Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 18 August 2012

ብአዴን እየታመሰ ነው

ነሀሴ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የብአዴን አባል የሆኑ ታማኝ የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ሰሞኑን የብአዴን የኮር አባላት ለሁለተኛ ጊዜ በአቶ በረከት መሪነት በባህርዳር ከተማ ስብሰባ አድርገዋል።

የአማራ ክልል የወጣቶች ፕሬዚዳንት የሆነው ወጣት ዘመነ ካሴ ከአገር መውጣቱና ለኢሳት  ቃለምልልስ መስጠቱ፣  በክልሉ የተነሳው የሙስሊሞች እንቅስቃሴ ከአቶ መለስ ዜናዊ የጤንነት ሁኔታ ጋር ተደማምሮ በብአዴን የኮር አባላት ላይ ከፍተኛ ፍርሀት እና አለመረጋጋት መፍጠሩ የስብሰባው ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ነበሩ።

የብአዴን ዋና ዋና አመራሮች በተገኙበት የኮር አባላቱ ያሳለፍነውን ጉዞ እንገምግም፣ ለወደፊቱም የማስተካከያ እርምጃ እንውሰድ የሚል ሀሳብ ሰንዝረዋል። የወጣት ዘመነ ካሴ ከአገር መውጣት ብአዴን በወጣቱ ዙሪያ በቂ ስራ አለመስራቱን፣ የክልሉ ወጣት ልብ ከድርጅቱ ጋር ሳይሆን ከጸረ ሰላም ሀይሎች ጋር መሆኑን ያመለካተ በመሆኑ ድርጅቱ፣ የወጣቱን ልብ መልሶ ለመያዝ መንቀሳቀስ እንዳለበት አባላቱ መተማመን ላይ ደርሰዋል። 

የደህንነት ሹሙ አቶ አቶ ጌታቸው አሰፋ “የጠቅላይ ሚኒስትሩን ህመም ተከትሎ ጎንበስ ቀና ማለቱ ያስተዛዝባል” አሉ

ነሀሴ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኢሳት የብሄራዊ የመረጃ እና የደህንነት ምንጭ እንደገለጠው የደህንነት ዋና ሹሙ አቶ ጌታቸው አሰፋ ሰሞኑን ዋና ዋና የሚባሉ የኢሚግሬሽንና የውጭ መረጃ ሰራተኞችን እና በተለያዩ ተቋማት የተመደቡ የደህንነት አባላትን ሰብስበው በአቶ መለስ ዜናዊ የደህንነት ሁኔታ ላይ ገለጻ ሰጥተዋል።
ከስብሰባው በፊት በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ለሚገኙት የደህንነት አባላትና የመንግስት ባለስልጣናት ” የጠቅላይ ሚኒስትሩን ህመም ተከትሎ ጎንበስ ቀና ማለቱ ያስተዛዝባል” በሚል ርእስ  ባለሁለት ገጽ ደብዳቤ ጽፈው አሰራጭተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ጌታቸው በደብዳቤያቸው ” አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት መኖራቸውን፣ እንደማንኛውም ሰው መታመማቸውን፣ እንደማንኛውም ሰው እረፍት እንዳስፈልጋቸው እና በሀኪማቸው ምክር ከስራ እንደተገለሉ፣ ከዚህ ውጭ የሚናፈሰው ወሬ ትክክል እንዳልሆነ ፣ ህክምናቸውንም በአውሮፓ ውስጥ በጥሩ ሁኔታ እየተከታተሉ መሆኑን” ገልጠዋል።

የነበረከት ስምኦን አንጃ በአቦይ ስብሃት ላይ የሃያ አራት ሰአት ክትትል እንዲደረግባቸው ለደህንነት መመሪያ ሰጠ






ከቅርብ ግዜ ወዲህ በባህሪያቸው የማን አለብኝነትን ባህሪ እያሳዩ የመጡትን አቦይ ስብሃትን የማያቋርጥ ክትትል እንዲደረግባቸው እና ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ በበረከት ስሞን ከሚመራው አንጃ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው የውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልጠውልናል።
 
ይህንን በማያያዝም አቦይ ስብሃት ነጋን ያሞጋግሱ የነበሩ ማናቸውም አይነት ጽሁፎችም ሆኑ ቃለመጠይቆች የህውሓት አቀንቃኝና ደጋፊ ከሆኑ ድህረ ገጾች ለይ ተለቅመው እንዲነሱም መመሪያ ተሰጥቷል።

