Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday 16 July 2013

ሰበር ዜና፣ ከ42 በላይ የአንድነት ፓርቲ አባላት በአዲስ አበባ ታሰሩ

Millions of voices for freedom - UDJJuly 15, 2013

ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በፖሊስ የታሰሩት የአንድነት አባላት ከ42 በላይ ደርሰዋል ከታሳሪዎቹ ውስጥ ሁለት ሴቶች ይገኙበታል
ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2005 ዓ.ም መንግስት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን የወረዳ አመራሮችንና አባላትን በዘመቻ ማሰር ጀምሯል፡፡ እስከአሁኗ ሰዓትም 42 የሚሆኑ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት በፖሊሲ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች ተዘዋውረው እንደዘገቡት 42 የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላት በፖሊስ እንዲታሰሩ ተደርጓል፡፡ የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ እያሰራጨ ያለውን ህጋዊ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በማደላቸው የተያዙት አባላት ከአዲስ ከተማ 15፣ ከጉለሌ7 ፣ ከየካ 9 እንዲሁም ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ናቸው፡፡
የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠ የሚመስለው ኢህአዴግ በየአካባቢው የአንድነት አባላትን ምክንያት እየፈለገ ማገትና ማሰሩን ገፍቶበታል፡፡
ዛሬ ከታሰሩት 42 የአንድነት ፓርቲ አባላት መካከልባለፈው ሳምንት ቄራ አካባቢ ተመሳሳይ ወረቀት ሲበትኑ በህገወጥ መንገድ በፖሊስ ታስረው የነበሩት ስንታየሁ ቸኮልና ዳንኤል ፈይሳ ዛሬም በድጋሚ ህገወጥ እስር እንተፈፀመባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ዛሬ ህገወጥ እስር የተፈፀመባቸው የአንድነት አባላት የሚከተሉት ናቸው፡-
ስንታየሁ ቸኮል
ዳንኤል ፈይሳ
ኤፍሬም ሰለሞን
ታሪኬ ከፋ
ዘገዬ እሸቴ
ተፈሪ ተሾመ
ሀብታመ አድነው
ፍቃዱ በቀለ
ብስራት ተሰማ
መኳንንት ብርሀኑ
ፋና ወልደጎርጊስ
ሽፈራው ተሰማ
ፋንቱ ዳኜ
ገነት ሰለሞን
አላዛር አርአያ
ሳሙኤል ኢሳያስ
ደመላሽ ሙሉነህ
አማኑኤል መንግስቱ
ታሪኩ ጉዲሳ
አስማረ ንጉሴ
ፍቃደስላሴ ግርማ
አሸናፊ አስማረ
ዳንኤል
ለሚ ስሜ
ሰይፈ
ባዩ ተስፋዬ
ሰለሞን አክሊሉ
ወርቁ አንድሮ
ኃይሉ ግዛው
ሸዋአገኘው ማሞ
ቴዎድሮስ ገብሬ
አክሊሉ ሰይፉ
ንጉሴ ቀነኒ
ደረጀ ጣሰው
ገዛኸኝ አዱኛ
ሰፊው መኮንን
ታደለ ድሪባ
ሀብታሙ ሺበሺ
ሽመልስ ድንቁ
በየነ አበበ

No comments:

Post a Comment