Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 9 November 2012

66 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች በ2ዐዐ5 ዓም በሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ ረቂቅ ላይ ያቀረቡት ጥያቄ



ጥቅምት 29 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት
አዲስ አበባ


ጉዳዩ፡- ጥቅምት 15 ቀን 2ዐዐ5 ዓም በአዳማ ከተማ ቦርዱ ‹‹በ2ዐዐ5 ዓም በሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ ረቂቅ›› ላይ ከፖለቲካ ድርጅቶች ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባአደረገው ምክክር ፕሮግራም ተገኝተው ፔቲሽን ከፈረሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረበ ጥያቄ ስለማቅረብ፣

1. አጠቃላይ፡-
ከላይ በተጠቀሰው ቀን፣ ቦታና ርዕሰ ጉዳይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራር (ቦርድ) እና ሥራ አስፈፃሚ (ጽ/ቤት ኃላፊና ሠራተኞች) በተገኛችሁበት 66 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተን ውይይት ማድረጋችን ይታወሳል፡፡ በዚህ የምክክር ፕሮግራም ላይ ከተሣተፉ የፖለቲካ ድርጅቶች አብዛኛዎቹ ‹‹የአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር እየጠበበ መምጣቱንና የምርጫ ውድድር ሜዳው የተስተካከለ ያለመሆኑን፣ ከዚህ በፊት የተደረጉ ምርጫዎች በአፈፃፀም ችግሮች የተተበተቡ መሆናቸውን፣ እንዲሁም በየደረጃው ባሉት የምርጫ ቦርድ አመራርና አስፈፃሚ አካላት ተአማኒነትና ተቀባይነት ላይ ያለውን ጥያቄ ተጨባጭ መገለጫዎችንና መሣያዎችን በማቅረብ   ካስረዱ በኋላ በእነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት ከጊዜ ሠሌዳው ረቂቅ ላይ ከመወያየት ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል›› የሚል ሃሳብ ማቅረባችን በእለቱ በተቀረፀው ኦዲዮ-ቪዲዮ ላይ ይገኛል፡፡

በወቅቱ ላነሳናቸው ጉዳዮች በቂ መልስ ባለማግኘታችን በፕሮግራሙ ላይ የተሣተፍን 33 የፖለቲካ ድርጅቶች ከጊዜ ሠሌዳው በፊት የምርጫው ፍትሐዊነት፣ ዴሞክራሲያዊነትና ነፃ መሆን ላይ የሚደረግ ውይይት እንዲደረግ ፔቲሽን ለመፈራረም ተገደናል፡፡ የፔቲሽኑ ይዘት (1 ገጽ) እና የፈረሙ የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች ዝርዝር (2 ገጽ)  ከዚህ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ በመቀጠልም ፔቲሽንኑን የፈረምነው ፓርቲዎች ተጠሪዎች በ25/ዐ2/2ዐዐ5 ዓም ተገናኝተን በጉዳዩ ላይ በጥልቀትና በስፋት ተወይይተናል፡፡ ጥያቄአችን በዚህ መልክ እንዲቀርብ ተስማምተናል፡፡

ወይዘሮ አዜብ አደገኛ ቦታ "ማኖ" ነኩ........... አቤ ቶክቻው


በዛ ሰሞን አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆኑ የአፍሪካ መሪ ናቸው የሚለው ደግሞ ደግሞ ሲነገረን እንግዲህ እኛ እስከዛሬ ባንሰማ ነው እንጂ አዎ የአፍሪካ መሪ ናቸው ብለን አምነን ቁጭ ብለን ባለበት በዚህ ሰዓት፤ ወሮዋ ብቅ ብለው “መለስ ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ የቀየሰው ስትራቴጂ ነበር!” ብለው ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ተናግረዋል።

እኔማ “አረ ባክዎን መለስ የኢትዮጵያ መሪ ናቸው” “አረ እባክዎን መለስ የአፍሪካ መሪ ናቸው” “አረ እባክዎን እርሳቸው አድሎ አያውቁም” ብዬ ሀገር ይያያዝልኝ እያልኩ በማየው ቪዲዮ ላይ ለፍልፌ ነበር።

ማን ይስማኝ “ኢህአዴግ አፍ እንጂ ጆሮ የላትም” አሉ ፕሮፌሰሩ…! አንድ ወዳጄ “እኚህ ሰውዬ በጥረታቸው ፕሮፌሰር ባይሆኑም ኖር ለዝች ንግግራቸው ብቻ ፕሮፌሰር አደርጋቸው ነበር” ብሎኛል…!