Friday 17 August 2012

ጄነራል ሳሞራ የኑስ በጠና ታመው ትላንት ምሽት ኢትዮጵያን ለቀቁ


ሳሞራ የኑስ እንደኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1947 ዓ.ም. አክሱም፣ ትግራይ ተወለደ። በአባቱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን፤ እናቱ ኤትራዊ ናት። ሳሞራ የትግል ስሙ ሲሆን፤ ትክክለኛ ስሙ መሃመድ የኑስ ነው። ኢህአዴግ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ኦፕሬሽኑን የመራው ሳሞራ የኑስ ነበር።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ አይታወቅም። ጠቅላይ ሚንስትሩ ይዘውት የነበረውን የጠቅላይ ጦር አዝዥነትን ሚና በማን ኃላፊነት ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግልጽ አልነበረም። ይህንን ክፍተት ለመሙላት ከጠቅላይ ሚንስትሩ ቀጥሎ የጦር አዛዥነቱን ሚና ጄነራል ሳሞራ የኑስ ተክቶ ይሰራል፤ ተብሎ ግምት ሲሰጥ ቢቆይም…አሁን ግን ሳሞራ የኑስም በድንገተኛ ህመም ስራቸውን ያቆሙ መሆኑን ለማወቅ ችለናል። ይልቁንም በትላንትናው ምሽት ህመማቸው ስለጠና፤ ለህክምና ወደውጭ አገር ለቀው ወጥተዋል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ሰራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ ሆኖ፤ አመራሩን ሌ/ጄነራል ሰዓረ መኮንን እና ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ በመስጠት ላይ ናቸው። ከጄነራል ሳሞራ የኑስ ድንገተኛ ህመም በኋላ ሌ/ጄኔራል ፀዓረ በተለይ የትግራው / የህወሃት ጄነራሎች ጋር ስብሰባ ማድረጉንና ሰራዊቱ በተጠንቀቅ ላይ ሆኖ፤ በተለይ በኮሎኔል ደረጃ የሚገኙ የብአዴን ጦር መኮንኖችንን በቅርብ እንዲከታተሉ መመሪያ ተሰጥቷል። በዚህም መሰረት በተለይ የቀድሞ የኢህዴን ታጋይ የነበሩ እና አሁን በብአዴን ውስጥ በጦር አመራር ላይ የሚገኙ መኮንኖች ላይ የስራ ዝውውር እየተደረገ ሲሆን፤ ሌሎች መኮንኖች ደግሞ በተጠንቀቅ ላይ እንዳሉ ግምገማ እየተደረገባቸው ነው።

የአቶ በረከት ስምዖን ሽሙጥ: ከፍቅሬ ዘለቀው፣ ኖርዎይ

በባራክ ኦባማ አስተዳደር ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በደቪድ ካምፕ ዋሽንግቶን የዓለም ምግብ ዋስትናና ፖለቲካ ፈተናዎች በሚል ለተዘጋጀው የግንቦት 18፣ 2012 የቡድን ስምንት (G8- summit) የመሪዎች ጉባኤ አምባገነኑ መለስ ዜናዊ በአለቃቸው ተጋብዘው ለመሳተፍ ከውጪ ይጠብቋቸው የነበረውን የኢትዮጵያንን ቁጣ በጓሮ በር ሸሽተው በመግባት በስብሰባው ላይ ዲስኩር እያሰሙ እያሉ ነበር የመላውን ኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ ባነገበ ጀግናና አለኝታችን አበበ ገላው ቁጣ ቀልባቸው ተገፎ ከዕለቱ ጀምሮ ምናልባትም ለፍፃሜ ህልፈተ-ህይዎታቸው በሽታ ተዳርገው፣ ከአንድ ወር በሗላም በገረጣ ፊትና በከሳ ሰውነት በድጋሜ በሜክሲኮ ዋና ከተማ በኢንዱስትሪ በበለፀጉ አገሮች ስብሰባ ላይ ለመጨረሻ ጊዜ የታዩት።

እስካሁንም የእሳቸው ደብዛ መጥፋት በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ደስታና ስጋት የተቀላቀለበት ስሜት ፈጥሮ መነጋገሪያ የሆነ ቢሆንም፣ የጠቅላይ ሚኒስቴሩ እንዲህ መሆን ደግሞ በአንድ ግለሰብ ለምትመራ አገር ወይም በህገ አራዊት ለምትተዳደር አገር በአፍሪካ ቀንድ አለመረጋጋትን ሊፈጥር ይችላል በሚሉና ሐሳባቸውን በጊዜያዊ ጥቅምና መረጋጋት ላይ ያተኮሩትን የምዕራባዊያን ወዳጆቻቸውንም ስጋት መፍጠሩ አገር በቀል የዜና አውታሮች ብቻ ሳይሆኑ የዓለም አቀፉንም ትኩረት በመሳብ የዕለት ከዕለት መነጋገሪያ ርዕስ በመሆን ላይ ይገኛል። 

