ ከሚሰቃየው፡ ኢትዮጵያዊ፤ በ፡ 2012 “የህጻናት፡ መድህን፡ (Save the Children)፤ ባወጣው፡ “ከ20 አገሮች፡ ኢትዮጵያ፡ አስራ-ሰባተኛ፡ በመሆን፡ ለህጻናት፡ ሲኦል፡ ናት፡” ከሚለው፡ አንንጻር፡ ነው። ለተወሰኑማ፡ ዛሬ፡ ኢትዮጵያ፡ ገነት፡ መሆኗ፡ ምንም፡ አያጠያይቅም። ያስደነቀኝ፡ እንደዚህ፡ ያለ፡ተራ፡የፈጠራ፡ ወሬ፡ በኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ ላይ፡ ሲካኄድ፡ ሌሎቻችን፡ (አብዛኛወቻችን፡ ማለቴ፡ ነው)፤ በያለንበት፡ አለማስተባበላችን፡ ነው። እንዲያውም፤ ከእውነት፡ የራቀ፡ አነጋገር፡ በተደጋጋሚ፡ እየተነገረ፡ ብዙወቻችን፡ “በሬ፡ ወለደ” የሚሰኘው፡ የእድገት፡ መጠን፡ እውነት፡ ይመስለናል። ማንኛውም፡ በሃቅ፡ የቀረቨ፡ ዘገቫ፡ የሚያሳየው፤ እንኳን፡ ፍትሃዊ፡ እድገት፡ ሊኖር፤ ምስኪንነት፤ ድህነት፤ እርሃብ፤ የሰውና፤ የገንዘቭ”፤ ፍልሰት፤ (destitution, poverty, hunger, human and financial capital flight): በተባባሰ፡ ህኔታ፡ ስፋትና፡ ጥልቀት፡ እያሳዩ፡ ነው። በቅርቡ፤ ቢል፡ ጌተስ፡ እንዳሉት፡ “በድህነትና፡ እርሃብ፡ የተነሳ፤ አብዛኛው፡የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ ከአለም፡ አገሮች፡ በበለጠ፡ ደረጃ፤ የምግብ፡ እርዳታ፡ የሚያስፈሊጋት፡ አገር፡ ውስጥ፡ ይኖራል.” እድገት፡ ፍትሃዊ፡ ለመሆን፡ የሚችለው፡ ጥቂት፡ ሃብታሞች፡ ሚሊየነር፤ ቢሊየነር፡ ስለሆኑ፡ ሳይሆን፡ አብዛኛው፡ የኢትዮጵያ፡ ድሃ፡ ሕዝብ፡ የእድገቱ፡ ተካፋይ፡ ሲሆን፡ ነው። የነፍ፡ ወከፍ፡ እያደገ፡ ስሄድ፡ ነው። የዚህም፡ መለኪያ፡ ቢያንስ፤ አንድ፡ ዜጋ፤ በቀን፡ ሶስት፡ ምግብ፡ በልቶ፡ ሲያድር፤ ልጁን፡ ሲያስተምር፤ ጤናው፡ ሲጠበቅ፤ የተሻለ፡ መጠለያ፡ሲኖረው፤ ንጹህ፡ ውሃ፡ ለመጠጣት፡ ሲችል፡ የተማረው፡ ልጁ፡ ያለ፡ አድሎ፡ ስራ፡ ለመያዝ፡ ሲችል/ስትችል፤ ወጣቶች፡ በአገራቸው፡ እድል፡ ሲኖራቸው፡ ወዘተ፡ ነው።
ሰለሆነም፤ ከጠቅላይ፡ ሚንስትሩና፡ ከታዛዦቻቸው፡ ውጭ፡ እድገት፡ “ፍትያዊ፡ ለመሆኑ፡ምንም፡ ማስረጃ፡ የለም። እድገት፡ መኖሩን፡ ግን፡ እኔም፡ አልክድም። ዋናው፡ ጥያቄው፡ እድገቱ፡ ማንን፡ እየጠቀመ፡ ነው፡ የሚለው፡ ነው። በአመት፡ አስራ፡ አነድ፡ በመቶ፡ የሚለው፡ ግን፡ መንግስት፡ የፈጠረው፤ በነጻ፡ ታዛቢወች፡ ያልተመረመረ፡ መሆኑን፡ ለማመልከት፡ እገደዳለሁ። ኢትዮጵያ፡ እንዴት፡ ከቻይና፤ ከህንድ፤ ከቬትናም፡ ከብራዚል፤ ከጋና፤ ወዘት፡ የላቀ፡ አመት፡ በአመት፡ እድገት፡ ልታሳይ፡ እንደቻለች፡ የሚያስረዳኝ፡ አላገኝሁም። የገጠሩ፡ ህዝብ፡ ኑሮ፡ አስደናቂ፡ በሆነ፡ መንገድ፡ መዋቅራዊ፡ ለውጥ፡ የሚያሳይና፡ ህይወት፡ ለዋጭ፡ ኑሮ፡ መኖር፡ ጀምሯል፡ የሚያስብል፡ አለመሆኑን፤ ቢል፡ ጌትስ፡ ባሉት፡ የመለስኩት፡ ይመስለኛል። በርሻ፡ እረድፍ፡ የአለም፡ ባንክ፡ ባለሙያወች፡ ያጠኑት፡ የሚያሳየው፡ “የኢትዮጵያ፡ መንግስት፡ በሚለው፡ መሰረት፡ የእርሻ፡ ውጤቷ፡ አመት፤ ከአመት፡ ካደገ፡ በዚህ፡አለም፡ ያልታየ፡ ማንም፡ ያልደረሰበት፡ የአርንጓዴ፡ ለውጥ፡ ተቀናጂታለች፡ ማለት፡ ነው” ብለው፡ ባለፈፍው፡ አመት፡ የደመደሙት፤ የመንግስትን፡ የፈጠራ፡ ወሬ፡ ያመለክታል። ስለዚህ፤ ፍትሃዊ፡ እድገት፡ አለ፡ የምንል፡ ሁሉ፡ የፈጠራው፡ወሬ፡ ተባባሪ፡ እንዳንሆን፡ እሰጋለሁ። የስነ-ልቦና፡ መለወጫ፡ ዘዴ፡ ስለሆነ። ህወሃት፡ የሚለውን፡ ሁሉ፡ እንደ፡እውነት፡ ከተቀበልን፤ ለአብዛኛውን፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ አሰቃቂ፡ ኑሮ፡ ክብደት፡ አንሰጠውም፡ ማለት፡ ነው።
ቁም፡ ነገሩ፡ ግን፤ በህወሃት፡ ላይ፡ ብቻ፡ የማተኮር፡ ስነ-ልቦና፤ አገራችንና፡ ከዘጠና፡ ሚሊዮን፡ በላይ፡ የሆነውን፡ ሕዝቧን፡ ያደረሰባቸውን፡ ፈተና፡ ሙሉ፤ በሙሉ፡ አያሳይም። በጥቅሉ፡ ብናየው፡ አራት፡ ነጥብ፡ አምስት፡ ሚሊዮን፡ የሚሆን፡ የትግራይ፡ ህብረተሰብ፡ ወካይ፡ ነኝ፡ የሚለው፡ ህወሃት፡ ስልጣኑንና፡ ጥቅሙን፡ ሊያረጋግጥ፡ የቻለው፡ በእራሱ፡ ሃይል፡ ብቻ፡ አይደለም። ዋናው፡ የስልጣኑ፡ ምሰሶ፡ አድርጎ፡ የሚጠቀምበት፡ የሌሎቻችንን፡ ስነ-ልቦና፡ በመቨረዝ፤ በመስለቭ፤ በማዳከም፤ እርስ፡ በእርሳችን፡ እንድንጣላ፡ በማድረግ፤ በመከፋፍል፤ በጥቅም፤ ለጥቅም፤ ለስልጣን፡ እንድንገዛ፡ በመሳብ፤ በፍርሀት፡ ተጠምደን፡ ማንነታችን፡ እንድንክድና፡ ደፍረን፡ ለፍትህ፤ ለእርትህ፡ እንዳንቆም፡ በማድረግ፤ እንዳንደራጂ፡ የመከፋፈያ፡ ዘዴወችን፡ በያለንበት፡ በመዘርጋት፡ ጭምር፡ ነው። የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ የመዘገበው፡ በዘጠና፡ ሰባቱ፡ ምርጫ፡ ላይም፡ ያሳየው፡ በዘር፡ መለያየትን፡ ሳይሆን፡ በኢትዮጵያዊነት፡ ለአግሩና፡ ለመብቱ፡ የሚቆም፡ መሆኑን፡ ነው። ሰላማዊይ፡ ወገኑን፡ መግደል፡ ልምዱ፤ ባህሉ፤ አለመሆኑን፤ ነው።
የህወያትን፡ የተቀነባበረ፡ የስነ-ልቦና፤ ፕሮፓጋንዳና፡ እቅድ፡ መንሰኤና፡ ያስከተለውን፡ አስከፊ፡ ውጤት፡ በሚገባ፡ ለመረዳት፡ የሚቻለው፡ ከኢትዮጵያ፡ ተማሪወች፡ እንቅስቃሴና፡ ከተከተለው፡ ክፍፍል፤ እ.አ.አ. ከ 1960s ወዲህ፡ ስር፡ በመስደድ፡ ላይ፡ ያለውን፤ ጥቂቶቻችን፡ ይህ፡ በዘር፡ ልዩነትና፡ ጥላቻ፡ ላይ፡ የተመሰረተ፡ ጉዞ፡ ለማንም፡ አያዋጣም፤ አገራችን፡ ይጎዳታል፤ ሕዝቧ፡ በድህነት፡ አዙሪኝ (cycle): እንዲጠመድ፡ ያደርገዋል፡ ብለን፡ ስንከራከርበት፡ የቆየነውን፤ መተኪያ፡ የማይገኝላቸውን፡ ብዙ፡ መቶ-ሽህ፡ የሚሆኑ፤ ከሁሉም፡ ብሄር፤ ብሄረሰብና፡ ህዝብ፡ ክፍሎች፡ የተወጣጡ፤አገር፡ ወዳድ፡ ኢትዮጵያዊያን፡ ለሃገር፤ ለወግን፡ ብለው፡ መስዋእት፡ የከፈሉበትን፤ አሁንም፡ የሚከፍሉበትን፤ በጎሳ፡ የማይታረቅ፡ ልዩነቶች፡ ላይ፡ማር፡ ቀብቶ፡ ያዘጋጀልንን፤ የከፋፍለህ፡ ግዛው፡ የፍልስፍና፡ ጉዞ፡ ጠለቅ፡ ብሎ፡ በመመርመርና፡ በመረዳት፡ የሚገኝ፡ ሃቅ፡ ነው። ይህን፡ ለታሪክ፡ እተወዋለሁ። ዙሮ፡ ማንንም፡ ለመኮነን፤ ለመውቀስ፡ ሳይሆን፡ የስነ-ልቦና፡ ጦርነቱ፡ እኛን፡ ያደከመንና፡ ያከፋፈለን፡ መሆኑን፤ አሁን፡ የተጀመረ፡ አለመሆኑን፤ ይህን፡ ጎጅ፡ የፖለቲካ፡ ባህል፡ ማቆም፡ እንዳለብን፡ ለማመልከት፡ ብቻ፡ ነው።
ሀወሃት፡ አሁን፤ ከስራ፡ ላይ፡ አውሎት፡ የምናየው፡ “የብሄሮች፡ የማይታረቅ፡” ፍልስፍና፡ መሰረት፤ የአማራው፡ ህብረተሰብ፡ ሆነ፡ ተብሎ፡ በተለይ፤ በትግራይ፡ ህብረተሰብና፡ በሌሎች፡ እንዲጠላ፤ አማራው፡ እራሱን፡ እንዲጠራጠር፤ እርስ፡ በእርሱ፡ እንዲጣላና፡ እንዳይተባበር፤ በተከሰሰበት፡ አምኖ፤ አጎብዳጅ፡ እንዲሆን፤ ቀስ፡በቀስ፡ በኢትዮጵያ፡ የፖለቲካ፤ የባህል፤ የኢኮኖሚ፡ ዘርፎች፡ ሁሉ፡ አቅም፡ ያለው፡ ተወዳዳሪ፡ ሆኖ፡ እንዳይሳተፍ፤ ታሪክና፡ አስተዋጾውን፡ ሁሉ፡ እንዲያፍርበት፤ አንዳይቀበል፤ ቢቻል፡ የተማረው፡ ክፍል፡ በሙሉ፤ አገር፡ ለቆ፡ በስደት፡ እንዲኖር፡ ለማድረግ፡ ነው። ካልተቻለ፡ ደግሞ፡ ጸጥ፤ ለበጥ፡ ብሎ፤ አንገቱን፡ ሰብሮ፤ ማንነቱን፡ ክዶ፤ ተነስ፤ ውጣ፡ ሲባል፤ መብት፡ እንደሌለው፡ እዲወጣ፤ ህሊናው፡ ተበርዞ፤ እርስ፡ በእርሱ፡ ተናክሶ፤ አዲሱን፡ ስርአት፡ እንዲቀበል፡ ነበር፤ አሁንም፡ ነው። ይህ፡ ስልት፡ በአንጻሩ፡ የጣሊያን፡ ቅኝ፡ ገዦች፡ ያስተናገዱት፡ የከፋፍለህ፡ ግዛው፡ ስልት፤ የደቡብ፡ አፍሪካ፡ አፓርታይድ፡(Apartheid) የመሰለ፡ ስልት፡ መሆኑን፡ ብዙ፡ ማስረጃወች፡ መዝግበውታል።
በቅርቡ፡ አቶ፡ ገብረመድህን፡ አራአያ፡ ጠቅላይ፡ ሚንስትር፡ መለስ፡ “አማራ፡ ዋና፡ ጠላታችን፡ ነው። ይህን፡ ህብረተሰብ፡ ከስሩ፡ ማጥፋት፡ አለብን፡” ያሉት፡ ማስረጃ፡ ነው። ጠቅላይ፡ ሚኒስትሩ፡ ይህን፡ ያሉበትን፡ ዋና፡ ምክንያት፡ ብዙ፡ የውጭ፡ አገር፡ ባለሙያወች (Paul Collier/ethnic civil war; Bill Easterly, Ethiopian poverty; Michela Wrong, ethnic-based corruption and illicit outflow, etc)፤ ልይ፡ ልዩ፡ ተቋሞች (Human Rights Watch, Amnesty International, Oakland Institute, Survival International, ec)፤ የኢትዮጵያ፡ ምሁራን፤ ተመልካቾች፤ የስባዊ፡ መብት፡ ተቛሞች፡ አስረድተዋል። እኔም፡ በተከታታይ፡ ከዘጠና፡ ሰቫት፡ ምርጫ፡ በኋላ፡ ባቀርብኳቸው፡ አራት፡ መጽሃፎች፤ በተለይ፡ በ “Waves: endemic poverty that globalization can’t tackle–በተባለው፡ ላይ፡ ከብዙ፡ ዓቅጣጫ፤ በብዙ፡ ማስረጃ፡ አስቀምጨዋለሁ።
ህዝብ፡ የማይሳተፍበት፡ እድገት፡ ፍትሃዊ፡ ሊሆን፡ አይችልም፡