እንደ ወይዘሮ አዜብ ንግግር ከሆነ ይሄ ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል የማድረግ ስትራቴጂ በመለስ የተፃፈ ሲሆን ኢፈርት የተባለው የብዙ ኩባንያዎች እናት በዋናነት ያንቀሳቅሰዋል። እርሱንም እርሳቸው እና መሌ በመላ ያንቀሳቅሱታል።

ኢፈርት በሀብቱ ከኢትዮጵያ የሚደርስበት እንደሌለም “እንቁልጭልጭ” እያሉ ወሮ አዜብ ነግረውናል። ታድያ ይሄ ድርጅት ለትግራይ ብቻ እንዲሰራ ምነው ተፈረደበት!? አቶ መለስስ የኢትዮጵያ መሪ ሆነው ሳለ ስለ አንዲት ክልል ብቻ እንዲህ አብዝተው ሲጨነቁ መኖራቸው ለምን ይሆን!?

ለማንኛውም የወይዘሮ አዜብ ቃለ ምልልስን ልብ ብሎ ለተመለከተው ሰው በዚህ ክፉ ሰዓት እና መጥፎ ቦታ ኳስ በእጅ የመጠፍጠፍ ያክል ነው! እያሉ ብዙዎች እየተናገሩ ይገኛሉ!
http://www.youtube.com/watch?v=34yUalEtrDA&feature=youtu.be

Wednesday 7 November 2012

የመከላከያ ሰራዊት አዲሱን መንግስት እንዲቀበሉ ለማሳመን የሚደረገው ግምገማ ቀጥሎአል

ጥቅምት ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኢሳት የመከላከያ ሰራዊት ምንጮች እንደገለጡት  የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ  ካረፉ እና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ከተሾሙ በሁዋላ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የሚካሄደው ግምገማ ተጠናክሮ ቀጥሎአል።
ከፍተኛ የጦር አዛዦች ግምገማ መጠናቀቁን የጠቆሙት ምንጮች፣ ግምገማው ወደ መካከለኛና ተራ ወታደሮች እየወረደ ነው።
በምስራቅ እዝ የሚገኙ እስከ ኮሎኔልነት ማእረግ ያላቸው መኮንኖች ሀረር ውስጥ ልዩ ስፍራው ቤተመንግስት በሚባለው ቦታ ከፍተኛ ግምገማ እያደረጉ ነው። የግምገማው ዋና አጀንዳ አቶ ሀይለማርያም ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከመሾማቸው  በፊት ለ34 ወታደራዊ መኮንኖች ስለተሰጠው ማእረግ፣ ስለ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒሰትር እና ስለመለስ ራእይ መሆኑ ታውቋል።
ሀረር ውስጥ በሚካሄደው ግምገማ የአመለካከት ልዩነቶች መታየታቸውንና ግልጽ ሆኖ ባይወጣም ክፍፍል መፈጠሩን ምንጮች ገልጠዋል።
በቅርቡ ለ34 ወታደራዊ መኮንኖች ከፍተኛ የማእረግ እድገት ሲሰጥ፣ 29ኙን የማእረግ እድገት የወሰዱት የህወሀት ጄኔራሎች መሆናቸው በሌሎች ብሄሮች የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ቅሬታ መፍጠሩ ታውቋል።አሁን የሚካሄደው ግምገማ በዋነኝነት ይህን ቅሬታ ለመፍታት መሆኑ ታውቋል።
ግምገማው  ሹመቱን የማይቀበሉትንና በአዲሱ አስተዳዳር ላይ ቅሬታ ያላቸውን መኮንኖች በመለየት ለመውሰድ ተብሎ የተዘጋጀ ነው በሚል ፍርሀት የሌሎች ብሄር ተወላጅ መኮንኖች አስተያየቶችን ከመስጠት መቆጠባቸውንና አስተያየትም ከሰጡ የድጋፍ አስተያየት ብቻ በመስጠት ተቃውሞአቸውን በውስጣቸው መያዛቸውን ምንጫችን ገልጠዋል።
ከፍተኛ አዛዦች በተሳተፉት ግምገማ የአየር ሀይል ዋና አዛዥ የሆኑት ሜጀር ጄነራል ሞላ ሀይለማርያም  ከስልጣን መባረራቸው ይታወሳል።