ዲፕሎማቶች እየኮበለሉ ነው ተባለ

(Aug. 17) ከአቶ መለስ ዜናዊ መሰወር ጋር ተያይዞ በውጭ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ወደአገር ቤት ቢጠሩም፤ ብዙዎቹ በነበሩበት አገር ወይንም ወደሌላ ሶስተኛ አገር በመኮብለል ጥገኝነት እየጠየቁ እንደሆነ የኢሳት ምንጮች ገለጹ።
በህንድ የወ/ሮ ገነት ዘውዴ ምክትል ሆነው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ደረጀ አስፋው ጄቶ ወደአሜሪካን እንደከዱና በአሜሪካን ጥገኝነት እንደጠየቁ ታማኝ ምንጮች ነግረውናል።
በሌላ ዜናም በካርቱም ዲፕሎማት ሆነው ሲሰሩ የቆዩትና ከዚህ ቀደም በጃፓንና በዱባይ ለረጂም ግዜ አምባሳደር በመሆን ያገለገሉት አቶ ተስፋዬ ደሳለኝም፤ ስራቸውን ለቀው ወደአሜሪካን እንደመጡ ለማወቅ ተችሏል።
ቀደም ሲል በቱርክ ዲፕሎማት የነበሩት አቶ ዮናስ መሀመድ ማይሎ እንዲሁ ወደአሜሪካን ተሰደው፤ በአሜሪካን ጥገኝነት እንዳገኙ ለማወቅ ተችሏል።
ብዙዎች የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በስራቸው ላይ ከመንግስት በሚደርስባቸው ፖለቲካዊ መድልዎና ጫና የተነሳ ስራቸውን እየለቀቁ ጥገኝነት እንደሚጠይቁ ሲናገሩ፤ በተለይ የአቶ መለስ መሰወርን ተከትሎ ወደኢትዮጵያ እንዲመለሱ ትእዛዝ ከተላለፈ በሁዋላ በውጭ አገራት ጥገኝነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያዊያን ዲፕሎማቶች ቁጥር እንዳሻቀበ መረጃዎች ይተቁማሉ።
የጠ/ሚ/ር መለስን መሰወር ተከትሎ በሀገሪቱ የሰፈነው አለመረጋጋት የዲፕሎማቶችን ኩብለላ እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ጨምሮ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶችን እያባባሰ መሆኑን መረጃዎች ያስረዳሉ።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ “መኖር” እናምናለን አምነን ግን እንጠይቃለን! ....ከአቤ ቶክቻው




በቅርቡ አቶ በረከት ስምዖን ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከዛም ቀጥሎ ውጪ ሀገር ለሚገኝ ራዲዮ ጣቢያ ቃለ ምልልስ ሰጥተውም አልነበር! በዛን ወቅቅት የኮሚኒኬሽን ሚኒስቴራችን ደረታቸውን ነፍተው ደምፃቸውን አወፍረው “የአቶ መለስ ጤና ባለፈው ጊዜ ከገለፅኩት በጣም እየተሻሻለ መምጣቱን እና በቅርቡም ወደ ስራቸው እንደሚመለሱ ልነግራችሁ እወዳለሁ!” ብለው ነገረውናል።




ታድያ ውጪ የሚገኘው ጋዜጠኛ አቶ በረከትን አንድ ፈታኝ ጥያቄ ጠይቋቸው ነበር። “አቶ መለስ በህይወት ካሉ ወይ ድምፃቸውን ወይ ደግሞ ምስላቸውን አለማቅረብዎ እንደ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊነትዎ የብልህ እርምጃ ነው ይላሉ?” ብሏቸው ነበር። እርሳቸውም እንደ ማህረቤን ያያችሁ ጨዋታ ዙሪያውን ተሽከርክረው ተሽከርክረው “እኛ ምስል ባናሳይም ድምፅ ባናሰማም ህዝባችን ያምነናል ውጪ ሀገር ያለው ህዝብ ነው የማያምነው እርሱ ደግሞ የራሱ ጉዳይ” ብለዋል።