እነዚህና፡ ሌሎች፡ ጥናቶች፡ የሚያመለክቱት፡ ማንኛውም፡ የክልልና፡ ጠባብ፡ ብሄርተኛ፡ ስርአት፡ፍትህ/እርትህ፡ የሌለበት፤ በህግ-የበላይነት፡ የማይዳኝ፤ የህዝብ፡ ድምጽና፡ተሳትፎ፡ የሌለበት፤ የውስጥ፡ ውድድር፡ የተከለከለበት፡ ወይንም፡ አድሏዊ፡ ሆነበት፤ ግልጽነት፡ የሌለበት፡ ነው። ስለሆነም፤ እድገቱ፤ ዘላቂነትና፡ ፍትሃዊነት፡ ያለው፡ ሊሆን፡ አይችልም። ዘረኛው፡ ቡድን፤ ማን፡ ሃብታም፡ እንደሚሆን፤ ማን፡ የስራና፧ የትምህርት፡ እድል፡ እንድሚኖረው፤ ማን፡ የከተማ/የገጥር፡ መሬት፡ እንደሚያገኝ፤ ማን፡ የስራ፡ ፈቃድ፡ እንደሚሰጠው፤ ማን፡ ከፍተኛ፡ ቀረጥ፡ እንደሚከፍል፤ የማን፡ ገቪ፡ ከፍ፤ የማን፡ ዝቅ፡ እንደሚል፡ ይወስናል። ይህ፡ ስርአት፤ የሚጎዳው፡ አንድ፡ ብሄረሰብ፡ ሳይሆን፡ አብዛኛውን፡ የኢትዮጵያ፡ ድሃ፡ ህዝብ፡ ነው። ስርአቱ፡ ካልተለወጠ፡ ሁሉም፡ ይጎዳል። ጥቂት፡ ሰወች፡ ብቻ፡ ስልጣንና፡ ሃብት፡ ያካብታሉ።
ዋናው፡ ለማመልከት፡ የምፈልገው፤ ሁላችን፤ ልናጤነው፡ የሚገባን፤ ከህወሃት፡ የመነጨውን፡ የስርአት፡ ችግር፡ ከሁሉ፡ አቅጣጫ፡ ስናየው፡ ፍትያዊ፡ አይደለም፤ ሊሆንም፡ አይችልም። ይህን፡ ከተረዳን፤ ችግሩን፡ ደጋግመን፡ ብናኝክ፤ ቀን፡ ቀን፡ ከሌት፡ ብናወጣ፡ ብናወርድ፡ ቀጣይ፡ ሁኖ፡ የሚታየው፡ ክፍተት፡ የእኛው፡ ድርጂታዊ/አመራራዊ (organizational and leadership crisis)፤ መሆኑ፡ አያጠራጥም። ግፉን፡ እናያለን፡ የምንል፡ ሁሉ፡ በሚያስማሙን፡ የአገርና፡ የመላው፡ ህዝብ፡ ጉዳዮች፡ ላይ፡ ተነስተን፡ እቅድን፡ ወደ፡ ተግባር፡ ለመተርጎም፡ እንቅፋት፡ የሆኑትን፤ በተቃዋሚው፡ ዘርፍ፡ ተዘርግተው፡ ያሉትን፡ ማነቆወች፡ በግልጽ፡ ተወያይተን፡ መፍትሄ፡የምንፈልግበት፡ አሁን፡ ነው። እራሳችን፡ የምንፈጥራቸውን፡ ችግሮች፡ እስካላየን፡ ድረስ፡ የትም፡ አንደርስም። ለምሳሌ፤ ብናውቀውም፡ ባናውቀውም፤ ብንቀበለወም፤ ባንቀበለውም፤ አንዳንድ፡ በፖለቲካና፡ ማህረሰብ፡ ስብስቦች፡ ውስጥ፡ የሚገኙ፡ ግለሰቦች፡ ሌላውን፡ ያለ፡ ምንም፡ ማስረጃ፡ ስም፡ ማጥፋት፤ መወንጀል፤ መኮነን፤ ማስጠላት፤ ተግባራቸው፡ ሲሆን፡ የማይረዱት፡ ይህ፡ ባህሪይ፡ ህወሃትን፡ ደጋፊ፡ መሆኑን፡ ነው።
የእነዚህን፡ አይነት፡ ባህሪይ፡ በቀጥታ፡ መከላከል፡ የሁላችንም፡ ተግባር፡ ሲሆን፤ አብዛኛውን፡ ጊዜ፡ ሰው፡ ይቀየማል፡ ብለን፡ እናልፋለን። የፈጠራ፡ ወሬ፡ ሰምተን፡ ሳንናገር፡ ዝም፡ እንላለን። እውነት፡ ስለመናገር፡ አንድ፡ ፈላስፋ፡ ሲናገሩ፡ “ስለ፡ እራስህ/እራሽ፡ እውነት፡ ለመናገር፡ ካልቻልክ/ካልቻልሽ፤ ስለ፡ ሌላ፡ ሰው፡ ለመናገር፡ አትችልም/አትችይም፡” የተባለው፡ ሙሉ፡ በሙሉ፡ እውነትነት፡ አለው። የዘመኑ፡ ምሁር፡ ትውልድ፡ ስለ-እራሱ፡ እውነት፡ ከመናገር፡ ይልቅ፡ ስለ፡ ሌላው፤ ስለሚቃወመው፡ “ሃጢያት/መጥፎነት፡ ፈጥሮ፡ መናገር፡ ይቀለዋል። ይህ፡ልምድ፡ የጥላቻ፡ ምልክት፡ ነው። መቀቨል፡ ያለብን፤ ከየትም፡ አቅጣጫ፡ ቢመጣ፤ የፈጠራ፡ ወሬ፤ የጥላቻ፡ ፖሊቲካ፤ ስም፡ ማጥፋት፤ ለእውነት፡ ቀጥ፡ ብሎ፡ አለመቆም፡ የንጹህን፡ ሰው፡ ክብር፡ የግፋል፤ አመኔታን፡ አያጠናክርም። እንዲይውም፤ ደጋፊ፡ የሆነን፡ ግለሰብ፡ ከተሳታፊነት፡ ያባርራል፤ ተመልካች፡ የሆነን፡ “ፖለቲካ፡ ኮረንቲ፡ነው”፡ ብሎ፡ ወደ-መሃል፡ ሰፋሪነት፡ ይመራል። በተቃዋሚው፡ ክፍል፡ ደጋግግሜ፡ ለብዙ፡ ጊዜ፡ ያየሁት፡ ሌላው፤ ልንፈታው፡ የሚገባን፡ ችግር፡ ውይይት፡ በቁም፡ ነገሩ፤ በሃሳቡ፤ በችግሩ፡ ላይ፡ ትኩረት፡ መስጠት፡ ሳይሆን፡ በግለሰቡ፡ ላይ፤ በአለፈው፡ ታሪኩ፡ ላይ፡ የምናደርገው፡ ትኩረት፡ ጎጂ፡ መሆኑ፡፡ነው። ይህ፡ ባህሪይ፡ አገራችን፡ እየጎዳት፡ ነው። ግለሰብ፡ ከሃሳብ፡ አለመለየት፡ ኋላ፡ ቀር፡ አመለካከት፡ ነው። ለገንቢ፡ ለውጥ፡ ማነቆ፡ ነው። ጥላቻን፡ የሚፈጥር፡ መሆኑን፡ ደጋግመን፡ አይተናል።
ይህ፡የሽሙጥ፡ አይነት፡ ባህሪይ፡ ለገንቢ-ለውጥ፤ አብሮ፡ ለመስራት፡ እንቅፋት፡ ሁኗል። ሁለቱንም፡ ጎጂ፡ ባህሪወች፡ ለመለወጥና፡ ለሃያ፡ አንደኛው፡ መቶ፡ ክፍለ-ዘመን፡ የሃገር፡ እድገት፡ አስተዋጾ፡ ለማድረግ፡ ከፈለግን፤ የእኛን፡ ድፍረት፤ ፈቃደኛነት፡ እንጂ፤ የህወሃት፡ ፈቃድ፡ አይጠይቁም። አነኝህን፡ የመሳሰሉ፡ የባህሪይ፤ የአስተሳሰብና፡ የስነ-ልቦና፡ ሁኔታወች፡ አለመለወጥ፤ ያለውን፡ የተማረ፡ የሰው፡ ሃይል፡ በታትነውታል። ለአገራዊና፤ ለወገናዊ፡ ገንቢ፡አስተዋጾ፡ እውን፡ መሆን፡ ማነቆ፡ ሁነዋል። የባሰውን፤ ስም፡ማጥፋት፤ ያለ-ማስረጃ፡ ሰውን፡ መክሰስ፤ አንድ፡ ግለሰብ፡ አቅዋሙን፡ ሲለውጥ፡ መጠራጠር፤ ወዘተ፡ የአገራችን፡ ተወዳዳሪ፡ የማይኖርለት፡የሰውና፡ የእውቅና፡ሃይል፡ በታትነውታል፤ ለመጠቀም፡ ማንቆ፡ ሆነዋል። ተቃዋሚ፡ ነን፡ እያልን፤ ህወሃትን፡ በመዋሸት፡ እየከሰስን፤ እየኮነን፤ እኛ፡ ከዋሽን፡ ልዩነቱ፡ የት፡ ላይ፡ እንደሆነ፡ መጠየቅ፡ አለብን። ተስማምተን፡ አገርና፡ ህዝብ፡ ለመርዳት፡ ከፈለግን፡ ተባብረን፡መስራት፡ አለብን። አብረን፡ ለመስራት፡ ሃቀኛ፡ መሆን፡ የሞራል፡ ግዴታችን፡ ንው።
ይህን፡ በደንብ፡ የተረዱት፤ የኢትዮጵያን፡ የጥንትና፡ ዘመናዊ፡ ታሪክ/ሂደት፡ የሚያውቁት፡ የኢትዮጵያ፡ ወዳጂ፡ አሜሪካዊ፡ ሊቅ፤ ፕሮፌሰር፡ ዶናልድ፡ ለቪን፡ የተናገሩት፡ በአእምሮየ፡ ውስጥ፡ ጸንቷል። አንድ፡ ኢትዮጵያዊ፡ ተማሪ፡ የጠየቃቸውን፡ በማስታወስና፡ በመጥቀስ፡ እንዲህ፡ ይላሉ፡፡ “ለመሆኑ፤ ኢትዮጵያዊያን፡ በጋራ፡ ሁነው፡ አንድ፡ አገራዊ፡ ችግር፡ የሚፈቱበት፡ ጊዜ፡ መቸ፡ ነው።” ይህን፡ አባባል፡ በሙሉ፡ እጋራለሁ። እኔ፡ በተወለድኩበትና፡ ባደግኩበት፡ ክፍል፤ ጎንደር፤ የሚነገር፡ ቀልድ፡ መሳይ፡ ቁም፡ ነገር፡ ላስቀምጥ። ጎንደሬወች፡ በያለሉበት፡ ታታሬ፡ መሆናቸውን፡ የተመለከተ፡ አንድ፡ ታዛቢ፤ እንዲህ፡ ይላል። “አንድ፡ ጎንደሬ፡ የአንድ፡ ሽህ፡ ሰው፡ ስራ፡ ለመስራት፡ ይችላል። ሆኖም፤ ሽህ፡ ጎንደሬወች፡ አንድ፡ ቤት፡ አብረው፤ ተባብረው፡ ለመስራት፡ አይችሉም።” ጎንደሬወች፡ ሆኑ፡ ሌሎች፡ ዛሬ፡ የተስማሙበትን፡ ነገ፡ “ያፈርሱታል.” ተባብረው፤ የተቃጠለ፡ ቤት፡ አያጠፉም። ከማዳን፡ ይልቅ፡ ለማጥፋት፡ የሚደረገው፡ባህል፡ያይላል፡ ለማለት፡ የሚያስደፍሩ፡ ብዙ፡ ሁኔታወች፡ ይታያሉ። የሚያስፈራው፡ ይህ፡ አባባል፡ አገራዊ፡ መሆኑ፡ ነው። ይህ፡ ሁሉ፡ ተደማምሮ፡ የሚረዳው፡ ህወሃትን፡ ነው።
የታሪክ፡ ተጠያቂ፡ ከሚያደርጉን፡ ምክንያቶች፡ መካከል፡ ከተወሰነች፡ ገቢው፤ ቀረጥ፡ ከፍሎ፡ ላስተማረን፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ ዛሬ፤ እኛ፡ የህብረተሰብ፡ “ምርጦች፤ (political and social elites)” ፤ በምናሳየው፡ባህሪና፡ ተግባር፡ የተነሳ፤ ተባብረን፡ ለአንድ፡ አላማ፡ ቆመን፡ የህዝብን፡ ውለታ፡ ለመክፈል፡ አልቻልነም። ህወሃት፡ እፎይ፡ ይላል፤ አብዛኛው፡የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ “የድርጂት/የመሪ፡ ያለህ፤ የተማሩት፡ የት፡ አሉ፤ የት፡ ገቡ፡” ብሎ፡ የጠይቃል። ነጥቡ፤ ለአላማ፡ አንድነት፡ ዛሬ፡ ተቻችለን፡ ካልተነሳን፤ መቸ፡ ነው፡ የምንደርስለት፡ የሚለውን፡ በህሊናችን፡ እንድናብላላ፡ ያስገድደናል። ይህን፡ ወሳኝ፡ ጥያቄ፡ ካልመለስን፡ የታሪክ፡ መፋረጃ፡ መሆናችን፡ አይቀርም።
በአጠቃላይ፡ ሲታይ፤ የእርስ-በእርስ፡ ክስ፤ የእርስ-በእርስ፡ መዘላለፍ፤ የእርስ-በእርስ፡ መጠላለፍ፤ ስም፡ማጥፋት፡ ወዘተ፤ ሌላው፡ (ቢያንስ፡ ከህወሃት፡ ችግር፡ ጋር፡ የሚወዳደር)፡ ቅጥ፡ ያጣ፤ በግልጽ፡ የማንነጋገርበት፡ የሰነ-ልቦና፤የባህሪይ፤ የእሴት፤ የአመለካከት፡ ችግር፡ ሁለተኛው፡ ከእራሳችን፡ የመነጨ፡ ማነቆ፡ ሁኗል፡ በማለት፡ ባቀርበው፡ ከሃቁ፡ የወጣሁ፡ አይመስለኝም። ይህ፡ እራሳችን፡ መፍታት፡ ያለብን፡ ችግር፡ ነው።
ስለሆነም፤ ችግሩን፡ በሁለት፡ ዘርፍ፡ ማስቀመጥና፡ መፍትሄ፡ መፈለግ፡ የያንዳዳችን፡ ሃላፊነት፡ ሆኗል። የችግሩ፡ መፍትሄ፡ ፈላጊወች፡ ካልሆን፤ የችግሩ፡ አጋሮች፡ መሆናችን፡ አይቀርም። ሁኔታው፡ ከቀጠለ፡ ተጠቃሚው፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ ሳይሆን፡ ህወሃት፡ ነው።
የችግሮች፡ ሁለት፡ መልክ፤
አንድ፡
የጠባብ-ዘረኝነት፡ ስርአት፡ ያመጣውን፡ ጣጣ፡ በሚገባ፡ ለማስቀመጥ፡ ከተፈለገ፡ ቢያንስ፡ ከሁለት፡ አንጻር፡ መመርመር፡ ተገቢ፡ ነው። አብዛኛው፡ የተቃዋሚ፡ ዘርፍ፡ ያደረገውና፡ አሁንም፡ የሚያደርገው፡ ሃይሉን፤ እውቀቱን፤ ስብስቡንና፤ ውይይቱን፡ ከህውሃት፡ ጠባብ፡ ቡድን፡ ችግር፡ ላይ፡ ማፍሰስ፡ ነው፡ ለማለት፡ ይቻላል። ችግሩን፡ ሚዛናዊ፡ በሆነ፡ መንገድ፡ በማስረጃ፡ እየደገፉ፡ ማስቀመጥ፡ ተገቢ፡ መሆኑን፡ ባቀርብኳቸው፡ ትንተናወች፡ ሁሉ፡ አሳይቻለሁ። የእራሳችን፡ ድክመት፡ አያይዘን፡ ሳናጤን፡ በህወሃት፡ በደል፡ ማተኮራችን፡ ለመገንዘብ፤ የሚጻፈውንና፡ የሚነገረውን፡ ብቻ፡ ማየት፡ ይበቃል። ህወሃት፡ ለአሰበው፡ ‘የኢትዮጵያ፡ ተቃዋሚ፡ ሃይሎች፡ በምንም፡ አይስማሙም፤ እርስ፡ በእርስ፡ መጠላለፍ፡ ልምዳቸው፡ ስለሆነ፡ እየገባሁ፡ መከፋፈል፡ እችላለሁ’ ብሎ፡ ከስራ፡ ላይ፡ ላዋለው፡ እቅድ፡ የተጠቀመባቸውን፡ መሰረተ፡ ሃሳቦችና፡ ዘዴወች፡ ስንመለከት፡ ይህ፡ ዘዴ፡ ምን፡ ያህል፡ አገራችንና፡ ህብረተስቡን፡ እንደጎዳው፡ እናያለን። ከዚህ፡ አዙሪኝ፡ ችግር፡ ለመውጣት፡ በመጀመሪያ፡ የአስተሳሰብ፤ የአሰራር፤ የአወቃቅር፤ የአመራር፡ ለውጠች፡ ለማድረግ፡ ፈቃደኛ፡ ብቻ፡ ሳይሆን፡ ዝግጁና፡ ብቁ፡ መሆን፡ ያስፈልጋል።
