Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Saturday 4 August 2012

መንግሥት በለንደን አውሮፕላን ማረፊያ ዕፅ ሲያዘዋውሩ ስለተያዙት ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት አላውቅም አለ ....ጉድ ነው !!!

በለንደን ሔትሮ አውሮፕላን ማረፊያ 56 ኪሎ ግራም ካናቢስ ሲያዘዋውሩ ስለተያዙት ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት ጉዳይ መንግሥት ምንም አላውቅም አለ፡፡
በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የቪዛ ክፍል ውስጥ የሚሠሩት ወይዘሮ አመለወርቅ ወንድማገኝ 160 ሺሕ ፓውንድ ዋጋ ያለው የካናቢስ ዕፅ ሲያዘዋውሩ ር የተያዙ ሲሆን፣ የሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወር እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለድርጊቱ መስማታቸውን ገልጸው፣ ጉዳዩን ገና እያጣሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለጊዜው ከዚህ በላይ ስለጉዳዩ መናገር እንደማይቻል ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የ36 ዓመቷ ወይዘሮ አመለወርቅ 56 ኪሎ ግራሙን ካናቢስ ከአዲስ አበባ አየር መንገድ ሲነሱ ከሰው የተቀበሉት መሆኑን ተናግረው፣ የተቀበሉት ዕቃ ግን ሥጋና በርበሬ ነው የሚል እምነት እንደነበራቸው አስረድተዋል፡፡ በለንደን የሚገኘው ፍርድ ቤት የወይዘሮ አመለወርቅን የዲፕሎማቲክ መብት በመግፈፍ ዕፅ በማዘዋወር ወንጀል የሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወር እስራት ፈርዶባቸዋል፡፡ ዳኛውም ለዲፕሎማቷ፣ ‹‹ያለመከሰስ መብት አለኝ በሚል እሳቤ ዕፁን ይዘሽ መገኘትሽ ለክሱ ዋነኛ መነሻ ነው፤ ምን እንደፈጸምሽም ታውቂያለሽ፤›› ብለዋቸዋል፡፡

በረከት ስምኦን “መለስ አልሞተም” አለ! ሙክታር ከድር የመለስን ቦታ ሸፍኖ እየሰራ መሆኑ ታወቀ!!

ኢ.ኤም.ኤፍ (ልዩ ዘገባ) – በአሁኑ ወቅት የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ከህክምና አገግሞ ለስራ ባለመብቃቱ፤ በሬዲዮ ፋና በኩል… “ጠቅላይ ሚንስትሩ ከሞተ ማን ተክቶ ይሰራል?” በሚል ርዕስ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ነበር። በዚህም ውይይት ወቅት የህግ ሰዎች “በምትኩ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተክቶት ይሰራል” የሚል ትንታኔ ሰጥተዋል። ይህ እንግዲህ በኢህአዴግ ሬዲዮ ፋና በኩል የተደመጠ ነው። በተግባር ግን አሁን የጠቅላይ ሚንስትሩን ቢሮ ስራ እየሰራ የሚገኘው የቀድሞው የኦሮሚያ ምክትል ፕሬዘዳንት የነበረው፣ ሙክታር ከድር መሆኑ ታውቋል።
ሙክታር ከድር የኢህአዴግ ጽ/ቤት ኃላፊ ሲሆን፤ መለስ ዜናዊ ከመታመሙ በፊት የጠቅላይ ሚንስትሩን ቢሮ ሸፍኖ እንዲሰራ ተደርጎ እንደነበር የደረሰን መረጃ አሳውቋል። በአሁኑም ወቅት ሚንስትሮች ግንኙነታቸውን ከምክትሉ ጠ/ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ሳይሆን፤ ከሙክታር ከድር ጋር እንዲሆን መመሪያ ተላልፏል። በዚህም መሰረት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ኃይለማርያም በውጭ ስራዎች ብቻ ትኩረት እንዲያደርግ በኢህአዴግ በኩል ትዕዛዝ የተሰጠው መሆኑን የደረሰን የውስጥ መረጃ ያሳውቃል።