Thursday 16 August 2012

የአቶ መለስ ጉዳይ ዛሬም አለየለትም

         -“በዚህ የሚጠመዘዝ የዓረና/መድረክ አባል የለም”-አቶ አስገደ /ስላሴ
      -“በህይወት ካሉ ለምን በቴሌቪዥን አለሁ አላሉም?”- የአዲስ አበባ ነዋሪዎች  
-“በስልጣን ሽኩቻው ዙሪያ ገና በጉባዔ ነው የሚወሰነው”- አቶ ስብሐት ነጋ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የጤና ጉዳይ ዛሬም አለየለትም፡ በተለያዩ ዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ብዙኃን መገናኛ ላይ በአቶ መለስ ዜናዊ ጤና ዙሪያ የተለያዩ መረጃዎች እየተዘገቡ ይገኛሉ፡፡

ባለፈው አንድ የግብፅ ከፍተኛ ባለሥልጣንቢኪያ ሞሳርለተባለ ድህረ ገጽ አዲስ ከሚመጣው የኢትዮጵያ አመራር ጋር በተሻለ ሁኔታ እንሰራለንማለታቸውን ተከትሎ የአቶ መለስ የጤና ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ እንዳደረገው ያነጋገርናቸው አንዳንድ የአዲስ አበባና የክልል ነዋሪዎች አስታውቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢህአዴግ ቁልፍ ሰው እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ ስብሐት ነጋ ባለፈው ከጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታየስልጣን ሽግሽግ ላይ እንዳለ የሚያመላክት እሳቤን አንፀባርቀዋል፤ ይህ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ አይሰሩም የሚል ድምዳሜን ያሳያልሲሉ ገልፀዋል፡፡

በአሁን ወቅት ደግሞ በኢህአዴግ ውስጥ የስልጣን ሽኩቻ እንዳለ እና የነ አቶ ስብሐት ነጋ ቡድንም በዓረና ትግራይ /መድረክ ውስጥ ያሉ የቀድሞ የህወሓት አባላትን እያነጋገሩ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ይህን አስመልክቶ ያነጋገርናቸው የቀድሞ የህወሓት መስራች አባል የነበሩና የአሁኑ የዓረና /መድረክ አመራር የሆኑት አቶ አስገደ /ስላሴ የአቶ ስብሐት ነጋ ቡድን መጥቶ ያነጋገረን የለም በዚህ የሚጠመዘዝ አንድም የዓረና /መድረክ አባል የለም፤ በዓረና ውስጥ ያለን የቀድሞ የህወሓት መስራች አባላትም 30 አንበልጥምሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በኢህአዴግ ዉስጥ የተፈጠረዉ የስልጣን ሽኩቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Bereket Simon, Woyanne propaganda chiefየኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሕይወት መኖር አለመኖር አጠያያቂ በሆነበት በዚህ ሰዓት በኢህአዴግ ዉስጥ የተፈጠረዉ የስልጣን ሽኩቻ እያደገ መምጣቱንና በተለይም ሰሞኑን አፍለኛ የከተማ ካድሬዎች በበረከት ስምዖን ዙሪያ መሰባሰብ መጀመራቸዉን የኢህአፓ ድምፅ የሆነዉ ፍኖተ ህብረት የተሰኘዉ ሬድዮ ዘግቧል፡፡

በተያያዘም በዘገባዉ እንደተጠቆመዉ የኢህአዴግ የደቡብ ክንፍ የሆነዉ ደኢህዴን ከህወሓት ጋር እየወገነ ሲሆን ብአዴን ግን አሁንም በልዩነቱ ፀንቶ የዉስጥ ለዉስጥ ፍትጊያዉን አፋፍሞ ቀጥሏል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳዉሎስ በ76 ዓመታቸዉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ


Image




 ሸገር ኤፍ ኤም ዛሬ ጠዋት እንደዘገበዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክና የአለም አቢያተ-ክርስቲያናት ፕሬዝዳንት የሆኑት አብነ ጳዉሎስ በገጠማቸዉ ከባድ የጤና እክል ምክንያት በባልቻ ሆስፒታል ተኝተዉ  የህክምና እርዳታ ሲደረገላቸዉ ቆይቶ ዛሬ ሌሊት በ76 ዓመታቸዉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳዉሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ በመሆን ላለፉት 20 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን ከኢትዮጵያ ኦርዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ዉጭ በሆነ መንገድ ተሹመዋል በሚል ሲወነጀሉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከመንግስት ጋር ባላቸዉ የጠበቀ ግንኙነትና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያሳዩት በነበረ ፍፁም ወገንተኝነት በብዙዎች ዘንድ ይተቹ ነበር፡፡

Wednesday 15 August 2012

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አስተሳሰባችንን በማናወጥ ወንጀል” ሊጠየቁ ይገባል ተባለ!