ህወሃት፡ በኢትዮጵያዊነት፡ ፋንታ፡ የጎሳ፡ ስነ፡ ልቦና፡ (psychological make-up and mindset)፡ በኢትዮጵያዊያን፡ ልብ፡ እንዲቀረጽ፡ ማድረጉ፡ ለክፍፍል፡ ፖለቲካ፤ ዋና፡ መሳሪያ፡ ሆኗል። “ብሄር፤ ብሄረሰብና፡ ህዝቦች፡ በምንም፡ ሊታረቁ፡ አይችልም፤ መገንጠል፡ መብታቸው፡ ነው” የሚለውን፡ የፖለቲካ፡ አመራር፡ በ አንቀጽ፡ 39፤ አስገብቶ፡ ድጋፍ፡ ሰጭ፡ መሪወችን፤ ደጋፊወችን፡ መመልመል፤ ህዝቡና፡ አገሪቱ፡ ገደብ፡ ከሌለው፡ ርጋታ፡ የለሽ፡ ወጥመድ፤ (permanent suspense) ውስጥ፡ እንዲገቡ፡ ማድረጉ፡ ለአንድ፡ አላማ፡ ላለሞቆማችን፡ አስተዋጾ፡ እያደረገ፡ ቆይቷል። የሚያሳየው፡ ተቃዋሚው፡ የሚመራው፡በእራሱ፤ ወይንም፡ በኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ አጀንዳ፡ ሳይሆን፡ በህወሃት፡ አጀንዳ፡ ነው፡ ያሰኛል። ህወሃት፡ ይህን፡ ዘዴ፡ ስራ፡ ላይ፡ ሲያውለው፡ የአብዛኞቻችን፡ ደካማነት፤ መከፋፈል፤ የመጠራጠር፡ ባህል፤ ለስሜት፤ ለጉራ፤ ለግለኝነት፤ ለጥቅም፤ ወዘተ፡ በቀላሉ፡ የመውደቅ፡ ዝንባሌን፡ በደንብ፡ ስላጤነ፡ ነው። በእኛ፡ ላይ፡ የስነልቦና፡ ሰለባ፡ ከተካሄደ፡ የተቃዋሚው፡ ክፍል፡ እየደከመ፡ ይሄዳል፤ በረባ-ባረባው፡ ይከፋፋል።ጉልበቱን፤ እውቀቱን፤ ገንዘቡን፡ የሚያጠፋው፡ በመከላከል፡ ላይ፡ እንጂ፡ በማሸነፍ፡ ላይ፡ ያልሆነው፡ ለዚህ፡ ነው። እስከ፡ አሁን፡ የሚታየው፡ ህወሃት፤ ያለ፡ ብዙ፡ ወጭ፤ የተቃዋሚው፡ ክፍል፡ ተሳስቦ፤ እንደ፡ ሰንሰለት፡ ተያይዞ፡ በአንድ፡ አላማ፡ አይቆምም፡ የሚል፡ ስሌቱ፡ እኛ፡ በምናወራውና፡ በምናደርገው፡ ሲሳካለት፡ ቆይቷል፤ አሁንም፡ ያው፡ ነው። ማሻማት፡ የሌለባቸው፡ ምሳሌወች፡ ልስጥ።
የክርስትና፡ ሃይማኖት፡ አመራርንና፡ ተከታዮችን፡ ብንወስድ፤ ህወሃት፡ መከፋፈልን፡ ለመጠቀም፡ ገደቭ፡ እንደሌለው፡ ያሳየናል። የክርስትና፡ ሃይማኖት፡ ተከታዮች፡ የምናመልከው፡ አንድ፡ “ታቦት፤ አንድ፡ አምላክ” ነው፡ ካልን፤ ቢያንስ፡ የ 1,700 አመታት፡ ታሪክ፡ ያላት፡ የኢትዮጵያ፡ ኦርቶዶክስ፡ ቤተክርስቲያን፡ መሰብሰቢያችን፤ መታወቂያችን፤ የመንፈስ፡ ምሽጋችን፡ እንጂ፡ የጠባብ፡ ብሄርተኞች፡ መከፋፈያ፡ ቤት፡ መሆን፡ የለባትም፡ ነበር። ስለሆነም፡ በዚህ፡ እራሳችን፡ ልንጠብቀውና፡ ልንከባበከው፡ በምንችል፡ ታሪካዊ፡ ተቋም፡ ውስጥ፡ የሚካሄደው፡ ክፍፍል፡ ከየት፡ እንደመጣ፡ አውቀን፡ መፍትሄ፡ መሻት፡ የህወሃትን፡ ፈቃድ፡ አይጠይቅም። ተቋሙን፡ መጠበቅ፡ ለፍትሃዊ፡ ስርአት፡ እውን፡ መሆን፤ ለኢትዮጵያ፡ ዘላቂነት፤ ለኢትዮጵያዊያን፡ ክብር፤ ለማንነታችን፡ አስፈላጊ፡ ስለሆነ። ይህ፡ የህወሃትን፡ ፈቃድ፡ አይጠይቅም።
የተቋማት፡ አድሏዊ ፡ሚና፡
በአንድ፡ የዘረኛ፡ ክልል፡ ቡድን፡ ፍላጎትና፡ ጥቅም፡ የሚመራ፤ በስልጣንና፡ የኢኮኖሚ፡ ጥቅም፡የተሳሰረ፤ የተቆላለፈ፤ እርስ፡ በእርሱ፡ የሚረዳዳ፤ ተቋሞቹን፡ ሁሉ፡ (የአመራር፣ የመከላከያ፤ የስለላ፤ የፌደራል፡ ፖሊስ፤ የውጭ፡ ጉዳይ፤ የባንክ፤ የገንዝ፤ የመሬት፡ ይዞታ፤ ሌሎች፡ የተፈጥሮ፡ ሃብት፡ ዘርፎች፡ አስተዳደርና፡ ስርጭት፤ የውጭ፡ እርዳታ)፡ ሙሉ፡ በሙሉ፡ የበላይነት፡ ወደ፡ እራሱ፡ ደጋፊወቹና፡ ፓርቲው፡ ተቆጣጣሪነት፡ ያዛወረው፡ ሌላው፡ አጎብዳጅና፡ ጥገኛ፡ እንዲሆን፡ በማሰብና፡ በማድረግ፡ ነው። ለዚህ፡ ዘዴ፡ እንዲጠቅ፡ ተብሎ፡ ህወሃት፤ የትግራይን፡ ክልል፡ ከሌላው፡ ለይቶ፤ ከመጠን፡ በላይ፤ ግልጽ፡ አድሏዊነት፡በሚያሳይ፡ መልኩ፡ ፈርጂ፡ የሌለው፡ መዋእለ፡ ንዋይ፡ (financial and material investments): ከማእከላዊ፡ መንግስት፡ እየወሰደ፡ ለመሰረተ፡ ልማት፤ ለፍጆት፡ እቃ፡ ማምረቻ፤ ለስራ፡ እድል፡ ማስፋፊያ፤ ለጥቂቶች፡ መክበሪያ፡ ወዘተ፡ ብዙ፡ ቢሊየን፡ ብር፡ አፍስሷል፤ አሁንም፡ ያፈሳል። ህወሃት፡ ይህን፡ ሲያደርግ፡ ዋጋ፡ የሚከፍሉት፡ ሁለት፡ የህብረተስብ፡ ክፍሎች፡ ናቸው። አንዱ፤ ቀረጥ፡ ከፋይ፡ የሆነው፡ አብዛኛው፡ የኢትዮጵያ፡ ድሃ፡ ሕዝብ፡ ሲሆን፤ ሌላው፡ በአድሎ፡ እድገት፡ አገኘ፡ የሚባለው፡ የትግራይ፡ ህብረተሰብ፡ ነው። ለዚህ፡ ህብረተሰብ፡ ጎጂ፡ የሚሆነው፡ ቀረጥ፡ ከፋዩ፡ አብዛኛው፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ አድሎውን፡ ሙሉ፡ በሙሉ፡ ስለሚያውቅ፡ ሊረሳው፡ አይችልም። የትግራይ፡ ወጣቶች፡ የትምህርት፤ የስራ፡ የመሾም፡ እድል፡ ሲያገኙ፡ ሌላው፡ እንዴት፡ ይህ፡ ሊሆን፡ ቻለ፡ ብሎ፡ መጠየቁ፡ የማይቅር፡ ነው። ስርአቱ፡ ፍትሃዊ፡ ስርጭትን፡ ለማምጣት፡ አለመቻሉን፡ ህዝቡ፡ በግልጽ፡ እያየው፡ ነው። ስለሆነም፡ የትግራይ፡ ህብረተሰብ፡ ይህን፡ የአጭር፡ ጊዜ፤ ከፖለቲካና፡ ከጠባብ፡ ዘረኝነት፤ ከዘር፡ ጥላቻ፡ የመጣ፡ ጥቅም፡ መቃወም፡ አለበት። ወደፊት፡ የሚያመጣውን፡ አደጋ፡ ማየት፡ ለዚህ፡ ይጠቅማል።
አድሎ፡ ስላለ፡ በጀምላ፡ መወንጀል፡ ይቁም፡
ይህ፡ የህወሃት፡ ሙሉ፡ የፖለቲካና፡ የኢኮኖሚ፡ የበላይነት፡ ቢያንስ፡ ሁለት፡ ያልተጠበቁ፡ ሁኔታወችን፡ ያሳያል። በአንድ፡ በኩል፡ ሌላ፡ መግቢያ፡ ቀዳዳ፡ስለሌለ፡ ብዙ፡ ኢትዮጵያዊያን፡ ወደዱም፡ ጠሉም፡ መሬት፤ ቤት፤ ፋብሪካ፤ ተቋም፤ ሌላም፡ ሃብት፡ ለመያዝና፡ ለማቋቋም፡ ከህወሃት፡ ባለስልጣኖች፡ ፈቃድ፡ ማግኘት፡ ግዴታ፡ ሁኖባቸዋል። በሃገራቸው፡ ይህን፡ ስላደረጉ፡ መወንጀል፡ አለባቸው፡ የሚል፡ ግምት፡ የለኝም። ኢላማው፡ ስርአቱን፡ ለመለወጥ፡ እንጂ፡ ማንንም፡ ለመኮነን፤ ለማውገዝ፤ ለመወንጀል፡ መሆን፡ የለበትም። ጎሳ፡ መኮነን፤መወንጀል፡ የህወሃት፡ ጠባብ፡ ቡድን፡ እሴት፡ እንጂ፡ የአብዛኛው፡ ኢትዮጵያዊ፡ እሴትና፡ ልምድ፡ አይደለም። የአማራ፤ የትግራይ፤ የኦሮሞ፤ የጉራጌ፤ የአኗክ፤ ወዘተ፡ ባህልና፡ ልምድ፡ አይደለም። ሁለተኛው፡ ነጥብ፤ ህወሃት፡ ሆነ፡ ብሎ፤ ትግራይን፡ እንደምሽግ፡ ለመጠቀም፤ ህብረተሰቡን፡ ከሌሎች፡ ወገኖቹ፡ ጋር፡ እንዲጣላ፡ ለማድረግ፡ ያቀደውን፡ ስልት፡ አይተን፡ መላውን፡ የትግራይ፡ ህብረተሰብ፡ የጠባቡ፡ ቡድን፡ አጋር፡ ነህ፡ ማለቱ፡ ህወሃት፡ ካጠመደው፡ ወጥመድ፡ መግባትና፡ ጠባቡን፡ ቡድን፡ የሌለ፡ ክብር፡ መስጠት፡ ነው። ይህን፡ ስል፡ በሁለቱም፡ ጎራ፡ ያሉ፡ ግለሰቦች፡ ለጥቅም፡ ብቻ፡ ብለው፡ ህሊናቸውን፡ አልሸጡም፡ ማለቴ፡ አይደለም። ባጠቃላይ፡ ሲታይ፡ ግን፡ በጀምላ፡ ማንንም፡ ክፍል፡ መኮነን፤ መዝለፍ፤ ማዋረድ፤ መወንጀል፡ ወደ፡ ተፈለገው፡ ብሩህ፡ አላማ፡ ሊወስደን፡ አይችልም። ይህ፡ የመወነጃጀል፡ ባህል፡ በሙሉ፡ እንዲቆም፡ ሁላችንም፡ ጥረት፡ የምናደርግበት፡ ጊዜ፡ አሁን፡ ነው።
የሰብአዊ፡ መብቶች፡ መገፈፍ፡ በ ጎሳ፡ መለየቱ፡ ያዘገንናል፡
ከላይ፡ የጠቀስኳቸውንና፡ ሌሎች፡ የአስተሳሰብ፡ ለውጦች፡ (redirection) ከስራ፡ ላይ፡ ለማዋል፡ እራሱን፡ መርጦ፡ የስልጣን፡ ቁንጮ፡ የያዘው፡ ብሄርተኛ፡ ቡድን፤ ህወሃት፤ እኛን፡ በግልጽ፡ ሆነ፡ በምስጢር፡ ለመያዝና፡ ለመሳብ፡ አጎልማሽ፡ ሁኔታወችን፡ (enabling conditions) አስቀድሞ፡ መፍጠሩን፡ ማጤን፡ያስፈልጋል። አጎልማሽ፡ ሁኔታወችን፡ ፈጥሮ፡ እኛን፡ የእራሱ፡ አጀንዳ፡ ተከታዮች፡ ማድረጉ፡ ጥንካሬውን፡ ያሳያል። ለምን፡ ብንል፤ እያወቅንም፡ ሆነ፡ ሳናውቅ፡ ብዙወቻችን፡ ባዘጋጀልን፡ የጥላቻ፡ መርዝ፡ ተዘፍቀናል፤ ለመውጣት፡ ሲያዳግተን፡ እንታያለን። ለምሳሌ፤ በቅርቡ፡ የአማራ፡ ህብረተሰብ፡ ክፍል፡ ሆነ፡ ተብሎ፡ (deliberate ethnic cleansing and dispossession) ‘የተፈረደበት፡’ ህብረተሰብ፤ እንደከብት፤ በጀምላ፡ ከጉራ፡ ፈርዳ፤ ደቡብ፡ ክልል፡ ኢሰባዊ፡ በሆነ፡ መንገድ፡ ተገዶ፡ ለስደት፡ ሲዳረግ፡ ስንት፡ የፖሊቲካና፡ የማህበራዊ፡ ድርጂቶች፤ የታወቁ፡ ግለሰቦችና፡ መሪወች፡ የማያሻማ፤ የሚያስተማምን፤ የሚያቀራርብ፤ ህዝብን፡ ከህዝብ፡ ጋር፡ በሰላም፡ እንዲኖር፡ የሚረዳ፡ አቋም፡ እንደወሰዱ፡ አይተናል። የሰባዊ፡ መብቶች፡ መገፈፍ፡ በዘር፤ በጾታ፤ በሃይማኖት፤ በእርዮት፤ በእድሜ፡ አይለዩም። የአማራ፡ ህብረተሰብን፡ የምንለይ፡ መሆናችን፡ መለኪያው፤ ድምጻችን፡ ባለማሰማት፤ ህወሃት፡ ከሚያደርገው፡ የዘር፡ ልዩነት፡ ፍልስፍና፡ ጋር፡ ከመቆም፡ ምንም፡ ለመለየት፡ አለመቻሉ፡ (indistinguishable)፡ መሆኑ፡ ነው። በፍትህ፤ በእርትእ፤ በህግ-የበላይነትና፡ በሰብአዊ፡ መብቶች፡ ማመን፡ ማለት፡ ማንንም፡ ኢትዮጵያዊ፡ ከሌላው፡ ሳይለዩ፡ ድምጽ፡ ማሰማት፤ አቋም፡ መውሰድ፤ መታደግ፡ ማለት፡ ነው።
ሰባ፡ ስምንት፡ ሽህ፡ ህዝብ፡ በአንድ፡ ጊዜ፤ ከአንድ፡ ቦታ፤ ከአንድ፡ ብሄረሰብ፤ በቋንቋው፡ ተለይቶ፡ ከማሳው፡ ተፈነቅሏል። አንዲት፡ እናት፡ ልጂ፡ ወልዳ፡ በወለደችበት፡ ሌሊት፡ ከቤቷ፡ ተገዳ፡ ወጥታለች። እርጉዝ፡ ሴቶች፡ ለጤናቸው፡ በሚያሰጋ፡ ሁኔታ፡ እንደ፡ ተራ፡ ወንጀለኛ፡ ክብራቸው፡ ተገፎ፡ ቤታቸውን፡ ለቀው፡ እስር፡ ቤት፡ ገብተዋል። ህጻናት፤ ወጣቶች፤ እናቶች፤ እሰከ፡ ሰማኒያ፡ ዘጠኝ፡ አመት፡ የሆናቸው፡ አዛውንቶች፡ ለእስር፡ቤት፡ ተዳርገዋል። ሰላማዊ፡ ገበሬወች፡ ከእርሻ፡ መሬታቸው፡ ከሰብላቸው፤ ከአትክልታቸው፤ ከኑሯቸው፡ ተገደው፡ ህየወታቸው፡ ወደ፡ አስጊ፡ ደረጀ፡ ተለውጧል። እነዚህ፡ ኢትዮጵያዊያን፡ ሁሉ፤ ከቤታቸው፤ ከሃብታቸው፤ ከንብረታቸው፡ ተገደው፡ ሲሰደዱ፤ ሲታሰሩ፤ የሚገፈፉት፡ ሃብት፡ ብቻ፡ አይደለም።