Miscommunications, EPRDF’s usual way to escape crises

by BIZUAYEHU TSEGAYE
Do we Ethiopians agree to disagree to form a United Action?Not that previously unfamiliar to the readers; having a dialog about a topic and end up debating totally different issue or specking twice on a topic and end up having two different closing arguments…it can happen in every day of our life. But, not easy-thing to skip when public officials do it.  Such miscommunication can have two reasons:
One; could be due to communication barriers attributed to  inefficiency in communicating or lack of focus; which is unintentional.
Second; could also resulted with diversion. Deliberate change of subject with out disclosing it‘s bad intention. Though both can be equally destructive.
In relation to the subject, most might have caught with the repeated hierarchically inconsistent public announcements made by EPRDF’s officials earlier and currently on Zenawi’s disappearance from media.
Having the fact EPRDF is animus to communication; one may look for answer wither it’s weak public communications are intentional or attributed to lack of proficiency?
In effort to forward my reflection I want to share you…the readers the following story first.
It was a while a go when a person having the opportunity to get in touch with EPRDF officials and whom I was very close too shared me about the attention diversion strategies been followed by the consecutive administrations including the current one. It has helped in shaping my perception about the actions taken by EPRDF.

የአቶ መለስ ዜናዊ መጨረሻ አሁንም የኢትዮጵያውያን ያልተመለሰ ጥያቄ ሆኗል

ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-እጅግ ውስብስብ የሆኑ ሚስጢሮችን በማውጣት የሚታወቁት አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን የአቶ መለስን የደህንነት ሁኔታ ለማወቅ አለመቻላቸው ብዙዎችን አነጋግሯል። አንዳንድ ወገኖች የምእራባዊያን የመገናኛ ብዙሀን ከአሜሪካ ወይም ከአውሮፓ መንግስታት የ”ይለፍ መብራት” ካልበራላቸው፣ ዜናዎችን ለማውጣት ፈቃደኛ አይሆኑም በማለት ሲናገሩ ሌሎች ደግሞ ኢትዮጵያ የምእራባዊያን የመገናኛ ብዙሀን የምትስብ አገር ባለመሆኑዋ የመገናኛ ብዙሀኑ ትኩረት እንደነፈጉዋት ይገልጣሉ።
በመሀሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ድረገጾች በመግባት ዜናዎችን በእየለቱ ይቃርማሉ። አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ቦታ መራቅ ለኢትዮጵያ አዲስ ተስፋን ይዞ ሊመጣ ይችላል ሲሉ፣ ሌሎች ወገኖች ደግሞ፣ በፍትህ ጋዜጣ ላይ የደረሰውን በመፍራት ከእስካሁኑም የባሰ አፋኝ መንግስት እንዳይመጣ ይሰጋሉ።

ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ይቅርታ አልጠይቅም አሉ

ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ባለቤታቸው የታሰሩባቸው የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ፦”ይቅርታ ጠይቁ” በመባላቸውን በመጥቀስ፦” የሠራሁት ስህተት ስለሌለ የምጠይቀው ይቅርታ የለም” አሉ።
ባለቤቴ  ከህፃናት ልጆች ተነጥላ ትክክለኛ ባልሆነ ማስረጃ ታስራብኛለች ሲሉም  አቤት አሉ።
ሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ  የባለቤታቸውን መታሰር አስመልክቶ በኢትዮ ቻነል እና በሰንደቅ ጋዜጦች ለወጡት ዜናዎች መልስ በሰጡበትና በዛሬው የ ኢትዮ ቻነል ጋዜጣ ላይ በታተመው ጽሁፋቸው  ፤በጋዜጦቹ የወጡትን ጽሁፎች ተከትሎ  ባለቤታቸው  ከሰሞኑ የ እስልምና ተከታዮች እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ተደርጎ የሚወራው ስህተት እንደሆነ ገልጸዋል።

