Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 8 September 2012

የጌታቸውን ስድብ የተሞሉ በቀቀኖች






ከዳዊት ዋስይሁን

 እንደተለመደው ሁሌም ጠዋት ከምሰራቸው ስራዎች አንዱ የማህበራዊ ገጽ ጓደኞቼን እንኳን አደራችሁ ማለት እና ባንዳንድ ጉዳዮች ላይ ኦንላይን መጻጻፍ ነው። በተለይ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ መልእክቶች በሰፊው ከማውቃቸውም ከማላውቃቸውም ሰዎች ይደርሱኛል ባብዛኛው ገንቢና ትግላችንን አጠናክረን ለውጡን ማፍጠን እንዳለበት የሚያሳስቡኝ ሲሆኑ አንዳንዶቹ ግን መረን የለቀቀ ከባህላችን ውጭ በሆነ መንገድ በሚያንቋሸሹና በጥላቻ የተሞሉ መልእክቶችን የያዙ ናቸው ይህም ከመገረም አልፌ ተደምሜባቸዋለሁ፣ በተለይ ከሰሞኑ የጻፍኳት መለስን የማልወድበት ምክንያት የምትል ጽሁፌን ያነበቡ ጥቂት /ይህንን ቃል ተውሼ ነው/ የመለስ ደጋፊዎች በመቅበጥበጣቸው አቋሜ በግልጽ እንዲያውቁ ይህንን ደግሜ ጽፌያሁ።

ጥያቄው ለምን በአሁን ሰአት ስድቡና ማንቋሸሹ እንዴት እንዲህ ሊበዛ ቻለ የሚለው ነው። አንድ መምህሬ ባንድ ወቅት ሲያስተምሩኝ ሰዎች በራሳቸው መተማመን ሲያቅታቸው እና ነገሮች ከቁጥጥር ውጪ ሲሆኑባቸው የውስጣቸውን መሸነፍ፣ መረበሽ እና መታመስ ያሸነፉ ስለሚመስላቸው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ከመሳደብና እራሳቸውን ከማዋረድ ወደኋላ አይሉም ምክንያቱም በምክንያታዊነት ከማሳመንና ከማሸነፍ ይልቅ ሌሎች ላይ በሚሰነዝሩት አስጸያፊ ቃል ሰዎች ተንቀጥቅጠው የሚገዙላቸው ስለሚመስላቸው ነው ያሉት ትዝ ያለኝም ወቅት ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስከሬን ያረፈበት 300 ካሬ ሜትር የሚሆን ቦታ ታጠረ


Meles Zenawi's photo on Selassei church wall



ስላሴ ቤተ ክርስቲያን “የአቡነ ጳውሎስ ፎቶ ተነስቶ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶ በግራም በቀኝም ቦታ በጣም በትልቁ ተሰቅሏል” ደፍሮ የሚያነሳው ጠፍቷል!
 
የጠቅላይ ሚኒስትሩ  ግብዓተ መሬት ከተፈጸመ እነሆ 5 ቀናት አለፉ ፤ አስከሬናቸው ያረፈበት ቦታ ከዚህ በፊት የማንም አስከሬን ያላረፈበት ከቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በስተ ግራ በኩል ይገኛል ፤ በቴሌቪዥን እንደተመለከታችሁት የውስጡ ግድግዳ በሴራሚክ ተነጥፎ ሳጥኑ በክብር አፈር እንዳይበላው ታስቦ አስከሬኑ አርፏል ፤ ሳጥኑ ላይ ወደፊት ሙዚየም እንደሚሰራ ታሳቢ በማድረግ ብዙ ድንጋይ እና አፈር ሊያሸክሟቻ አልወደዱም ፤ ባይሆን ትንሽ ባዞላ ቢጤ ከላይ በማስቀመጥ ክፍተቱን በሲሚንቶ በመሙላት ከላይ የኢትዮጵያ ባንዲራን አልብሰዋቸዋል ፤

Tuesday 4 September 2012

ይድረስ ለአነስተኛ እና ጥቃቅን ስድብ አምራቾች!...... ከአቤ ቶክቻው

ይቺ ጨዋታ ባለፈው ጥር ወር በዌብ ሳይቶች እና በፍትህ ጋዜጣ ላይ ወጥታ ነበር። ዝም ብዬ ሳስበው ዛሬ ደግመን ብንጫወታት ወቅታዊ ትመስለኛለች… ጎሽ እስቲ እናውጋ…!

በመጀመሪያም 1

ይህ ፅሁፍ ባለፈው ሳምንት ለምናፍቃት ፍትህ ጋዜጣ ልኬው የነበረ ነው። ታድያ እንደምናውቀው ለፍትህ ሲፃፍ ራስን ሳንሱር ማድረግ ግድ ይላል። እናም በተቻለኝ አቅም ቆጠብ ሰደር ብዬ ነው የፃፍኩት። እየተሳቀቅሁ። ምክንያቱ ደግሞ ለራሴ በመስጋት አይደለም።