ሰው፡ ለምኖም፡ ቢሆን፡ ያድራል። አሰቃቂው፡ ግን፡ ከክብራቸው፤ ከማእረጋቸው፤ ከማንነታቸውን፤ ከሰብእነታቸውን፡ ጭምር፡ መሆኑ፡ ነው። በአማራው፡ ሆነ፤ በአፋር፤ በኦጋዴን፤ በኦሞ፡ ሸለቆ፤ በጋምቤላ፤ በኦሮሚያ፤ ለሚካሔደው፡ ማንኛውም፤ የሰብእነት፤ የክብር፤ የማንነት፡ ገፈፋ፡ (recurring violations of human dignity and human rights)፤ ለገጠማቸውና፡ ለሚገጥማቸው፡ ሁሉ፡ ያለ-አድሎ፤ በግልጽ፡ መቃወም፡ አዲሱ፡ መለኪያችን፡ (criteria) መሆን፡ አለበት። ድምጽ፡ ሳያሰሙ፤ አቋም፡ ሳይወስዱ፡ እንዲሁ፡ ህወሃትን፡ መኮነን፡ በቂ፡ ሊሆን፡ አይችልም። በመኮነን፤ በመወንጀል፤ ስም፡ በማጥፋት፡ ለውጥ፡ ለማምጣት፡ ቢቻል፡ ኖሮ፡ ህወሃት፡ እስካሁን፡ በስልጣን፡ ላይ፡ አይቆይም፡ ነበር። የዘጠና፡ ሰባቱ፡ ምርጫ፡ የሚያሰተምረን፡ በመወነጃጀል፤ ለስልጣን፡ በመወዳደር፤ በመካካድ፡ ባህል፡ የኢትዮጵያን፡ ሕዝብ፡ አመኔታ፡ አጥተናል። ልዩ፡ ልዩ፡ መልኪያወች፡ የሚያሳዩት፤ ከህዝቡ፡ ጋር፡ የሚቆምበት፡ “ስድሳ፡ ስድስት፤ ስድሳ፡ ስድስትን” የሚሸትና፡ የሚመስል፡ ጊዜ፡ እያየን፡ ነው። ይህን፡ እድል፡ በጥበብ፡ ለመጠቀም፡ የህወሃትን፡ ፈቃድ፡ አይጠይቅም።
ይህን፡ ግንዛቤ፡ ለማቅረብ፡ ያስቻሉኝ፡ ምልክቶችና፡ ምክንያቶች፡ እነሆ። በመሬት፡ ነጠቃና፡ በህዝብ፡ መፈናቀል፡ የተነሳ፡ የጋምቤላ፡ ህብረተሰብ፡ እራሱን፤ ክብሩን፤ ጥቅሙን፡ ለማስከበር፤ በህይወቱ፡ መስዋእት፡ እየከፈለ፡ ነው። የኦጋዴን፡ ህብረተሰብ፡ አሁንም፡ ለመብቱ፡ እየሞተ፤ ዋጋ፡ እየከፈለ፡ ለመብቱ፡ ይታገላል። የአፋር፡ ህብረተሰብም፡ እንደዚሁ። የኦሮሞ፡ ህብረተስብ፡ በህይወቱ፡ ዋጋ፡ ሲከፍል፡ ቆይቷል፤ አሁንም፡ እየከፈለ፡ ነው። በስሜን፡ ኢትዮጵያ፡ የጎንደር፡ ክፍለ፡ ሃገር፡ ህዝብ፡ የህዋሃት፡ መንግስት፡ የውስጥና፡ የውጭ፡ የመሬት፡ ነጠቃ–ለሱዳን፡ መንግስት፡ በምስጢር፡ ለም፡ መሬት፤ ደንና፡ ወንዞች፡ ከህግ፡ ውጭ፤ ህዝቡን፡ ሳያማክር፡ የሚያደርገውን፡ አገርና፡ ደንበር፡ ለዋጭ፡ ተግባር፡ ሲቃወም፡ መቆየቱን፡ ታሪክ፡ ይመስክራል። ከጥቅም፡ ላይ፡ ያልዋለ፡ ሰፊ፡ መሬት፡ አለ፡ የሚለው፡ ህወሃት፤ የጥንት፡ ቅርስ፡ የሆነውን፤ ለተከታታይ፡ ትውልድ፡ መታወቂያና፡ መኩሪያ፤ መተኪያ፡ የማይገኝለትን፡ የዋልድባ፡ ገዳም፡ ለም፡ መሬት፡ ለስኳር፡ ፋብሪካ፡ በሚል፡ ሲያርሰው፡ ህብረተሰቡ፡ በህይወቱ፡ ዋጋ፡ ለመክፈል፡ መዘጋጀቱን፡ እያሳየ፡ ይገኛል። ይህ፡ ጥሪት፡ የጎንደሬ፡ አማራ፡ ብቻ፡ አለመሆኑን፡ አውቆ፡ አብሮ፡ መሰለፍ፡ የህወሃትን፡ ፈቃድ፡ አይጠይቅም። ሌላው፤ የኢትዮጵያ፡ ገበሬ፡ መሬት፡ ጠቦት፡ ሊለማ፡ የሚችልውን፡ ለም፡ መሬትና፡ ደጋፊውን፡ ወንዝ፡ በብዛት፡ ሆነ፡ ብሎ፡ 36 አገሮችን፤ 8,000 የውጭ፡ ግለሰብ፡ ሃብታሞችን፡ ለም፡ ጋብዞ፡ ሲያቀራምት፤ ይታያል። ይህ፡ ከእርሻ፡ መሬት፡ ጋር፡ የተያያዘ፡ አዲስ፡ የቅኝ፡ ገዦች፡ ግብዣ (colonization by invitation) መላውን፡ ህዝብ፡ እንዳሳሰበው፡ ምልክቶች፡ አሉ። ይህን፡ እያደረገ፡ ዙሮ፡ ዋልድባን፡ ለስኳር፡ ማምረቻ፡ አርሳለሁ፡ ማለቱ፡ የሚያሳየው፡ የፖለቲካ፡ እቅዱን፡ እንጂ፡ ለጎንደር፤ ወይንም፡ ለመላው፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ እድገትና፡ ደህንነት፡ መቆሙን፡ አይደለም። ጉዳቱ፡ ለጎንደር፡ ህዝብ፡ ብቻ፡ ሳይሆን፡ ለመላውን፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፤ በተለይ፡ የክርስትና፡ ሃይማኖት፡ ተከታይ፡ ለሆነው፡ ነው፡ ለማለት፡ ያስችላል፡፡ ስለሆነም፡ አብዛኛውን፡ የሃይማኖት፡ ተከታይ፡ ሁሉ፡ አስቆጥቶታል፤ አስነስቶታል። እኔ፡ እንደማየው፡ ዋልድባ፡ የሚፈለገው፡ የጎንደርን፡ ህብረተሰብ፡ ኑሮ፡ ለማሻሻል፡ ሳይሆን፡ ይህን፡ የመንፈሳዊ፡ ማማና፡ ለም፡ መሬቱን፡ ወደ፡ ትግራይ፡ ለመጠቅለል፡ ነው። የጎንደር፡ ህዝብ፡ ይህን፡ ሴራ፡ አውቆ፡ ትግሉን፡ ቀጥሏል። ስለሆነም፡ ለማንኛውም፡ የህብረተሰብ፡ ክፍል፡ ትግል፡ ሊሰጠው፡ የሚገባ፡ ድጋፍ፡ ለዚህም፡ ህብረተሰብ፡ ክፍል፡ መሰጠት፡ አለበት።
ሌላው፡ ማንም፡ ሊክደው፡ የማይችል፡ የኑሮ፡ ውድነትና፡ የዋጋ፡ ግፍሸት፡ በየቀኑ፡ ማደግ፤ የነፍስ፡ ወከፍ፡ የገቢ፡ አለማደግ፤ የሃብትና፡ የኑሮ፡ ሁኔታ፡ በሚያሰቅቅ፡ ደረጃ፡ መራራቅ (gross income inequality) የሰብአዊ፡ መብቶች፡ መገፈፍ፤ ሁኔታው፡ ያስመረረው፡ አስተማሪ፡ የሰላም፡ ተቃውሞውን፡ አገር፡ አቀፍ፡ በሆነ፡ ደረጃ፡ ማቅረቡ፡ የአደባባይ፡ ምስጢር፡ ናቸው። በአጼ፡ ሃይለ፡ ስላሴ፡ ዘመነ፡ መንግስት፡ የአብዮት፡ ቀስቃሽ፡ ሆኖ፡ አገራችን፡ ለለውጥ፡ ያሸጋገራት፡ ዋናው፡ የህብረተሰብ፡ ክፍል፡ የአስተማሪወች፡ ተሳትፎ፡ ነው፡ ብል፡ አልሳሳትም። የእስልምና፡ ሃይማኖት፡ ተከታዮች፡ ህወሃት፡ በእምነት፡ ውስጥ፡ ገብቶ፡ የሚያደርገውን፡ ብጥብጥና፡ መከፋፈል፤ ሃይማኖትን፡ ለፖለቲካ፡ ስልጣን፡ መሳሪያ፡ ማድረግ፡ ተቃውመው፡ ከዘጠና፡ ሰባት፡ ወዲህ፡ ታይቶ፡ የማያውቅ፡ ሰላማዊ፡ ሰልፍ፡ አድርገዋል።ብዙ፡ ሰላማዊ፡ ሰወች፡ ሙተዋል። ይህን፡ ሰላማዊ፡ ሰልፍ፡ የክርስትና፡ ሃይማኖት፡ ተከታዮች፡ እንደሚደግፉት፡ ይነገራል። ተስፋ፡ የሚሰጠው፡ እነዚህ፡ አንጋፋ፡ የሃይማኖት፡ ዘርፎች፡ ከጥንት፡ ጀምሮ፡ በሰላም፤ በመከባበር፤ የቆየውን፡ የኢትዮጵያዊነት፡ እሴት፡ ከስራ፡ ላይ፡ እያዋሉ፡ መሆናቸው፡ ነው። ይህ፡ የመተባበር፡ ሰላማዊ፡ ትግል፡ ከቀጠለ፡ ትኩረቱ፡ ከዋናው፡ የህወሃት፡ ከፋፋይ፡ ስርአት፡ ላይ፡ እንጂ፡ ከህዝብ፡ ክፍፍል፡ ላይ፡ አይሆንም፡ የሚል፡ ግምት፡ አለኝ። የታሪክ፡ ሃላፊነት፡ የሚጠይቀው፡ ይህን፡ ተባብሮ፡ አገርን፡ ከአደጋ፡ መከላከል፤ የኢትዮጵያን፡ ሕዝብ፡ በሙሉ፡ በሰላም፤ ከድህነት፤ ከእርሃብ፤ ከስደት፤ ከኋላ፡ ቀርነት፡ ነጻ፡ የሚሆንበት፡ ድልድይ፡ በየፊናችን፡ ማመቻቸትና፡ መገንባት፡ ብቻ፡ ነው።
በሌላ፡ በኩል፡ የምገነዘበው፡ በየቦታው፡ የምናየው፡ ይህ፡ ሁሉ፡ ያልተቀነባበረ፡ የሰላማዊ፡ ህዝብ፡ እንቅስቃሴ፡ አገር-ቤት፡ ሲካሄድ፡ በውጭ፡ ሆነ፡ በውስጥ፡ ያሉ፡ የፖለቲካና፡ የማህበራዊ፡ ስብስብስቦች፡ የማቀነባበር፤ የአቅጣጫ፡ መስጠት፤ የገንዘብ፤ የሃሳብ፤ የዲፕሎማቲክ፤ የሞራል፤ ድጋፍ፡ የመስጠት፡ ሚናቸው፡ አለመታየቱ፡ ለምን፡ ይሆን፡ የሚለውን፡ ነው። ከላይ፡ እንዳሳየሁት፤ ህወሃት፡ የፈጠረልን፡ የስነ-ሊቦና፡ ወጥመድ፡ ማነቆ፡ መሆኑ፡ አያጠራጥርም። መረዳት፡ ያለብን፤ አገር- ቤት፡ ለሚካሄደው፡ ሰላማዊ፡ የፍትህ፤የእርትህ፡ ትግል፡ ድጋፍ፡ የመስጠት፤ ያለመስጠት፡ አዛዡ፡ ህወሃት፡ አይደለም፤ ሊሆንም፡ አይችልም። የፖለቲካ፡ ሆነ፡ የማህበራዊ፡ እንቅስቃሴወች፡ ሁሉ፡ በህወሃት፡ አጀንዳ፡ አንመራም፡ ብለው፡ ካመኑ፡ ልዩ፡ ልዩ፡ እድሎችን፡ የመጠቀም፤ የማያያዝ፤ የመሰብሰብ፤ የማገናኘት፤ የማቀናጀት፤ (connecting the dots) አበይት፡ ተግባራቸው፡ መሆኑን፡ የመረዳት፡ ሃላፊነት፡ አለባቸው። አገር-ቤትም፡ ሆነ፡ ውጭ፡ የሚገኙ፡ የተቃዋሚ፡ ሃይሎች፡ ይህን፡ የተቀደሰ፡ ተግባር፡ ከስራ፡ ላይ፡ ለማዋል፡ በቅተው፡ ካልተነሱ፡ የታሪክ፡ ተጠያቂወች፡ ይሆናሉ፡ ለማለት፡ የምደፍረው፡ ለዚሁ፡ ነው።
በአጠቃላይ፤ ኢትዮጵያና፡ መላው፡ ሕዝቧ፡ የሚስፈልጋቸው፤ ከድህነት፤ ከእርሃብ፤ ከስደት፤ ከጥገኝነት፤ ከሃፍረት፤ ከፍርሃት፤ ከአድሎና፡ ከሙስና፤ ከማንኛውም፡ ዘርኝነት፡ ወዘተ፡ ነጻ፡ የሚያወጣቸው፤ በነጻ፡ ምርጫ፤ በህግ፡ የበላይነት፤ በእኩልነት፤ በመተሳሰብና፡ በመፈላለግ፤ በጋራ፡ ጥቅም፤ በጋራ፡ አገር፤ እሴቶችና፡ መሰረተ-ሃሳቦች፡ ላይ፡ የተመሰረተ፡ የፍትሃዊነትን፡ ምንነት፡ በሁሉ፡ ዘርፍ፡ እውን፡ የሚያደርግ፡ የፖለቲካ፡ አማራጭ፡ ጭብጥ፡ ማድረግ፡ ነው። ይህን፡ ለማመቻቸትና፡ የኢትዮጵያ፡ ሕዝብ፡ የእራሱ፡ እድል፡ ወሳኝ፡ እንዲሆን፡ ያልተቆጠቨ፡ ድጋፍ፡ መስጠት፡ የህወሃት፡ አለቆች፡ ፈቃድ፡ አይጠይቅም።
በዚህ፡አጭር፡ ትንተና፡ እንዳሳየሁት፡ ለዚህ፡ ተስፋ፡ አስተዋጾ፡ ለማድረግ፡ በመጀመሪያ፡ እያንዳንዳችን፡ ካለፈው፡ ከመራራ፡ ፖለቲካ፤ ከቂም፡ በቀልነት፤ ከሃሜት፤ ከአሉባልታ፤ ከፍርሃት፡ ባህል፡ በተቻለ፡ መጠን፡ እራሳችን፡ ነጻ፡ ማውጣት፡ አለብን። ህወሃት፡ በቀባን፡ ወይንም፡ እራሳችን፡ በፈጠርነው፡ የጥላቻ፡ መርዝ፤ የሃሜት፤ የእርስ፡ በእርስ፡ መጠላለፍ፤ የጉራ፡ ወዘተ፡ ባህል፡ ተዘፍቀን፡ ለአሁኑና፡ ለወደፊቱ፡ ትውልድ፡ አርአያ፡ ለመሆን፡ እንችልም። ለዲሞክራሲ፡ ስርአት፡ አስተዋጾ፡ ለማድረግ፡ እራሳችን፡ ዲሞክራሲን፡ ከስራ፡ ላይ፡ ማዋል፡ አለብን። አለበለዚያ፡ ጸረ-ዲሞክራሲ፡ ከምንለው፡ ከህወሃት፡ የምንለይበት፡ መሰረት፡ ሊኖረን፡ አይችልም።
ይቀጥላል…