አንድ አስተያየት፤ አቶ ጁነዲን ቻል ያድርጉት… ሁሉም የሚታሰረው ያለ ማስረጃ ነው!........አቤ ቶክቻው

አቶ ጁነዲን ሳዶ ዛሬ ለታተመው ኢትዮ ቻናል  ጋዜጣ  የነገሩትን አውራምባ ታይምስ ዌብ ሳት አቀብላን ተመልክተነዋል።
ሚኒስቴር ጁነዲን ሳዶ ባለቤታቸው ከታሰሩባቸው ዛሬ አስራ ስድስተኛ ቀናቸው ነው። በዚህም የተነሳ ቤታቸው መቀዝቀዙን ልጆቻቸው መጎሳቆላቸውን እና የመሳሰሉትን ጠቅሰው እስሩ አግባብ አይደለም ብለው ተናግረዋል።
የሚኒስቴሩ ባለቤት የታሰሩት ከአክራሪነት ጋር በተያያዘ መሆኑን ነገር ግን ምንም ማስረጃ እንዳልተገኘባቸው እና የዚህ አይነቱ እስር ነውር መሆኑን አስረድተውናል።
ጥሩ ነው ለሚስትዎ እርስዎ ካልተከራከሩላቸው ሌላ ማን አላቸው…!? ነገር ግን ኦቦ ጁነዲን፤ ካለ ማስረጃ መታሰር እኛ ሀገር ብርቅ ነው እንዴ!?
አንድ ወዳጄ በዚህ ጉዳይ ላይ ስናወራ ምን አለኝ መሰልዎ፤ በቅርቡ የዋልድባ ገዳም መነኩሴዎችን እና የአንዋር መስጊድ “ኡስታዞችን” እስር አነሳልኝ እና “ተዋርዶ ያለበት እስላም ክርስቲያኑ ተዘነጋሽ እንዴ ኢትዮጵያ መሆኑ!” ሲል አንጎራጉሮልኛል።

If Meles goes too…

The reported ill health of Ethiopia’s big man is jangling the nerves

The EconomistMELES ZENAWI, Ethiopia’s usually dynamic prime minister, has not been seen in public since mid-June. Regularly invited to grand gatherings such as those of the G8 and G20, he has often been deemed “the voice of Africa”. But he was notably absent earlier this month from a summit of the African Union in his own capital, Addis Ababa. His government added to the uncertainty by first denying that he was critically ill in a hospital in Belgium, then announcing that he was away on sick leave. When a weekly newspaper was about to publish an article on his health, the authorities stopped the presses.

Is Ethiopia’s PM dead, sick, or just on holiday?

Foreign Policy
Meles Zenawi’s Shame and the Dead-End of HatredIn an echo of death rumors that have periodically surrounded former Egyptian President Hosni Mubarak and Zimbabwean President Robert Mugabe this year, there’s increasing speculation about the whereabouts of Ethiopia’s Prime Minister Meles Zenawi after a local radio station pronounced him dead. Meles hasn’t been seen in public since mid-July, and confirming his whereabouts and condition has proven difficult.
The confusion hit a fever pitch on July 30 when Ethiopian opposition radio outlet ESAT announced they had confirmed that Meles had died.  They claimed to have received the information from diplomatic and international sources including the International Crisis Group (ICG).

ESAT interview with Andargachew Tsige August 2012 Ethiopia


Woyane diplomat jailed in UK for cannabis smuggling

(AFP)
Amelework Wondemagegne, an official at the Ethiopian embassy in Washington, had tried to claim diplomatic immunity when she was caught at the airport in April with 56 kilograms (123 pounds) of cannabis.LONDON — A court in London on Thursday jailed an Ethiopian diplomat for trying to smuggle a large stash of cannabis through London’s Heathrow Airport.
Amelework Wondemagegne, an official at the Ethiopian embassy in Washington, had tried to claim diplomatic immunity when she was caught at the airport in April with 56 kilograms (123 pounds) of cannabis.
But Isleworth Crown Court in west London jailed her for 33 months after she admitted one count of drug smuggling.
The court had found that the 36-year-old was not entitled to immunity.

Tuesday 31 July 2012

በሙሉነህ ዮሃንስና የውጭ ጉዳይ ምንጮች የተጠናከረ (ጁላይ 31 2012)

የውጭ ጉዳይ ዜናዎች

  • አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ መለስን ሲያስታምም ከርሞ ከብራስልስ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ነው!
  • አምባሳደር ሙሉጌታ አለምሰገድ ባጣዳፊ ቤተሰቡን ወደ ጣሊያን አሸሸ!
  • አሜሪካን ሃገር በአምባሳደርነት ማእረግ ያሉ አራት ዲፕሎማቶች ከአበበ ገላው ጋር በተያያዘ ጠቅልለው እንዲመለሱ ታዘዙ!
  • መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብና የባለስልጣናት ቤተሰቦች ወደ ኬንያ እየተሸጋገሩ ነው!
አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ መለስን ሲያስታምም ከርሞ ከብራስልስ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ነው!
                           