እኔማ አንድ ጊዜ “የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም” አንዲሉ ከውዲቱ ሀገሬ ከተሰደድኩ እንደዋዛ ሶስት ወራት አለፉ። እስከምመለስ ድረስ ስንት ወራት እንደሚያልፉ እንጃ! ነግቶ በመሸ ቁጥር ሁሌም ፒያሳ በአይኔ ላይ ትሄዳለች። አራት ኪሎ መቀጣጠር ያምረኛል። ሽሮሜዳ ደረስ ብሎ መመለስ ይናፍቀኛል። የአዲሳባ ስታድየም ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን ለመታደም እጓጓለሁ። በተቃዋሚዎች ስብሰባ ላይ መገኘት ያሰኘኛል። እንኳን ሌላው ቀርቶ ካገር እንድሰደድ ምክንያት የሆነኝ ኢህአዴግ፤ የሚጠራቸው ባለ አበል ሰልፎች ላይ ራሱ አባልም ባልሆን አበልም ባይሰጠኝ ለመታደም የማደርገው ጥረት ራሱ ዛሬም ይናፍቀኛል።

Monday 3 September 2012

ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስን ለመተካት እየታገሉ ነው

ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤታቸውን በሞት ካጡ በኃላ በእሳቸው እግር ተተክተው የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ ተቆናጥጦ ወደ ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርነት ለመሳብ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ላይ መክረማቸውን ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡
በኢህአዴግ 36 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ብቸኛ ሴት ሆነው በመስከረም ወር 2003 ዓ.ም ከፍተኛውን የፓርቲ ሥልጣን በባለቤታቸው በአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ ድጋፍ ማግኘት የቻሉት ወ/ሮ አዜብ የሰሞኑን ሐዘናቸውን ለድጋፍ ማሰባሰቢያ እንደተጠቀሙበት ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ አዜብ ለድጋፍ ማሰባሰቢያ ይጠቅሙኛል የሚሉዋቸው የህወሃት ሰዎች ለቅሶ ለመድረስ ቤተመንግስት በሚመጡበት ወቅት አንገታቸውን እያነቁ በማልቀስና በማስለቀስ፣የማይፈልጉዋቸውን ደግሞ ፊት ሲነሱ መቆየታቸው በተለይ በአመራር ላይ ባሉት የብአዴን ሰዎች ዘንድ አልተወደደላቸውም፡፡
ወ/ሮ አዜብ ባለቤታቸው አቶ መለስ በ8ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በጡረታ ያሰናበታቸው አቶ ሥዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዬ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣አቶ ተፈራ ዋልዋ፣አቶ አዲሱ ለገሰን “የመለስን ራዕይ ለማሳካት” በሚል ስትራቴጂ ከጎንዋ ለማሰለፍ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መሰንበታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

የመለስ “ተወዳጅነት” ለኢህአዴግ ምኑ ነው!? ....ከአቤ ቶክቻው

የርዕሷ ዜማ በአንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ “የአክሱም ሀውልት ለደቡብ ምኑ ነው!?” ሲሉ የተናገሯትን ትመስላለች። እናም ለዜማ ኩረጃዬ ይቅርታ ጠይቄ እቀጥላለሁ።

አሁን አሁን ኢህአዴግ ምን እየሰራ እንደሆነ እጅግ በጣም ግራ እየገባኝ መጥቷል… “ገና አሁን!” ብለው ሲጠይቁኝ ይታየኛል። እኔም አይ ገና አሁን ሳይሆን አሁንም ድጋሚ በጣም ግራ እየገባኝ ነው!? እልዎታለሁ። የምሬን እኮ ነው…

አቶ መለስ ሞቱ በተባለ ሃያ አራት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አስከሬናቸው አዲሳባ ይገባል ተባለ። በነገራችን ላይ ይሄ ፍጥነት አቶ መለስ የሞቱት ቀድመው ነው። የሚሉትን ወገኖች ንግግር ይበልጥ ያጠናክረዋል። ይሄንን እንተወው እዚህ ግባ የሚባል ወሬ አይደለም። ኢቲቪም ሆነ አቶ በረከት እንደሆኑ “ሰው ያምነናል” ብለው ይናገሩ እንጂ ሁሉም በየጓዳው “አዬ..ዬ…” እንደሚለቸው እናውቃለን…!

(እንኳን ይቺንና የአበል ለቅሶ እንለያለን…!)

የሆነው ሆኖ ለአቶ መለስ በርካታ ሰው አለቀሰላቸው። እንደ እውነቱ ከሆነ ትክክለኛው የአቶ መለስ አዛኞች የመጀመሪያው ቀን እየዬ ብለው ቦሌ አየር መንገድ የታዩት ናቸው። ከዛ በኋላ ይሄንን ያኽል ሰው ይመጣል ብለው ያልጠበቁት እነ ጋሽ ኢህአዴግ ልክ ባለፈው ጊዜ አቶ መለስ የዘጠና ሰባቱን የኢህአዴግ ሰልፍ ሲያዩ አቅላቸውን ስተው “ይሄንን የህዝብ ማዕበል ይዘን ማጭበርበር ሳያስፈልገን ምርጫውን እናሸንፋለን…!” እንዳሉት አይነት “ይሄንን የህዝብ ማዕበል ይዘን በለቅሶ እድገት እመርታ እናሳያለን” ብለው ለራሳቸው ቃል ገቡ። ገቡናም ለሚቀጥሉት አስራ ምናምን ቀናት ህዝቡን ለማስለቀስ ተማማሉ፤