ይህንን ቃል ለመጀመሪያ ግዜ የሰማሁት ሰፈሬ እንጦጦ ኪዳነምህረት ፀበል ነው። ተጠማቂዎች በአጋንንት እና በሌሎች ርኩስ መናፍስት አይምሯቸው ይናወጥ እና በአስጠማቂዎች ፍዳቸውን ያያሉ። “ያናወጥከውን አዕምሮዋን መልስ…! ልቀቅ…! ውጣ!” ይባላል። ከዛም ወዶ ሳይሆን በግዱ ይለቃል። ያናወጠውን አዕምሮም ይመልሳታል።
ዛሬ ደግሞ ጋዜጣ በማሳተም የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና ከፍ አደርጋለሁ ብሎ መከራውን ሲያይ የነበረው ወዳጃችን ተመስገን ደሳለኝ “የህብረተሰቡን አስተሳሰብ በማናወጥ” ወንጀል ተከሷል።
ይሄንን ነገር እርኩስ መናፍስት ብቻ የሚያደርጉት ሲመስለን የነበርን እኛ፤ በነገሩ ግራ ተጋብተን እንዴት አድርጎ አስተሳሰባችንን እንዳናወጠ  አቃቤ ህግ የሚያቀርበውን ማስረጃ ለመስማት ተቻኩለናል። የተሜን የክስ ሂደት አስመልክቶ እየተከታተልኩ የአቅሜን ያህል “አንጀት ላይ ጠብ የሚል” መረጃ ለማቀበል እሞክራለሁ።

ኢራፓ፦”አገሪቷን ማን እንደሚመራት ባለመታወቁ በስጋት እየታመሰች ትገኛለች”አለ

ኢሳት ዜና:-ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራ ላይ አለመሆናቸው ከተነገረና ከተረጋገጠ ጊዜ አንስቶ፣ ኢትዮጵያን ማን እየመራት እንደሆነ ለሕዝብ ይፋ ባለመገለጹ አገሪቱ በወሬ፣ በሐሜት፣ በፍርኀትና በሥጋት እየታመሰች ትገኛለች ሲል የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ገለጸ።
ኢራፓ ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ   አገሪቱ በማን እየተመራች እንደሆነ  ለኢትዮጵያ ህዝብ በግልጽ እንዲነገረው አሣስቧል።
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 12(1) የመንግሥት አሠራር ለሕዝብ ግልጽ በሆነ መንገድ መከናወን እንዳለበት መደንገጉን ያወሳው ኢራፓ፤  በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 75 በተደነገገው መሠረት፣ ኢትዮጵያ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም በሌላ አካል እየተመራች ከሆነ፣ የሕገ መንግሥቱ ቃል ሳይሸራረፍ በግልጽና በትክክል ለሕዝብ ሊገለጽ እንደሚገባ አስታውቋል፡፡
የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ እንዳሉት፤ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29(3ለ) የሕዝብ ጥቅምን በሚመለከት ሕዝቡ መረጃ የማግኘት መብት እንዳለው የሚያረጋግጠው መብት ሊከበር ይገባል፡፡
ኢራፓ ሰላማዊና ሕገ መንግሥታዊ ዘላቂ መፍትሔ ከመፈለግ አንፃር፣ አገራዊ አጀንዳዎች በተወሰኑ ቡድኖች ከመጋረጃ በስተጀርባ መታየትና መወሰን እንደሌለባቸው ጽኑ እምነት አለው የሚለው የፓርቲው መግለጫ፤ ተቃዋሚና ተፎካካሪ ፓርቲዎችንና ኅብረተሰቡን አሳታፊ የሆነ የፖለቲካ የውይይት መድረክ በመፍጠር፣ ለብሔራዊ መግባባት ጥርጊያ መንገድ መመቻቸት እንዳለበት አስረድቷል፡፡
ኢራፓ እንዳለው፤ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራ ላይ አለመሆናቸው ከተነገረና ከተረጋገጠ ጊዜ አንስቶ፣ ላለፉት ስድስት ሳምንታት ኢትዮጵያን ማን እየመራት እንደሆነ ለሕዝብ ይፋ አልተደረገም። ይህም አገሪቱን በወሬ፣ በሐሜት፣ በፍርኀትና በሥጋት እንድትታመስ አድርጓታል። ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ፤ለውጭና ለውስጥ ጠላቶች ምቹ ሁኔታዎች ይፈጠራል የሚል ስጋት አለ፡፡
ይህ እንዳይፈጠር፤ መንግስት  ለህዝብ ግልጽ መሆን አለበት ብሏል-ኢራፓ።
ሰው እስከሆኑ ድረስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ለምን ታመሙ? እንደማይል ይልቁንም መልካም ጤንነታቸውን እንደሚመኝ የገለጸው ኢራፓ፣ ድነው የአመራር ዘይቤአቸውንና የአስተዳደር ሥርዓታቸውን  የሚፈትሹበት የንስሀና የመሠረታዊ ለውጥ አብሳሪ የሚሆኑበት ዕድል እንዲገጥማቸው ተመኝቷል፡፡

አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር 16 በመቶ ጨመረ


Horn of Africa famine: Somalia, Ethiopia and Kenya suffer worst drought in 60 years



ኢሳት ዜና:-ግብርና ሚኒስቴር እና የውጭ ለጋሾች ትናንት በጋራ ያቀረቡት ሰነድ እንደሚያሳየው ከሀምሌ እስከ ታህሳስ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር ከ3 ሚሊዮን 200 ሺ ወደ 3 ሚሊዮን 700 ሺ ከፍ ብሎአል። ለእነዚህ ተረጅዎች ከ189 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ3 ቢሊዮን 4 መቶ ሚሊዮን በላይ ብር እንደሚያስፈልግ ታውቛል።
41 በመቶ የሚሆኑት ተረጅዎች በሶማሊ፣ 27 በመቶ በኦሮሚያ፣ 10 በመቶ በትግራይ፣ 8 በመቶ በአማራና በደቡብ፣ እንዲሁም 4 በመቶ በአፋር ክልል ይገኛሉ።
በአጠቃላይ 193 ሺ 866 ሜትሪክ ቶን ምግብ እንደሚያስፈልግ በሰነዱ ተመልክቷል።
ይህ አሀዝ በአለም ባንክና በሌሎች የምእራብ አገራት ምግብ ለስራ በሚል መርሀ ግብር የታቀፉትን 8 ሚሊዮን ተረጅዎች አይጨምርም። የእነዚህ ተረጅዎች ቁጥር በተረጅዎች ቁጥር ውስጥ ሲገባ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከ16 በመቶ ያላነሰው በውጭ በሚሰጥ ምጽዋት የሚኖር ነው።
የግብርና ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ሶስት አመታት በምግብ ራሳችንን እንችላለን ብለው ከትናንት በስቲያ መናገራቸው ይታወሳል። ይሁን እንጅ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በምግብ ራሱዋን ለመቻል በርካታ አመታት ትጠብቃለች።
ኢትዮጵያን ላለፉት 21 አመታት የመሩት አቶ መለስ ዜናዊ ከ15 አመታት በፊት በምግብ ራሳችንን እንደምንችል መናገራቸው ይታወሳል።