Ethiopian terrorism trial delayed

2012-05-11 19:16 -AFP
lineAddis Ababa - An Ethiopian judge delayed the verdict on Friday in the case of 24 people charged with terrorism, including prominent journalist Eskinder Nega and opposition member Andualem Arage.

The conclusion of the trial, which has been widely condemned by human rights organisations, was postponed until June 21 because the judge had not received a full transcript of the defendants' case.

"We will not give a decision because some parts of the defence are not transcribed," Judge Endashaw Endale told the courtroom.

The 24 on trial were charged with terrorism in September 2011, and potentially face the death penalty if found guilty.

Only 20 people were allowed into the crowded courtroom, including US Ambassador Donald Booth, journalists and family members.

About two dozen people remained outside because of space restrictions.

The group is charged under Ethiopia's anti-terrorism legislation, which rights groups have criticised of being used to stifle peaceful dissent.

Last week Eskinder was honoured in New York with a "freedom to write" award by the US-based press watchdog PEN.

Eskinder was arrested after publishing an article questioning arrests under the anti-terrorism legislation.

He is among 11 independent journalists and bloggers Addis Ababa has charged with terrorism since 2011, according to the Committee to Protect Journalists, which says Ethiopia's media is one of the most restricted in the world.

In December, two Swedish journalists were found guilty on terror charges after they were arrested with members of an outlawed group. They were sentenced to 11 years in prison.

Geldof urges more tolerance for Ethiopia civil society..AFP-16hrs ago

Aid activist and Irish pop star Bob Geldof on Friday urged Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi to be more inclusive and tolerant of civil society groups.
"If they keep saying 'you can't write anything critical,' they're in trouble," Geldof told AFP. "Have them participate, allow the pressure valve to come off," he added.
He said Ethiopia must follow the example of Western nations, which developed only with greater freedom of expression. Unless Ethiopia becomes more tolerant, he cautioned, it could reverse recent economic and social progress.
"It will stumble if they don't bring their people into the argument," he warned, adding that Meles is a "very intelligent leader who truly understands government."
Rights groups have criticized Ethiopia for using its anti-terror legislation to stifle peaceful dissent and restrict freedom of the press. Close to 200 people were arrested under the law in 2011.
Geldof said Ethiopia's system of federalism had bred dissent throughout the country, but warned that opposition activity could become a political threat if they are not offered a voice in national politics.
"You cannot stifle people's voices. If it became more inclusive, if argument was allowed if the country -- if civil society is allowed to breathe -- then you would see a reduction in all this independence activity," he said.
"One way or another, civil society will win. They will win, there's more of them, and people will breathe."
Geldof led a campaign to raise $1 million for Ethiopian famine victims in the 1980s. He was in the Ethiopian capital for the World Economic Forum, which closes Friday.
Alongside fellow pop star Bono, he has advocated for greater aid from the West to help lift African countries out of poverty.
There are currently 24 people, including prominent journalist Eskider Nega and opposition member Andualem Arage, on trial for "terrorism" in Ethiopia.
In December, two Swedish journalists accused of terrorism were sentenced to 11 years in prison.

Canada to cut aid to Ethiopia

 
Ethiopians from the township of Feji Goba pick up bags of maize they receive through an emergency food assistance program in Shashemene, Ethiopia, after prolonged droughts affected their crops, February 3, 2012. The relief program is funded by CIDA and run by the Canadian Foodgrains Bank and its partners.
 

Ethiopians from the township of Feji Goba pick up bags of maize they receive through an emergency food assistance program in Shashemene, Ethiopia, after prolonged droughts affected their crops, February 3, 2012. The relief program is funded by CIDA and run by the Canadian Foodgrains Bank and its partners.