ህወሃት በጫካ እያለ ጀምሮ የድርጅቱን ገንዘብ ውጭ ሃገር በማንቀሳቀስ የሚታወቀውና በአሁኑ ወቅት በEthiopian pm Meles Zenawiምክትል ሚኒስትርንት ስም ውጭ ጉዳይን የሚያዘው ብርሃነ ገብረክርስቶስ

Meles Zenawi
መለስ ዜናዊ ከታመመ ጀምሮ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (ሄድ ኦፊስ) አካባቢ ጠፍቶ መክረሙን በቦታው ያሉ ሰራተኞች አረጋግጠዋል። ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰራተኞች እንዳረጋገጡት ብርሃነ የከረመው ብራስልስ ውስጥ መለስ ዜናዊን በቅርብ ሲያስታምም ነው። የመለስ ዜናዊ የመሞት ዜና በውጭ ጉዳይ አካባቢ የመረበሽ ድባብ እንደፈጠረ የገለጹት የዜናው ምንጮች ብዙ ዲፕሎማቶች ለማምለጥ አጋጣሚ እያመቻቹ መሆኑን ጠቁመዋል። ብርሃነ ገብረክርስቶስ መጠኑ ያልተገለጸ ከፍተኛ ገንዘብ ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ወደብራስልስ ይዞ መሄዱም ተያይዞ ተገልጿል። መለስ ዜናዊ በጸና መታመሙ ከተረጋገጠበት የዋሽንገተን ቆይታ አንስቶ በቅርብ ሲያስታምም የከረመው አምባሳደር ብርሃነ በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ አዲስ አበባ እንደሚገባ ማወቅ ተችሏል። ይህም በራሱ የማስታመሙ ስራ በሰውየው ሞት ምክንያት ማለቁን ይጠቁማል ይላሉ የውጭ ጉዳይ ሰራተኞች። የሚመለሰው አስከሬን ይዞ ወይም ቀብሩን ለማመቻቸት ይሆናል የሚል ግምት አለ።
አምባሳደር ሙሉጌታ አለምሰገድ ባጣዳፊ ቤተሰቡን ወደ ጣሊያን አሸሸ!

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕመም የዋልድባ መነኰሳት ተጠያቂ ተደረጉ


(ደጀ ሰላም፤) ሐምሌ 23/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 30/ 2012)፦ ምሽቱን ወደ ገዳሙ በገቡት ዐሥር ያህል የማይ ፀብሪ
ፖሊሶችና ታጣቂዎች የተወሰዱት ሁለት መነኰሳት አባ ወልደ ጊዮርጊስ ከዋልድባ አብረንታንት መድኃኔዓለም፣ አባ ገብረ ማርያም ጎንዴ ከማይ ለበጣ (የማኅበረ መነኰሳቱ ሰፊው የአትክልት ቦታ) ናቸው፡፡ ሁለቱ አበው መነኰሳት በፖሊሶቹ ተይዘው ከመወሰዳቸው አስቀድሞ በኣቶቻቸው በፖሊሶቹ ፍተሻ እንደተካሄደበት ተገልጧል፡፡ ከፖሊሶቹ አንዲቱ ከጾታዋ የተነሣ ወደ ዋልድባ ለመግባት የማይፈቀድላት ሴት መኾኗ የወረዳው አስተዳደር ለገዳሙ ትውፊታዊ ሥርዐትና ክብር መጠበቅ ያለውን የወረደ ግንዛቤ የሚያሳይ ነው፡፡
ትናንት ምሽት በገዳሙ ውስጥ ከተካሄደው ፍተሻ ሁለት ቀናት ቀደም ብሎ ዓርብ፣ ሐምሌ 20 ቀን 2004 ዓ.ም፣ ከጠዋት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በዋልድባ ዶንዶሮቃ ገዳም የሚገኙ ከኀምሳ ያላነሱ መነኰሳትና መነኰሳዪያት ቤት ቁልፎች በኀይል እየተሠበሩ ፍተሻ እንደተካሄደበት ተመልክቷል፡፡ ኻያ ስምንት ያህል የገዳሙ ማኅበረ መነኰሳት የሁለቱን አባቶች መወሰድ በመቃወም ወደ ማይ ፀብሪ ተጉዘው አቤቱታቸውን ለማቅረብ ወደ ወረዳ ከተማው ከሚወስደው ፅርጊያ መንገድ ሲደርሱ በፖሊሶቹ የኀይል ርምጃ መገታቱ

Sunday 29 July 2012

ህወሃት አባላት ስብሰባ እንዲጠራ እየጠየቁ ነው!