Tuesday 14 August 2012

አቦይ ስብሐት “አዲስ አድማስ ጋዜጣ ውሸቱን ነው መለስ በቤታቸው የሉም” አሉ .....ከአቤ ቶክቻው

  • d
  • Sh
ስለ አቶ መለስ ዜናዊ ማውራት ደክሞኝ ነበር። ሳስበው ሳስበው እርሳቸው የሆኑትን ሆነው ደከመኝ ሳይሉ እኔ እንዴት ደከመኝ እላለሁ ብዬ ተፀፅቻለሁ። መቅደላዊት የተባለች ወዳጄም ከሪያድ በሰደደችልኝ አስተያየት ሀዘኑን እንረሳው ዘንድ ስለርሳቸው መጨዋወታችንን እንቀጥል እንጂ ድንኳን ሳይነሳ የምን ዝም ዝም ነው የሚል ወቀሳ ሰንዝራልኛለች። እኔም በሆዴ የምን ሀዘን ብዬ ሳበቃ  “እውነት ግን ምን ነካኝ…!” ብዬ ሂሴን ውጫለሁ!
አሁን በቅርቡ ከኔ በላይ ውስጥ አዋቂ ላሳር ያለው አዲስ አድማስ ጋዜጣ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በቤተ መንግስት እያገገሙ ነው” በሚል ርዕስ ባሰፈረው ዘገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራት ባለስልጣናት ጋር እየተመካከሩ በቤታቸው ውስጥ የጠቅላይነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው የሚል ሀተታ አቅርቦልን ነበር።
እርግጥ ነው በርካታ የአራዳ ልጆች የጋዜጣውን ዘገባ በጥርጣሬ ነበር የተመለከቱት። አንዳንዶቹም “ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤተ መንግስት እየገገሙ ነው ወይስ እያገገሙ!?” ሲሉ ጠይቀው ነበር። በአራዶች ቋንቋ “መገገም” ማለት እምቢኝ አልተውም፣ የመጣው ቢመጣ ዘወር አልልም፣ የያዝኩትን ከምለቅ ወገቤ ይላቀቅ ወዘተ. የሚል ትርጉም ቢሰጠው ብዙ አራዶች ይስማሙበታል። በዚህ የትርጉም አግባብ ታድያ አቶ መለስ በቤተ መንገስቱ እውነትም እየገገሙ ከሆነ ሞተውም ሆነ ድነው አይለቁንም ማለት ነው።
የሆነው ሆኖ ትላንት ለኢሳት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) (እናንተዬ ኢሳት እና ኢቲቪ ስማቸው እየተመሳሰለ ያለበትን ሁኔታ ልብ አላችሁልኝ!?) እና አቦይ ስብሀት ለኢሳት ሲናገሩ አዲስ አድማስ ጋዜጣ መለስ ቤተ መንግስት ውስጥ ናቸው ያለው ውሸቱን መሆኑን ተናግረዋል!  አቦይ ስብሀትን አመስግነን አዲስ አድማስን “ሼ” ብለን ስለጠቅላይ ሚኒስትራችን ጉዳይ ዳግም ለማውራት ተነሳሽነታችን እንደመጣ በይፋ እንናገራለን!
በርሰቸው ጉዳይ ሌላም ጨዋታ አለኝ!

Monday 13 August 2012

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በአርማጭሆ ወታደራዊ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ

ኢሳት ዜና:-ኢሕአግ በሰሜን ጎንደር አርማጭሆ ልዩ ስሙ አዋሳ በተሰኘ አካባቢ ከመንግስት ልዩ ሃይል ታጣቂ ጋር ሐምሌ 28-2004 ዓ∙ም ባካሄደው ውጊያ 11 የመንግስት ቡድን ቅጥረኞችን በመግደልና 19 በማቁሰል አንፀባራቂ ድል ማግኘቱን ለኢሳት በላከው መግለጫ አመልክቷል።
በእለቱ የግንባሩ  ሰራዊት የተለመደውን ታሪካዊ ጀብድ ሲያከናውን የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ ድጋፍና አቀባበልም እንዳደረገለት ገልጧል።
ማህበረሰቡ የአርበኛ ግንባር ደጋፊ ነህ በሚል ሳቢያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሰነዘረበት ያለው የግፍ በትር እያየለ መምጣቱ ፣በአካባቢው በኢንቨስትመንት ሽፋን አገሬውን በማፈናቀልና እርስት አልባ በማስቀረት በኩል አገዛዙም የበቀል እርምጃም እየተወሰደ እንደሚገኝ አትቷል።
ግንባሩ እየወሰዳቸው በሚገኝ ወታደራዊ ጥቃቶች ጎን ለጎን እንደ ወትሮው ሁሉ ህዝቡን የማንቃትና የማስታጠቅ እንዲሁም የድርጅቱ አቋም ገላጭ የሆኑ በራሪ ወረቀቶችና መፅሔትቶችን አሰራጭቷል።
በሰራዊቱ በኩል እየተወሰደ በሚገኘው አገርን ከጥፋት ሃይሎች የመታደግ ታሪካዊ እንቅስቃሴ  የኢትዮጵያ ሕዝብ ዛሬም ለለውጥ የሚያደርገውን ትግል ማጠንከር እንደሚገባውና ኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ሊፈጠሩ ይችላሉ በሚባሉ መላ-ምቶች መዘናጋት እንደማይገባው መክሯል።
መንግስት አርበኞች ግንባር አገኘሁ ስላለው ድል ማስተባያም ሆነ ማረጋጋጫ አልሰጠም።
በሌላ ዜና ደግሞ የአርበኛውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለማክሰም በሚል አላማ የተደራጀው ልዩ ሃይል የበላይ የጦር መኮንኖች በጠራራ ፀሐይ ከወልቃይት ሶረቃ አንስቶ በአርማጭሆና መተማ አይን ያወጣ ዘረፋ መጀመራቸውን፣  ዘረፋው የሕዝብ መገልገያ በሆኑ አውቶቡሶችና አገር ሰላም ነው ብለው ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱ ዜጎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ግንባሩ ጠቅሷል።
የልዩ ሃይል ታጣቂ አባላት በዚህ ሳምንት ውስጥ የጀመሩት አይን ያወጣ ዘረፋ ይህ መረጃ ይፋ እስከተደረገበት ዕለት ድረስ ያልተቋረጠ እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬት እንደሚገልጡ ግንባሩ የላከው መረጃ ያመለክታል።

ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ የሚታየው ገንዘብ የማሸሽ እንቅስቃሴ ንግዱን እየጎዳ የኑሮውን ውድነትም እያባበሰው ነው ተባለ

ኢሳት ዜና:-በአንድ የግል ባንክ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኛ ለኢሳት እንደገለጡት፣ የተለያዩ የውጭ እና የአገር ውስጥ ባለሀብቶች ባለፉት ሁለት ወራት ከዚህ በፊት ታይቶ ባልታወቀ ሁኔታ ገንዘባቸውን አሽሽተዋል። ይህንኑ ተከትሎም ንግድ ባንክ ለመድሀኒትና መሰረታዊ ለሚባሉት የፍጆታ እቃዎች መግዢያ ካልሆነ በስተቀር ፣ ማንኛውም ነጋዴ ሌተር ኦፍ ክሬዲት እንዳይከፍት መመሪያ አስተላልፎአል። እገዳው በአገሪቱ የሚታየው የዶላር እጥረት እስከሚቀረፍ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ እንደሚጸና ታውቋል።
ብሄራዊ ባንክም ሆነ ንግድ ባንክ እስካሁን ድረስ የሰጡት ይፋዊ የሆነ መግለጫ  ባይኖርም፣ የባንክ ሰራተኞች ግን ዶላር በገፍ ወደ ውጭ አገር እየተሸኘ መሆኑ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ ሆኗል ብለው እንደሚያምኑ የባንክ ሰራተኛው ገልጠዋል። የአቶ መለስ ዜናዊ የደህንነት ሁኔታ በውል አለመታወቅ ባለሀብቶች ገንዘባቸውን ለማሸሻቸው ዋነኛ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ነው ሰራተኛው ግምታቸውን ያሰፈሩት።
በግልጽ የሚታየው ነገር ይላሉ ሰራተኛው ” በአሁኑ ጊዜ አሳሳቢ በሚባል ደረጃ ዶላር ከአገር ጠፍቷል፤ ሁኔታውም በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚሻሻል አይመስልም።”
መንግስት ከዚህ ቀደም እንዳደረገው ሁሉ ዶላር በጥቁር ገበያ ይሸጣሉ ብሎ የሚገምታቸውን ድርጅቶች ወደ ማሰስና እርማጃ ወደ መውሰድ ሊያመራ ይችላል በማለት አክለዋል።
የዶላር መጥፋት በእቃዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዲታይ አድርጎታል።  መንግስት በአስቸኳይ የአቶ መለስን የጤና ሁኔታ ይፋ ማድረግ ካልቻለና የውጭ እና የአገር ውስጥ ባለሀብቶችን ማረጋጋት ካልቻለ አሁን የሚታየው የውጭ ምንዛሬ እጥረት በአገሪቱ ውስጥ የሚታየውን ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ይበልጥ እንዳያባብሰው ተሰግቷል።

ስደት መርረረን......ከጌዲዮን ደሳለኝ\ኖርዌይ\


ከጌዲዮን ደሳለኝ\ኖርዌይ\
ተሰደን ተሰደን አላልቅ ስላልን እንጂ በጣም ተሰደናል እኮ፥ አገራችንን ለቀን እየወጣን ለባዳ ሳናቀው እያስረከብን እኮ ነው፥፥
የድሮው የማናቀው የቅኝ ግዛት ታሪክ ተከረባብቶ ወደ ወደተስፋይቱ ምድር ወደ አገሬ ኢትዮጵያ ከች እያለ ነው፥፥ እርግጥ ነው አንዳንዴም የመለስ ስርአት ሲመረን አንዳንዴም የነጮቹ ኑሮ ሲያስቀናን መጀመርያ ትዝ የሚለን ስደት ነው፥፥
አሁን አሁን ግን የምንሰደደው የሆነ ከአቅም በላይ ፍለፊታችን ግትር ያለ የሰይጣን ተራራ የሚሉት አይነት ባላንጣ የቆመ መሰለኝ፥፥ እኛም ደሞ ተልፈስፍሰናል፥ ምን እንደምንፈልግ እንኩአን ያወቅነው አልመሰለኝም፥፥ ሰይጣኑን በማስወጣት ፈንታ ለሰይጣኑ መገበር ጀምረናል፥፥