OTTAWA — The Conservative government will reduce aid to Ethiopia as part of its effort to slash $377 million in foreign aid over the next three years.
“Ethiopia has been identified as one of the countries where CIDA will reduce its bilateral programming,” the office of International Cooperation Minister Bev Oda said in an email statement. Oda’s office would not disclose the amount of the cuts.
In 2010-11, Canada spent more than $176 million in Ethiopia, making it our third-largest aid recipient after Haiti and Afghanistan. This year’s cut will be the second in a row and comes as the country continues to face food shortages following a devastating drought last year that saw more than one in 10 citizens receive some level of food assistance.
Cuts are also coming to 12 of the world’s poorest countries, Postmedia News reported last month. Benin, Niger, Cambodia, China, Nepal, Rwanda, Zambia and Zimbabwe are expected to lose virtually all Canadian aid funding.
The news comes as the World Economic Forum, which Oda attended, wrapped up Friday in Addis Ababa, Ethiopia’s capital. European financial woes are expected to slow investment across Africa, but oil-rich Middle-Eastern investors are looking increasingly to Africa, attracted by some of the world’s fastest growing economies, rapidly rising disposable incomes and relative political stability in many countries.
Q&A: Responses from the office of International Cooperation Minister Bev Oda to the Citizen’s questions on Ethiopia.
Q: Can you confirm that Canada’s bilateral aid to Ethiopia will remain constant for 2012-13 at $146 million (same as 2011-12)? If not, what funding changes are planned for this year and coming years? Will there be changes to multilateral aid? If funding has not been cut, can you explain what specific factors led Canada to keep the funding constant in Ethiopia while a number of other African and other countries internationally are seeing funding cut or dropped altogether?
A: Ethiopia has been identified as one of the countries where CIDA will reduce its bilateral programming.
- Canada’s international development assistance will continue our government’s commitment to make our international assistance focused, effective, and accountable and that Canada will continue to deliver value for aid dollars, making a real difference in the lives of the people they are intended to help. \
- We will continue our efforts in this direction and build on steps we have taken so far. Canada will continue to build on its successes and lessons learned in its drive for focussed results benefitting the people of Ethiopia to build upon the results, successes and lessons learned in Ethiopia to provide the best use of our aid dollars.
- CIDA will maintain strong partnerships with key multilateral and global partners and will continue to respond quickly and effectively to humanitarian crises.
- We are consolidating some programming and winding down support where Canadian commitments have been met.
- At the same time, Canada continues to provide leadership and investments to various important multilateral initiatives such as the Global Fund to Fight AIDS, Tuberculosis and Malaria, and the Global Partnership for Education.
- Canada also continues its support to development banks that provide financing to developing countries to boost economic growth and UN organizations that provide support and engage with developing countries on a wide range of issues in all corners of the world.
- CIDA will eliminate/reduce modest multilateral investments that have high operating costs, that have overlap with other programming or that do not closely align with CIDA’s thematic priorities.
Q: How much do trade and strategic/security concerns factor in to Canada’s bilateral aid strategy for Ethiopia?
A: Results and effectiveness are at the forefront of the development agenda.
- Canada’s aid achieves concrete results.
- For example, we support programs that help alleviate hunger in developing countries, enable millions more children to be in school, and help developing countries ensure the essential elements for sustainable economic growth are in place.
- Canada is also leading a global effort to help improve the health of mothers and children and reduce the number of preventable deaths.
Q: Does Canada support the Ethiopian government’s resettlement of Ethiopians to make way for large-scale commercial agriculture developments? Will CIDA fund NGOs that help with the humanitarian effects of the resettlement policy, as it has said it would for Canadian mining projects?
A: CIDA does not provide support to the Government of Ethiopia’s Commune Program nor to any industrial and large scale commercial agriculture projects.
- CIDA currently has no bilateral programming related to the resettlement policy.
Q: Why does Canada continue to support, through its bilateral aid, a government in Ethiopia that has jailed its opposition and critical journalists, limits the work of groups to do advocacy work and democratic development, and is seen by most observers as a repressive, undemocratic regime that routinely abuses the human rights of its citizens?
A: Canada takes human rights, including the persecution of LGTBQ individuals, into consideration when determining the most effective distribution of aid, and Canada takes allegations of human rights abuses in Ethiopia very seriously.
- Canada does not provide direct budget support to the Government of Ethiopia.
- Canada’s development assistance to Ethiopia is channelled through international, multilateral and Canadian organizations.
- Canada attaches conditions and controls to its development assistance delivery mechanisms in all recipient countries, including Ethiopia to prevent misuse of Canadian taxpayers’ dollars.
Q: Some NGOs complain that CIDA’s new competitive-bid protocols on applying for project funding via the Partnership Branch favour short-term projects to the detriment of the long-term projects they think a country with deep-seated poverty like Ethiopia needs. What is CIDA’s response to this, and does it plan any changes to this protocol? Will there be any change of focus to the kinds of projects the Partnership Branch funds in Ethiopia and through which partners it will fund them?
A: Efficiency, effectiveness and the capacity to deliver concrete results are the key criteria for allocating development resources. The most meritorious proposals put forward by Canadians organizations will continue to be funded.
- CIDA’s Partnerships with Canadians Branch (PWCB) recognises that Canadian organizations are respected, effective and experienced in work with the objective of poverty reduction in developing countries.
- Our Government respects the wishes of Canadians who want Canada to do its part to help those living in poverty. Canadian tax payers also want Canada’s international assistance to be effective and make a real, sustainable difference to help those we intend to help.
- Under its Partners for Development Program, CIDA selects effective, and cost -efficient projects that will deliver results and outcomes in an accountable way.
- CIDA’s support decisions are made according to the merits of proposals, good use of tax payers dollars and results to be achieved, not only based on organizations. Canada is fortunate to have many organizations based in every region of Canada and CIDA receives many worthwhile proposals. However, not every proposal can be supp

Friday 11 May 2012

Breaking News: Thousands of Muslims have protested against the government today


ADDIS ABABA — Security was tightened in the Capital Addis Ababa. Defying government threats, Ethiopian Muslim have vowed to continue their protests against the “Ahbashism Campaign” instigated by the government and “Majlis”.
“Call me a terrorist but I will defend my religion,” a muezzin in a mosque at the outskirts of Addis Ababa said in his sermon, denouncing the Al Ahbash movement, Reuters reported.
Over the past few weeks, Muslim protests have been causing concern in the predominantly Christian nation that takes pride in centuries of coexistence.
Thousands of Muslims have protested against the government’s oppression of their community, accusing it of spearheading a campaign in collaboration with the Majlis to indoctrinate Muslims with the ideology of a sect called “Ahbash”.
Protesters were further infuriated when Ethiopian police shot dead seven Muslims in Assasa town in Arsi province of Oromiya regional state two weeks ago.
Witnesses say the Muslim victims fell when Ethiopian security forces surrounded a mosque to arrest Sheikh Su’ud Aman on accusations of prompting “terrorist” ideology.
Scores of people were also reportedly injured in the incident.
Observers said the brutal killing of innocent people in Assasa town has fueled tension between the government and the Muslim community.
Muslims say the government is spearheading a campaign in collaboration with the Supreme Council of Islamic Affairs to indoctrinate their community with the ideology of a sect called “Ahbash”.
The government of Ethiopian Premier Meles Zenawi has put the Ahbash in charge of the religious affairs of Ethiopia’s Muslims.
Muslims say the government move is in violation of the constitution, which prevents the government interference in religious affairs.
Muslims also accuse the Ahbash of launching an “indoctrination program” in predominantly Muslim areas, forcing people to attend “religious training” camps or risk police interrogation and possible arrest.
Founded by Ethiopian-Lebanese scholar Sheikh Abdullah al-Harari, Ahbash is seen by the West as a “friendly alternative” to Wahabi ideology, which the West sees as extreme and militant.
Muslims say Ahbash imams are being brought over from Lebanon to fill the Majlis and teach Ethiopians that “Wahabis” are non-Muslims.
Interference
Ethiopian Muslim activists confirmed that protesters reject any government interference or trial to impose Ahbashism ideology on their society.
“It (Al Ahbash) has the right to exist in Ethiopia, but it is unacceptable that the Council tries to impose it on all members of the Muslim community,” Abubeker Ahmed, an Ethiopian Muslim activist and head of an independent Islamic arbitration committee, told Reuters.
He said the government wanted to prevent a vote to elect a new council and replace the decade-old one.
He added that the appointed leadership of Ethiopia’s Islamic Affairs Supreme Council was not representative of the country’s Muslim community.
“They (the government) want to keep them because they agree to whatever orders,” he said.
Rejecting the government claims that hardline Islam was taking root in the Horn of Africa country, some protesters say the government’s strategy might backfire, sowing the seeds of the hardline Islam it seeks to keep at bay.
“We are against any sort of extremism ourselves,” said Ahmed Mustafa, secretary of the independent arbitration panel.
“We want to stop such thinking.”
Ethiopia, Africa’s second most populous country, is home to 60 percent Christian and about 34 percent Muslim, according to CIA factbook.

መንግስትን ሆይ ሲደግፉህ እሺ በል … ሞቅ ብሎሃልና! (አቤ ቶኪቻው)

ጋሽ ግዛው በድፍን ሽሮሜዳ ታዋቂ የነበሩ ሞቅታን እንደገንዘብ እየቆጠቡ የሚጠቀሙ ሰው ነበሩ። እርሳቸውን ሳይሰክሩ ያያቸው ሰው ካለ እርሱ አብሯቸው ያደረ መሆን አለበት፤ በቀረ ግን ሁሌም ሞቅታ ውስጥ ናቸው።
ጋሽ ግዝሽ ሁልግዜም ወደቤታቸው የሚገቡት እምቢኝ እያሉም ቢሆን፤ በሰዎች ተደጋግፈው ነው። አንዳንዴም በወሳንሳ! አለበለዛ ሲወድቁ ሲነሱ የሚያዩት አበሳ አይወሳ…! ጋሽ ግዛው በሞቅታቸው ተዓምር ካመጡት ልዩ ልዩ ጠባይ ውስጥ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ። ከመንግስታችን ተዓምራዊ በሀሪያት ጋር እየተነፃፀረ ይቀርባል።
አንድ፡
ያለ አጠጋቢ ምክንያት መሳደብ እና መዝለፍ። ለነገሩ ምክንያቱ ለርሳቸው አጥጋቢ ነው በሞቅታ ውስጥ ለመግባት ላልታደለ ሰው ግን፤ “እንዲህ አይነት ክፉ ቃል ከእርሳቸው አንደበት ይጠበቃል?” በሚያስብል መልኩ አላፊ አግዳሚውን እና በአግዳሚ ወንበር ላይ የተቀመጠውን ጠጅ ጠጪ ሁላ ሙልጭ አድርገው ነው የሚሳደቡት። መንግስታችን በተለይም ዋናው ጠቅላይ ሚኒስትራችን በፓርላማ ዘመናቸው የሰነዘሩብንን ሃይለ ቃል… (ስድብ ማለት አላስችል አለኝ እኮ!) ያ ታማኝ በየነ ለታሪክ ይሆናል ብሎ ሰብስቦ አስቀምጦልዎታል  ከጥቂቶቹ መካከል “ቆሻሻ… በክት… የበሰበሰ…እብድ ውሻ…” የሚሉት ይበልጥ እውቅና ያገ  ስድቦቻቸው ናቸው። በእውነቱ እንዲህ አይነቱን ስድብ ጋሽ ግዛውም አይሞክሩትም።
በተለይ አሁን አሁን የሀይማኖት ሰዎች ላይ የሚያወርዱትን የስድብ ናዳዎች ስናይ በእውኑ መንግስታችን ሞቅ ብሎታል ያሰኛል። መቼም አንድ መነኩሴን “የተለየ የፖለቲካ አጀንዳ ያለው!” ብሎ መጠርጠር ከስድብ በላይ ነው። ስሙ ራሱ “ሰላም” የሆነውን ሙስሊም አሸባሪ ብሎ መኮነንም ደረጃውን የጠበቀ ስድብ ነው።
ሁለት
ጋሽ ግዛው ሰክረው ሲወጡ ህፃናትን ማባረር እና ሲይዟቸውም መምታት። መለያ የስካር ባህሪያቸው ነው። በርግጥ ህፃናቱም እርሳቸውን ከመተቸት ወደ ኋላ ብለው አያውቁም። “ሰካራም ቤት አይሰራም ቢሰራም ቶሎ አይገባም ቢገባም ቶሎ አይተኛም … ቢተኛም….” እያሉ መስከር ያለውን ጦስ በቀልድም በዋዛም ይነግሯቸዋል። እራሳቸው ግን ማንም ምንም እንዲናገራቸው አይወዱም። ስለዚህ ህፃናትን ያሳድዳሉ ሲያገኙም ይደበድባሉ። መንግስታችን እና ጋሽ ግዛው አንድ ናቸው። ቀላል ማስረጃ ይህው እነ እስክንድር የታሰሩት እነ ዳዊት ከበደ እና መስፍን ነጋሽ የተሰደዱት “ሰካራም ቤት አይሰራም ቢሰራም ቶሎ አይገባም” ብለው ትችት ስላቀረቡ አይደለምን!?
ሶስት
ዋና የጋሽ ግዝሽ መገለጫ መጣችላችሁ፤ “እኔ ግዛው ቀብራራ እኮ ነኝ አሁን ይሄንን ገብቼ ዘለዝልና  ከዚህ እዛ ድረስ ክሪስመርስ ነው ያማስመስለው” ብለው በጋዜጣ የተጠቀለለች ቅንጥብጣቢ ስጋ ለመንገደኛው በሙሉ ያሳያሉ። እውነቴን ነው የምልዎ ቅንጥብጣቢዋ እቤት ሳትገባ መንገድ ላይ ተበትና የምትቀርበት ግዜ ይበዛል። አንዳንዴ በሰላም እቤት ከገባች ደግሞ ለነገም መፎከሪያ ስለምትሆን ተጠቅልላ ትቀመጣለች እንጂ አትበላም። ብለው የሚያሟቸው ብዙ ናቸው። ታድያ እዝችጋ መንግስታችን ትዝ አላላችሁም…? ይሄ እኮ “መልካም ገፅታ ግንባታ” ነው። (ነውንዴ በዚህማ መንግስታችን ከጋሽ ግዛውም ይበልጣል! ሳይሉ አይቀሩም ብዬ ልጠርጥር?)
አራት
ጎረቤት ወይም ሌላ አሳቢ ሰው “ለምን ይሰክራሉ?” ብሎ የጠየቃቸው እንደሆነ፤ አሁን ትልቅ ፀብ ተነሳ! ከመንግስት ቋንቋ እንዋስላቸው “ይሄ የውስጥ ጉዳያችን ነው ከጣማችሁ ተቀበሉ ካልጣማችሁ በሊማሊሞ በኩል አቋርጡ!” ይላሉ። ታድያስ መንግስታችንስ ማንን ሲሰማ አይተው ያወቃሉ? (ቻይናን… ብለው እንዳያላግጡ ብቻ!)
በጥቅሉ
መንግስታችንም ሆነ ጋሽ ግዛው ሞቅታ ውስጥ መሆናቸው ጥርጥር የለውም። እናም ደገፍ ደግገፍ ካላደረግናቸው በቀር ክፉኛ አወዳደቅ እንዳይወድቁ ያሰጋል። ትልቁ ችግር ግን ጋሽ ግዛውም ሆኑ መንግስታችን እንደግፋችሁ ብለው የቀረቧቸውን ሁሉ እንደሌባ ነው የሚቆጥሩት…? እናም ማንንም አያስጠጉም ታድያ ብዙ ግዜ ክፉኛ አወዳደቅ ይወድቃሉ።
ቀጥሎ መንግስቴን እመክራለሁ። (ይህ ምክር እንደ አቋም መግለጫም ይታይልኝ!)
ማንም የተቃወመ ቢመስል ቅሉ ለሀገር እና ለመንግስቱ ልስራ ላገልግል ያለ ነው። መንግስቴ ሆይ እሺ በል “ተቃዋሚ” “አሸባሪ” “ነውጠኛ” ያልካቸው በሙሉ እንደግፍህ እያሉ እንደሆነ ምን ታውቃለህ…? በእውኑ ብቻህን እየተንገዳገድክ አይወድቁ አወዳደቅ ከምትወድቅ ደግፉኝ አግዙኝ ማለት የአባት ነውና ዛሬውኑ እንደግፍ ስላሉ የታሰሩት ይፈቱ! “ሞቅታ ይብቃ” ብለው የሚመክሩትም ይሰሙ!

የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ረገጣ እና እስራት በአስቸኳይ ያቁም!


በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባቱን እና ዜጎችን ማፈናቀሉን ያቁም!!
በብራሰልስ ከኢትዮጵያዊያን የተቃውሞ ሰልፍ አዘጋጅ ድርጅቶች የተሰጠ መግለጫ
ሜይ 03፣ 2012
ብራሰልስ፣ ቤልጀም
አገራችን ኢትዮጵያ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ጎዳና መከተሏ፣ የህግ የበላይነት ስለመረጋገጡ እና የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበራቸው እየተደሰኮረልን ሁለት አስርት አመታትን አስቆጥረናል። ይሁንና በእነዚህ ሁለት አሥርት ዓመታት ዉስጥ ያየነው እና እያየንም ያለነው እውነታ ከዚህ የመንግስት ፕሮፓጋንዳ ተገላቢጦሽ ነው። አገሪቱ የምትገኝበት ሁኔታ የዲሞክራሲ እምርታ ይቅርና ጭላንጭሉንም አይታለች ለማለት የሚያስደፍር አይደለም። ከፓርቲ አንባገነንነት አልፎ የግለሰቦች ወይም የጥቂት ቡድኖች አንባገነናዊነት እውን የሆነባት አገር ከሆነች ዉሎ አድሯል። መንግስት ራሱ ያጸደቀውን ህገ-መንግስት ሳይቀር በመጣስ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊያን ላይ እያደረገ ያለውን ግፍ አጠናክሮ ቀጥሎበታል። በዚያው መጠን የህዝብ እሮሮ፣ ስቃይና መከራ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በኢትዮጵያ ሰፊ ህዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት እየመነመነ መጥቶ እርቃኑን የቀረው ስርዓት አሁንም ለህዝቦች ፍላጎት ጆሮ በመስጠትና የአገሪቱን አጠቃላይ ደህንነት ከግምት በማስገባት ድርጊቱን ከማሻሻል ይልቅ አፈናዉን አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚህም የተነሳ፦
  • የ 1997 አገር አቀፍ ምርጫ ዋዜማ ላይ በተወሰነ ደረጃ ታይቶ የነበረው የዴሞክራሲ ጭላንጭል ሙሉ በሙሉ ከተዳፈነ በኋላ ገዢው ፓርቲ የስልጣኔ ተቀናቃኝ ናቸው በማለት የፈረጃቸውን በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሀን ዜጎች በእስር ቤቶቹ አጉሮ ይገኛል፤ አሁንም እያጎረ ነው። እነዚህ በየማጎሪያ ቤቶቹ የሚገኙት የፓለቲካ እስረኞች ቁጥር በእጅጉ ከመጨመሩም በላይ ታስረው በሚገኙበት ቦታ የሚፈጸመው እንግልት እና ስቃይ ተባብሷል፤
  • ስርዓቱ በህዝብና በአገር ላይ እያደረሰ ያለው ጥፋትና ውድመት ለሰሚ ጆሮ እንዳይደርስ እና አለማቀፋዊ ትኩረት እንዳያገኝ፤ እንዲሁም የአፈና ስራው ይሰምር ዘንድ የህዝብ የመረጃ ምንጭ የሆኑትን የግል ሚዲያዎች ህልውና እያዳከመ ይገኛል፤ ጋዜጠኞች ለእስር እና ለስደት ተዳርገዋል፤ ጋዜጦች ከሕትመት ውጭ ሆነዋል፤
  • የህዝብ ንብረት የሆኑ የመገናኛ አውታሮች (ቲቪ፣ ሬድዮ፣ ስልክ፣ …) ህብረተሰቡን ማገልገል ሲገባቸው የስርዓቱ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ከመሆን አልፈው ህዝብን የማፈኛ፣ የማሸበሪያ እና የመሰለያ አካል ሆነዋል፤
  • ኢትዮጵያዊያን ተወልደው ካደጉበትና ከሚኖሩበት ቀየ እየተነሱ መሬታቸው ለውጭ ዜጎች እና ለስርዓቱ ታማኝ ናቸው ለሚባሉ ግለሰቦች በሀራጅ እየተቸበቸበ ይገኛል፤ በዚህም በአፋር፣ በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል፣ በሶማሌ፣ በደቡብ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎች በርካታ የአገሪቱ ክፍሎች ኢትዮጵያዊያን ይህ ነው ለማይባል ስቃይና እንግልት ተዳርገዋል፤
  • ለዘመናት ተቻችሎና ተከባብሮ የኖረውን ህዝባችንን በእምነቶቹ ጣልቃ በመግባት እርስ በርሱ እንዲተላለቅ የሚያደርጉ ስራዎች ከመንግዜውም በላይ ተጠናክረው ቀጥለዋል፤
  • በሙስሊሙ ህብረተሰብ እምነት ጣልቃ በመግባትና “አህባሽ” የተባለ የአምልኮ አስተሳስብ በህዝቡ ላይ በሀይል ለመጫን እየተንቀሳቀሰ ነው፤ ይህን የተቃወሙ ሙስሊሞች ለእስራት ብቻ ሳይሆን በአገዛዝ ስርዓቱ ታጣቂዎች በግፍ ደማቸው እየፈሰሰ ይገኛል፤
  •  የአገርና የእምነት ቅርሶች ህልውናቸው እንዲያከስም እየተደረገ ነው። በታሪካዊነቱና በጥንታዊነቱ ታዋቂ የሆነው የዋልድባ ገዳም የዚህ አገርን እና ህዝብን በማጥፋት ስራ ላይ የተሰማራ መንግስት ሰለባ ሆኗል፤
  • በአለም አቀፍ ደረጃ የተወገዘ የሽብርተኝነት ህግ (Anti-Terrorism Law) በማውጣት ዜጎች ዘወትር መግስትን ፈርተውና ተሸማቀው እንዲኖሩ ተደርገዋል፤ ብሶቶቻቸውን ከመግለጽ መቆጠብ ብቸኛ አማራጫቸው ሆኗል። የሕዝብን ብሶት ሲያሰሙና የመንግስትን ፖሊሲዎችና አተገባበራቸውን ሲተቹ የነበሩ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ፓርቲ አባላትም በዚሁ ሕግ እንደ ሽብርተኛ ተቆጥረው ለወንጀል ክስ እና እስራት ተዳርገዋል። ገሚሶቹም ከአስር አመት በላይ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ይገኛሉ፤
  • የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ህግን (Civil Society and Charity Proclamation) በማውጣት ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው ውስጥ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ፣ በሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ፣ እንዲሁም መብትን መሰረት ባደረጉ የልማት ሥራዎች ላይ ለመሰማራት እንዳይችሉ እና በነጻ የመደራጀትና ተደራጅተውም የመንቀሳቀስ መብታቸውን ነፍጓቸዋል፤
  • ዜጎች በየትኛውም የአገሪቱ ክፍሎች ተዘዋውረው ሕጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የመኖርና ህይወታቸውንም የመምራት መብታቸውን ተነፍገዋል። በቅርቡ ከደቡብ ክልል በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵዊያን በተደረገባቸው የማፈናቀል ዘመቻ በገዛ አገራቸው ውስጥ ስደተኛ ሆነዋል፤
  • መንግስት በሚከተለው የተሳሳተ የኢኮኖሚ ፓሊሲ ሳቢያ ህዝባችን ለኑሮ ዋስትና ማጣት ተዳርጎ ጥቂቶች በንዋይ ውቅያኖስ ውስጥ ሲዋኙ ሰፊው ህዝብ ግን ወደተመጽዋችነት ደረጃ እየወረደ ይገኛል፤
  • ሕጋዊ በሆነ መንገድ የመብት ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ብቻ መምህራን ከሥራ ገበታቸው ተባረዋል። መንግስት የመምህራኑን አስተዳደራዊ ጥያቄዎች ተቀብሎ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ሲገባው በመምህራኑ ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ በመሰንዘር ጥያቄያቸውን አፍኗል፤
  • የሰራተኞች እና የሙያ ማህበራትን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድርጅቶቹን የኢሕአዴግ ካድሬዎች መፈንጫ እንድሆኑ ወይም ተለጣፊ በማበጀት ሕዝቡን እንዲያደናግሩ ተደርጓል፤
  • በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በነጻነት የመደራጀት፣ የመሰብሰብ፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ መንግስትን በሰላማዊ ሰልፍ የመቃወም እና ሌሎች መሰረታዊ መብቶች ታፍነዋል።
እነዚህን እና መሰል ግፎችን ኢትዮጵያዊያን አቅማቸዉ በፈቀደ ሁሉ እየታገሉ ይገኛሉ። ለቀሪው ወገንም የድረሱልን ጥሪያቸውን እያሰሙ ነው። ይህን እያየና እየሰማ አርፎ የሚቀመጥ ህሊና ሊኖረን አይችልም። በኢሕአዴግ መሪነት በአገራችን እና በህዝባችን ላይ እየተደረገ ያለውን የመብት ጥሰት፣ አገርን እና ህዝብን የማጥፋት ዘመቻዉ ሊያበቃ ይገባዋል። ግፉንም ሰላም ወዳድ ለሆነው የአለም ህዝብና መንግስታት ማሳወቅ ይገባናል። በዚህም መሰረት የአገዛዝ ስርአቱ መልካም እየሰራ እየመሰላቸው በገንዘብም ሆነ በዲፕሎማሲ ድጋፍ ለሚያደርጉለት መንግስታት አገሪቱ የምትገኝበትን አሳሳቢ ሁኔታ ለማስረዳት ሜይ 16፣ 2012 በብራሰልስ ቤልጀም የተቃውሞ ሰልፍ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ከቤልጀም ብቻ ሳይሆን ከአውሮፓ የተለያዩ አገሮችና ከተሞች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ይሳተፉበታል ተብሎ በሚጠበቀው ሰልፍ ላይ መንግስት ከላይ በዘረዘርናቸውና በሌላም መልኩ በህዝባችን ላይ የሚያደርሰውን የመብት ረገጣ በአፋጣኝ እንዲያቆም ይጠየቃል። የአውሮፓ መንግስታትም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጡና ራሳቸውን አምባገነናዊ ከሆነው የኢሕአዴግ መንግስት በመነጠል አጋርነታቸውን የጭቆና ቀንበር ከተጫነበት ሰፊዉ ህዝብ ጋር እንዲያደርጉ ጥሪ ይደረግላቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ሰልፉ የኢትዮጵያ ህዝብ ስርዓቱ ካዘጋጀለት የሀይማኖት፣ የጉሳና የዘር መከፋፈያ ወጥመድ ዉስጥ ሳይገባ በአንድነት በመነሳት አገሩንና ራሱን እንዲታደግ ጥሪ የሚቀርብበት፤ ለዲሞክራሲ፣ ለፍትህና ለህግ የበላይነት የሚደረገውን ትግል በመደገፍም አጋርነታችንን የምንገልጽበት ይሆናል። በሁሉም ቦታና በሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች፣ በሁሉም የእምነት ተቋማትና ምዕመናን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ህገወጥ ድርጊትና ጣልቃገብነት እንዲያቆም ድምጻችንን የምናሰማበትም ነው።
ስለሆነም በዚህ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ መገኘት የሚችሉ ሁሉ ሜይ 16፣ 2012 ከቀኑ 13፡00 ሰዓት ጀምሮ በብራስልስ የአውሮፓ ኮሚሺን ህንጻ ፊት ለፊት በመገኘት ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በአሁኑ ወቅትም በተለይ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የተጀመረውን የመብታችን ይከበር ጥያቄ በመደገፍና የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መብት ይከበር ዘንድ በያለንበት እንንቀሳቀስ የሚል መልክታችንን እናስተላልፋለን። ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ።
የሰልፉ አስተባባሪ ድርጅቶች፦

ጸረ አማራነት አንድ ቀን ጸረ ህዝብነት ይሆናል!