(ልዩ ግምገማ)


ኢ.ኤም.ኤፍ – ከቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ድንገተኛ ህመም በኋላ ከህወሃት አካባቢ መልካም ወሬ አይሰማም። በውጭ ሲታይ አሁንም የጠነከሩ ቢመስሉም ውስጥ ውስጡን ግን መጎሻሸማቸው አልቀረም። በተለይም የህወሃት (ህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ) ሊቀ መንበር የነበረው መለስ ዜናዊ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ተሽሎት ወደ ስራ እንደማይመለስ በመገለጹ፤ ከሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ይልቅ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራላቸው ለጽ/ቤቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምንም ምላሽ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል።
እንደደንቡ ከሆነ የህወሃት ምክትል ሊቀመንበር የሆነው አባይ ወልዱ ስብሰባውን ጠርቶ፤ በጉዳዩ ላይ ከአባላት ጋር መምከር እንደነበረበት ተገልጿል። ሆኖም ተራ አባላት የስብሰባውን መጠራት ሲጠይቁ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የደህንነት ሚንስትሩ “ለአገር ደህንነትና ጸጥታ” በሚል ምክንያት በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ዙሪያ በሚደረጉ ወይም በሚጠሩ ስብሰባዎች ዙሪያ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት የህወሃት፣ ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ኢደህዴን ድርጅቶች በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ጋር በተገናኙ አጀንዳዎች ዙሪያ ስብሰባ እንዳያደርጉ የውስጥ መመሪያ ተሰጥቷል።

አቶ መለስ የማን ናቸው?.........ከዳዊት ዋስይሁን




አቶ መለስ ከዚህ በፊት የራሳቸው እንዳልሆኑ በምርጫ 2010 ወቅት ነግረውናል። እንዲህ አሉን ”ድርጅቴ ቀጥል ካለኝ አሉ ”ታዲያ ይህ ድርጅት የትኛው ነው ብትሉኝ? ያልገባቸው ኢሕአድግ ይላሉ መች ሆነና እሳቸውማ የዚህ ድርጅት ሊሆኑ አይችሉም፣ በመጀመሪያ ኢሕአዲግ የሚባል ድርጅት የለም እሳቸውም ያውቁታል። 

በዚህ ስም የሚጠራ ግን ተለጣፊ ቡድን ኢትዮጵያን ለማከሰስና ለመቦጥቦጥ እንዲያመቸው ህውሓት የፈለፈላቸው ተምቾች ጥርቅም መሆኑን መገንዘብ አለብን። በምንም ቀመርና ቅመማ ብትመረምሩት ኢሕአዲግ ከሕውሓት ውጭ ህልውና እንደሌለው እርግጠኞች ልንሆን ያስፈልጋል፣ እንደውም እነኛ ፓርላማ ተሰብስበው የህውሓትን ግጥምና ድርስት በጭብጨባ ከሚያቆለጳጵሱ እቁባቶች በላይ ይህ እውቀት የተገለጠለት ማንም ያለ አይመስለኝም፣ ነገር ግን ለምንድን ነው የህውሃት ጭሰኛ ሆነው የሚቀጥሉት ብትሉኝ መልስ የለኝም? ሆዳምና ለጊዜያዊ ጥቅም ስብእናቸውን የሸጡ ባሮች ከማለት ውጭ። 

Do Ethiopians Really Need Human Rights? .....by Alemayehu G. Mariam



Written by Alemayehu G. Mariam   
Monday, 02 August 2010
Al Mariam If the silenced majority inside of what has become Prison Nation Ethiopia (PNE) could talk, what would they tell President Obama and Secretary Clinton about US human rights policy? Would they pat them on the back and say, 'Good job! Thank you for helping us live in dignity with our rights protected'? Or would they angrily wag an accusatory finger and charge, 'You speak with forked tongue. You wax eloquent on your lofty principles to us in the morning while you consort with thugs and murderers in the afternoon.'
What would the thousands of political prisoners rotting within the closed walls of dictator Meles Zenawi's prisons say of America's big human rights talk? 'Practice what you preach, Mr. President!' What would Birtukan Midekssa, Ethiopia's No. 1 political prisoner, first woman political party leader in Ethiopian history and the undisputed heroine of 80 million Ethiopians say to President Obama were she allowed to speak to him? 'Mr. President, why do you turn a deaf ear when I have been silenced in solitary confinement?' What would the innocent victims gripped in the jaws of Zenawi's steel vices say to Secretary Clinton in their faint whimpers from the torture chambers? I do not know. What I know for sure is that the silenced majority of Ethiopians does speak loud in bootless cries while gasping for air under the jackboots of a barbaric dictatorship. President Obama, can you hear their deafening silence?