በቃሊቲ ግንቦት 7 እየተባሉ በሚጠሩ እስረኞች ላይ ጥቃት እየተፈጸመ መሆኑ ታወቀ

ጥቅምት ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የኢሳት የቃሊቲ ምንጮቻችን  እንደገለጡት በተለምዶ የአማራ ተወላጅ የሆኑትንና ከፖለቲካ ጋር  በተያያዘ የታሰሩትን  በሙሉ  የማረሚያ ቤቱ ሀላፊዎች ግንቦት7 እያሉ እንደሚጠሩዋቸው ገልጸው፣ በእረኞች ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶች እየተፈጸመ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም  በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተከሰው በእስር ላይ በሚገኙት ወታደራዊ መኮንኖች ላይ እጅግ ኢሰብዓዊ የሆነ አሰቃቂ ድብደባ ( ቶርች) የተፈጸመባቸው መሆኑን ኢሳት የቃሊቲ ምንጮችን በመጥቀስ ለህዝብ ይፋ አድርጎ ነበር።
ዘገባው አለማቀፍ ትኩረትን በመሳቡ፣ በቃሊቲ የነበረው ሁኔታ በአንጻራዊ መልኩ ተሻሻሎ እንደነበር የጠቀሱት ምንጮች፣  ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በእነ አቶ አንዱአለም አራጌ መዝገብ በተከሰሱትና በሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚደርሰው እንግልት እየጨመረ መምጣቱ ታውቋል።
በቃሊቲና ቂሊንጦ ማረማያ ቤቶች በሚገኙ እስረኞች ላይ ከሚተገበሩት የማሰቃያ መንገዶች መካከል ድብደባ አንዱ መሆኑ ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በሽብር ወንጀል ተከሶ ፍረደኛ የሆኑት አቶ አንዱአለም አባተ ትናንት እኩለ ቀን ላይ ይግባኝ ሰሚ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
አቶ አንዱአለም በግላቸው ጠበቃ ለመቅጠር እንደማይችሉ በመግለጻቸው መንግስት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱም መንግስት ለእስረኛው ጠበቃ እንዲያቆምላቸው ትእዛዝ ሰጥቷል።  ይግባኙን ለማየትም ለህዳር 24 ፣ 2005 ዓም የጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱን አጠናቋል።

Monday 5 November 2012

በደጋን ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች ታሰሩ አካባቢው በፌደራል ፖሊስ ተከቧል

ጥቅምት ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በደቡብ ወሎ ዞን በደጋን ወረዳ ከሳምንታት በፊት የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ አካባቢው ከትናንትጀምሮ እንደገና በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በሁዋላ ከ100 በላይ ሰዎች ተይዘው መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጠዋል።
ወጣቶችም አካባቢውን ለቀው ወደ ወደ ገጠር በብዛት መሰሰደዳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ከታሰሩት መካከል በከተማዋ ውስጥ በእድሜ አዛውንት የሆኑት የ90 አመቱ አቶ እንድሪስ ከማል ይገኙበታል።
ኢሳት አንዳንድ ወጣቶችን ለማናገር የቻለ ሲሆን፣ ወጣቶቹ እንደሚሉት አካባቢው በሙሉ በፌደራል ፖሊስ በመከበቡ ወደ ጎረቤት አገሮች ወይም ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ለመሸሽ አልቻሉም።
እስረኞቹን ሆስፒታል ውስጥ በማጠራቀም ወደ ተለያዩ ቦታዎች ወስደው  እያሰሩዋቸው መሆኑ ታውቋል።
ባለፈው ወር በደጋን በተነሳው ግጭት ከ4 ሰዎች ያላነሱ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል። የግጭቱ መንስኤ በአዲስ አበባ ከሚካሄደው የሙስሊሞች ተቃውሞ ጋር የተያያዘ ነው።
በሌላ ዜና ደግሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መቋቋሙን የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ይፋ አድርገዋል።
ሼክ ኪያር መሃመድ አማን የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት፣ ሼክ ከድር መሃመድ፣  ምክትል ፕሬዝዳንት
አቶ መሃመድ አሊ ደግሞ ጸሃፊ ሆነው ተመርጠዋል።
አወዛጋቢ የሆነው የሙስሊሞች ጥያቄ በውል ባልተቋጨበት በዚህ ጊዜ አዲስ የእሰልምና ምክር ቤት ምርጫ መደረጉ ውዝግቡ እንዲቀጥል የሚያደርገው መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ።
በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ሙስሊሞች ከሚያነሱዋቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱ የሀይማኖት መሪዎቻችንን ያለመንግስት ታልቃ ገብነት በዲሞክራሲያዊ መንገድ እንምረጥ የሚል ነው።

ከጠ/ሚኒስቴር መለስ ምኑን እንውረስ?

ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ መሞታቸው ሁሉም ሰው ያሳዘነ ጉዳይ ነው፡፡ ለምን ከተባለ ሁሉም ሰው ከመሞት የሚያመልጥ ባይኖርም የአሟሟታቸው ሁኔታ ግን ለየት ባለ ሁኔታ ስለተፈፀመ በጣም ያሳዝናል፡፡
መጀመሪያ በሪፖርተር ጋዜጣ አንድ የመንግሥት ቃለ-አቀባይ መነሻ በሌለው ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ የጤና ችግር የለባቸውም የሚል መግለጫ ሰጠ፡፡ ሰዉየው ይህ ያሉበት ምክንያት ምንድነው? ስለጤናቸው ምን ተብሎ እና ነው ይህን መግለጫ የሰጡ ማለት ጀመረ፡፡ በስተጀርባ አንድ ነገር እንዳለ ጥርጣሬ ውስጥ ገባ፡፡
ቆየት ብለው ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ታመው ህክምና እንደገቡና ህመሙም የሚያሰጋ እንዳልሆነ መግለጫ ተሰጠ፡፡ ቆየት ብለውም በተለይ አቶ በረከት ስምዖን በዕረፍት ላይ መሆናቸው በቅርብ ግዜ ሥራቸው እንደሚጀምሩ መግለጫ ሰጡ፡፡
ይህ ሁላ ሲሆን ግን አንድ ደ/ር እንኳ ስለየጤንነታቸው ጉዳይ መግለጫ የሰጠ አልነበረም፡፡ ይህ ህዝቡ በበለጠ ጥርጣሬ ውስጥ ከተተው፡፡ የታመመ ሰው ስለህመሙ የሚያቅና ሁኔታውን ማብራራት የሚችል ሃኪም ነው ስለ ጠቅላይ ሚኒስቴር የጤንነት ጉዳይ የሚነገረን ያለ በመንግሥት ሥልጣን ባሉ ሰዎች ነው ይህንን ነገር እንዴት ነው በማለት ራሱ በራሱ መወያየት ጀመረ፡፡ የሃኪም መግለጫ ሳይሰማ ዜና ዕረፍታቸው ተሰማ፡፡ መሞታቸው በጣም አሳዝኖናል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ባህሪያት
ለተነሱለት ዓላማ በፅናት የሚተገብሩ ሰው ነበሩ፡፡ የሆነ ሐሳብ አቅርበው ተቀባይነት ካላገኘ ሞተው ይገኛሉ፡፡ በሐሳባቸውና በአመለካከታቸው የሚነሱ ልዩነቶች ፍፁም አያስተናግዱም፡፡ ለማስተናገድ ቢሞኩሩም የትም አይደርስም ብለው የገመቱት እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
በዓቅም የሚቀናቀናቸው ሰው አይወዱም፡፡ ብዙ አብነቶች ማቅረብ ይቻላል፡፡ አቶ አርከበ ዕቁባይ አቶ መለስ እንደሚጠሩዋቸው “ጅብ” ናቸው፡፡ ጅብነታቸው በሥራ ነው፡፡ የትግራይ ም/ፕሬሲዳንት በነበሩበት ጊዜ አንዳንድ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ሲሞኩሩ አዲስ አበባ ወስደው የአዲስ አበባ ከንቲባ ሁነው እንዲሾሙ አደረጉ፡፡ በዚ ጊዜ በተለይ በነጋዴው የአገልግሎት አሰጣጥ ለውጥ ሲያስመዘግቡ ቀለም ከመቀባት የማያልፍ ሥራ ነው የሠራኸው ብለው መዓት ወረዱባቸው፡፡ ከዛ በኋላ የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ድኤታ ሁነው እንዲሠሩ ተደረገ፡፡ ከዛ በማንሳት ደግሞ አማካሪ ብለው ሰው በማያያቸው (አቅማቸው ህዝቡ በማያየው ዋሻ) እንዲገቡ አደረጉ፡፡ይህ ሁሉ መነሻው ስጋት ነው፡፡ አቶ አርከባ በግልፅ መቃወም አልደፈሩም እንጂ ውስጣቸው ከኛ በላይ የአቶ መለስ በላያቸው ላይ ያደረጉት ዘመቻ ያውቁታል፡፡ በዚህ ቅሬታ ነበር በህወሐት ማእከላዊ ኮሚቴ ለፖሊት ቢሮ ምርጫ አልፈልግም ብለው ራሳቸው ያገለሉት፡፡