ገረመው አራጋው | May 11th, 2012 at 1:04 am | |
ገረመው አራጋው
የጎሳ ግጭትና እልቂት ዛሬ ዛሬ ጆሮአችን እንዲያም ሲል አይናችን እየለመደ መጣና እንደሌላው ጊዜ ብዙም የሚሰቀጥጥና የሚያስፈራ ወሬ አይደለም ዛሬ ካለንበት ጊዜ ላይ የደረስነው ባለፉት አያ አመታት በተለያይ የአገራችን ክፍሎች የብሄር ግጭትና የዜጎች ከመኖሪያ ቦታቸው መፈናቀል እየሰማንና እያየን ነው የመከራ ጊዜ እረጅም ነው ይባላል ግን ደግሞ ከዚያም በላይ ሃያ አመት አጭር ጊዜ አይደለም የኢትዮያ ህዝብ ከሞትና ከእቂት ከስደትና ክፍረሃት ጋር መኖሩን በግድ እየተለማመድን ነው ማለት ይቻላል ዛሬ በሀገራችን ላይ ሌላው ቀርቶ ለሰልፍ የወጣና ለምርጫ የተነሳን ህዝብ በጥይት ማስፈራራት ማሰር መደብደብ ማሰቃየትና መግደል  አዲስ ነገር አይደለም ሞትንና እልቂትን ሁሉም ከልጅ እስከ አዋቂ እየቀመሰ ነው::
ብዙ ሰው እንዲሁ በተለምዶና  ለአፍ ብቻ ካልሆነ በስተቀር ዛሬ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚነሱትን  ግጭቶችና  ግድያዎችን ማን እንደፈጠረውና እንዳቀነባበረው መጠየቁን  ትታል የትም ይሁን የት በጎሳዎች መካከል የሚቀጣጠለው ሁከትና ግጭት በእነማን ፍላጎትና  ግፊት እንደሚካሄድ ህዝቡ ጠንቅቆ ያውቀዋል በስልጠን ላይ ያለው አምባገነን የወያኔ ስርዓት ጫካ ገባሁ ሲል ጀምሮ ትግሌ ጸረ ኢትዮጵያና ጸረ አማራ ነው ካለ ከዘረኛ ቡድን ሌላ ባይጠበቅም አምባገነኑ የመለስ ስርአት የአማራውን ህዝብ  ለማጥፋት ገና ከደደቢት የጀመረውን ዘመቻ ቀስ በቀስ እየፈፅመና እያስፈፅመ መሆኑን ፅሀይ የሞቀው ሀቅ ከሆነ ሰነበተ::
ወያኔ ወደስልጣን  በጠመንጃ ሀይል ከመጣ ጀምሮ የአማራን ህዝብ ማንነትና ታሪኩን ለማጥፋት የላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቶአል አሁንም አጠናክሮ ቀጥሎበታል ለምሳሌ ወያኔ ወደስልጣን ከመጣ ጊዜ ጀምሮ በአማራው ህዝብ ላይ የተፈጸሙት ወንጀሎች;
አማራው ህዝብ ለብዙ ዘመናት ያስተዳድራቸው የነበሩትን  የጎንደርንና የወሎን ሰፋፊና ለም  መሬቶችን ወደፊት ታላቅዋን  ትግራይ ለመመስረት   ወደ እራሱ ግዛት ያጠቃለለው ወያኔ የአማራውን ህዝብ ከለም መሬቱ አፈናቅሎ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ጥገኛ እንዲሆኑ እንዲራቡ  እንዲሰደዱም አድርጎአል ይህ በዚህ ሳያንሰው ማንም የክልሉ ነዋሪ ሳያውቅና ሳይሰማ  የአማራን መሬት ለሱዳን አስረካቦል የአካባቢው ነዋሪዎች በባእድና በወያኔ ወታደሮች አስጨፍጭፋል::
በአማራው ላይ ጥቃት የተጀመረው ዛሬ ሳይሆን ከፋሽስት ኢጠሊያ ወርራ ግዜ ጀምሮ እንደነበር ታሪክ ይመሰክራል ይህንንም የባንዳነት ተግባር ወያኔ ጠመንጃ ካነሳ ጊዜ ጀምሮ በትግል ወቅትም ሆነ መንግስት ከሆነ በሃላ በግልጽና በስውር ከአፍራሽ የትግል አጋሮቹ ጋር በመሆን አያሌ ጥቃቶችን በዚህ ህዝብ ላይ ሲያካሂዱበት እንደነበር  የትናንት ትዝታችን ነው   ሆን ተብሎና በተቀነባበረ መልኩ በአርባጉጉ በምስራቅ ወለጋ በበደኖ በአረካ ወዘተ አያሌ አማሮችን ጨፍጭፋል አስጨፍጭፋል እንዚህም  የዘር ማጥፋት ድርጊቶች ክተፈጸሙ በሁዋላ የወያኔ መንግስት እንድም ግለሰብ ለፍርድ አለማቅረቡ እራሱ ወያኔ የድርጊቱ ዋነኛ ተዋናይ እንደነበረ ያረጋግጣል::
ዘሩና ታሪኩ እንዲጠፋ በወያኔ የተወሰነበት የአማራው ህዝብ እንደ ወያኔ የኢትዮጵያ ጠላት አባባል በራሱና በታሪኩ የሚተማመን አትንኩኝ ባይ ለነጻነቱ ለህልውናው ለህይማኖቱና ለሀገሩ ዳርድንበር ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ማች በመሆኑ ነው ለማያባራ ጥቃት የተዳረገው ወያኔ ወደ ሰልጠን ከመጠበት ጊዜ ጀምሮ አማራውን ነፍጠኛ በማለት ከሌላው ጎሳ ጋር ተፋቅሮ ተጋቤቶ ተዋልዶና ተዋህዶ ከኖረበት ቀየው በግፍ ሲያባርሩት እንደነበር ከሞት የተረፉት ተፈናቃዮች ምስክር ናቸው በተለይ በሽግግሩ ዘመን በአማራው ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ታሪክ ምን ግዜም ሲያስታውሰው ይኖራል ::
በጣም የሚገርመው በአንድ ወቅት አምባገነኑ መለስ የአማራውን ህዝብ እንዳያንሰራራ አድርገን አዳክመነዋል እስክታውንና ተረቱን ይዞ ይኑር ማለቱ አይዘነጋም ይህንኑ የአለቃቸውን ቃል እንደየገደል ማሚቱ  የሚያስትጋቡ አንድ  የወያኔ ጀነራልና  ጦር መሪ የሆኑት ግለሰብ በአንድ  ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር  በታጋዮች የህይወት መስዋትነት በተከፈለ አካላቸውን ባጡ በትግራይ ልጆች ደም እኮ ነው ደርግን ከፍተኛ መሰዋትነት ከፍለን ከስልጣኑ አውርደነዋል አማራውንም ደግሞ እንዳያንሰራራ አድርገን አጥፍተነዋል ማለታቸውን እናስታውሳለን::
የወያኔ ድበቅ አጀንዳ አሁን ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ በተለይ በቤንች ማጂ ዞን በጉራ ፈርዳ ወረዳ እራሱ ባወጣው ህገ መንግስት ውስጥ ዜጎች በፈለጉት ክልል የመኖርና ሀብት የማፍራት መብታቸውን በመጣስ  እጅግ ቁጥራቸው የበዛ የአማራ ብሄር ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመ ይገኛል በደሉን እያስፈጸመ ያለው የአምባገነኑ የመለስ ሰርዓት በሚሰጠው መመሪያና ትህዛዝ ከክልሉ መስተዳድር ጀምሮ እስከ ወረዳ ባሉ ተላላኪዎቹ በተቀናጀ አሰራር ነው ከማፈናቀሉ ተግባር ጋር በተያያዘ የወቅቱ ትልቅ ጥያቄ የደቡብ ክልል አስተዳደር ቀደም ሲል ሆነ አሁን በተለይ የአማራ ብሐር ተወላጆችን ለበርካታ አመታት ከኖሩበት እያፈናቀለና ወደመጡበት እየመለሰ ያለው ለምንድ ነው? ለአማራ ህዝብ መብትና ጥቅም የቆምኩነኝ የሚለው አሻንጉሊቱ ብአዴንስ የክልሉ ዜጎች መፈናቀልን በመደገፍ በዝምታ የተቀበለው ለምንድን ነው?
አማራውን ከፌደራል መንግስት ስልጣን የማራቁ  ድብቅ ተልኮ ወያኔ ስልጠን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ሲያከናውነው የነበረ ረቂቁ ሴራ ለማሳካት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም ነገር ግን ሊሳካለት አልቻለም  ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ትልቅ የህዝብ ብዛት ያላቸውን አማራንና ኦሮሞን ህዝቦች በማጋጨት እድሜአቸውን ለማርዘም ያሴሩት ሴራ ሲከሽፍባቸው ዛሬ ደግሞ ተጋብቶ ተዋልዶ ተከባብሮና ተስማምቶ በሰላም የሚኖረውን የደቡብ ኢትዮጵያ ነዋሪዎችን ሰላም በማደፍረስ ወቅታዊውን የመምህራን ጥያቄ :የህዝብ የኑሮ ውድነት: የሰባዊና ዲሞክራሲያዊ መብት መከበር ጥያቄ አቅጠጫ ለማስቀየር የተጠቀመበት እኩይ ተግባር መሆኑን  የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቀዋል::
በአማራ ህዝብ ላይ ጥላቻን መሰረት አድርገው በመካሄድ ላይ ያሉ ማንነቱንና ታሪኩን የማጥፋት ዘመቻ በአሁኑ ወቅት በጣም ተባብሰው ቀጥለዋል አማራው እንደ ህዝብ እስከ ዛሬ በኢትዮጵያ ላይ ጭቆናና መከራ ሁሉ ተጠያቂ ተብሎ ሲወገዝ ቆይታል ገዝው ሁሉ አማራ ተባለ እንጂ ፓለቲካቸው ለሰፊው የአማራ ህዝብ የፈየደው ብዙ አልነበረም የአማራ ህዝብ ሰፊ ነው በኢትዮጵያነቱ አምኖ ከሌሎች ብሄሮች ጋር በመሆን ታሪክ የሰራም ህዝብ ነው አምባገነኑ የመንግስት ስርዓት ይህንን እውነታ ወደጎን  በመተው የአማራን ህዝብ ማስጨፍና ማፈናቀልን ለጥቃት  ማጋለጡን ቀጥሎበታል ብዙሃኑ የአማራ ህዝብ  በማያወላዳ መልኩ ለአገር አንድነት የቆመ ነው ይህ የኢትዮጵያዊነት ስሜቱ እንደ ሀጥያትና ወንጀል ተቆጥሮበት ከተወገዘ ደግሞ እራሱን ለማዳንና መከላከል የግድ ይሆንበታል አማራን ያህል ሰፊ ህዝብ አግልሎና አውግዞ ልማት አካሂዳለው ማለት ዘበት መሆኑን አምባገነኑ የመለስ ስርአት ጠንቅቆ እንዲያውቀው ይገባል::

አጠፋፉን አይደል .......በ ??????????? ተጻፈ


Thursday 10 May 2012

ነፍሰ-ጡሯ ለመገላገል ወደ ሆስፒቷል ሲሄዱ በዘራፊዎች ተደብድበው ህይወታቸው አለፈ…ፍኖተ ነጻነት



ልዩ ቦታው ላፈቶ ኮንዶሚኒየም አካባቢ ነዋሪ የሆኑት / ምስራቅ አክመል ሚያዚያ 17 ቀን 2ዐዐ4 . ከሌሊቱ 73 ሰዓት ላይ ምጥ ይዟቸው ከባለቤታቸው ጋር ሲሄዱ ጎፋ ገብርኤል አደባባይ አካባቢ በዘራፊዎች ተደብድበው ህይወታቸው ማለፉ ተገለፀ፡፡ / ምስራቅ እና ባለቤታቸው አቶ ታሪኩ ጉዲሳ ላዳ ታክሲ ተኮናትረው ሜክሲኮ በሚገኘው ላንድማርክ ሆስፒቷል እየሄዱ ሳለ
ባለታክሲው በድንገት ጎፋ ገብርኤል አደባባይ አካባቢ በድንገት እዚህ ውረዱ ብሎ ካወረዳቸው በኋላ ሁለት ያልታወቁ ሰዎች ወዲያውኑ መጥተው በእጃቸው ያለውን ንብረት መዝረፋቸው ተጠቁሟል፡፡ በወቅቱም ዘራፊዎቹ ያላችሁን ሁሉ አምጡ እያሉ
ሲደበድቡ ነፈሰጡሯ ለመጮህ ሲሞክሩ በኃይል ከጀርባቸው እንደገፈተሯቸውና ወደፊት በሆዳቸው በመውደቃቸው አንድ ድምጽ ካሰሙ በኋላ ፀጥ እንዳሉ ባለቤታቸው አቶ ታሪኩ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም እኔ ነቅቼ እየጮህኩ የድረሱልን የእርዳታ ጥሪ ሳሰማ በአካባቢው ያሉ መኪና ጠባቂዎች ደርሰው ታክሲ ፈልገው እንዳመጡላቸውና ወዲያው ላንድማርክ ሆስፒታል ሲሄዱ ባለቤታቸው ህይወታቸው አልፎ እንደነበር ከዶክተሮቹ መስማታቸውን አቶ ታሪኩ ይናገራሉ፡፡ በስፍራው ጎፋ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቢኖርም ፖሊሶቹ ግን መኪና ላይ ተኝተው መገኘታቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለው ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ክፍል እንደሚገኙ

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስልጠና ባልጨረሱ ፖሊሶች ተደበደቡ


-በጥይትና በከባድ ድብደባ የተጎዱ ተማሪዎች ህክምና ላይ ናቸው
-የከተማው ነዋሪም ተቃውሞውን ተቀላቅሏል

ትላንት ለተቃውሞ በወጡ የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ታጣቂዎች በጥይትና በዱላ ጉዳት ማድረሳቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ ከትላንት በስቲያ እሁድ ሚያዝያ 28 እና ትላንት ሰኞ ሚያዝያ 29 በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ሊከሰት የቻለው ተማሪዎች ተጓደለ ያሉትን የምግብ ጥራት በመቃወማቸው እንደሆነ ምንጮቻችን ዘግበዋል፡፡ እሁድ
ሚያዝያ 28 ከቀኑ 1030 ጀምሮ በተቀጣጠለው በዚህ ተቃውሞ አብዛኛው ተማሪ ቁጣውን የዩኒቨርስቲውን መስታወቶች በመሰባበር እንደገለፀ የሚናገሩት ምንጮቻችን ምሽት ላይ በድንገት ወደ ግቢው የገቡት ታጣቂዎች ተማሪዎቹ ላይ ከመጠን ያለፈ ኃይል በመጠቀም ጉዳት እንዳደረሱ ገልፀዋል፡፡ በወቅቱ በታጣቂዎች በተወሰደው እርምጃ 60 ያላነሱ ተማሪዎች መታሰራቸውና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች ላይ ድብደባ እንደተካሄደ ታውቋል፡፡ በወቅቱ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ የተሰማ ሲሆን ኢብራሂም መሀመድ የተባለ 2 አመት የማኔጅመንት ተማሪ በጥይት መመታቱ ታውቋል፡፡ ተማሪው በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ በመከታተል ላይ እንደሚገኝ ፍኖተ ነፃነት ስፍራው ድረስ በመደወል አረጋግጣለች፡፡

ተማሪ ኢብራሂም መሃመድ በስልክ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፀው ከትላንት በስቲያ ምሽት ታጣቂዎቹ በቀጥታ በጥይት እግሩ ላይ መተው አቁስለውታል፡፡ ሌላው በታጣቂዎች ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመበት 2 አመት የማኔጅመንት ተማሪ የሆነውና ከትግራይ ክልል የመጣው ገብረ ኪዳን ብርሃኔ ትላንት ጠዋት በጀርባውና በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቹ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ለዝግጅት ክፍሉ ተናግሯል፡፡

በትላንትናው እለት ከጠዋቱ 230 ጀምሮ ‹‹የታሰሩ ተማሪዎች ይፈቱ›› የሚል ጥያቄን ይዞ የቀጠለው ተቃውሞ ቀስ በቀስ ከዩኒቨርሲቲው ውጪ መስፋፋቱን ከከተማው ያገኘናቸው መረጃዎች አመላክተዋል፡፡ ተቃውሞው በደብረ ማርቆስ ከተማ ጎዳናዎች ላይ በቀጠለበት ወቅት በርካታ የከተማው ነዋሪዎችም ትዕይንቱን ተቀላቅለው ጥያቄው ፖለቲካዊ ይዘት ተላብሶ ገዢውን ፓርቲ በማውገዝ እና ለኑሮ ውድነቱ ገዢውን ፓርቲ መኮነናቸውን ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎም ታጣቂቆች ቶክስ በመክፈታቸው ተቃውሞው ተበትኗል ሲሉ ምንጮቻችን ዘግበዋል፡፡ በሁኔታው የተደናገጡት ተማሪዎች ወደ ተለያየ አቅጣጫ ሲበታተኑ ታጣቂዎችና ፖሊሶች አብዛኞቹን እያፈሱ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዳጓጓዟቸው የከተማው ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች ወደ ህትመት እስከገባንበት ጊዜ ድረስ አፈሳው እንደቀጠለ ተናግረዋል፡፡ ጨምረውም በድብደባዉ ከተጎዱ ተማሪዎች መካከል አይናቸዉ ተመትቶ ኡፕራሲዮን የተደረጉ እንደሚገኙበት አስረድተዋል፡፡ ከስፍራው የደረስን መረጃ እንደሚያመለክተው በተማሪዎቹ ላይ እርምጃ የተወሰደው ስልጠናቸውን ባልጨረሱ ፖሊሶች ጭምር መሆኑን ያመለክታል፡፡ ማምሻውን የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ትገኛለች፡፡ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

 በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ለማግኘት ወደ ዩኒቨርሲቲውና ወደ ደብረማርቆስ ሆስፒታል ደውለን ምላሽወደ ህትመት እስከገባንበት ሰአት ድረስ ምላሽ ማግኘት አልቻልንም፡፡