The World Bank has closed its eyes to risks to the human rights of the very people it seeks to benefit, Human Rights Watch said in a report released today. The bank lacks adequate checks to guard against funding human rights abuse. The bank’s board will meet as part of its ongoing policy review, which provides an opportunity to remedy this policy gap, in Washington on July 23, 2013.
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሙሰኞችን በተመለከተ ሲናገሩ፣ ‹‹ወይ እነሱ ያሸንፋሉ ወይ እኛ እናሸንፋለን፤›› ብለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ነገር ግን መንግሥት ሙስናን ለመታገል ደፋ ቀና የሚለውን ያህል በመንግሥት ጉያ ሥር ተሸጉጠው የሙስና ትግሉን በመቀልበስና የሚገኘውን አይስክሬም ለመላስ የቆረጡ እንዳሉ እየታየ መሆኑን የሚገልጹ አሉ፡፡
በሁለቱ አካላት መካከል የሚደረገው ሽኩቻ ወይም ትግል በማን አሸናፊነት እንደሚቋጭ ባይታወቅም አሸናፊና ተሸናፊ የግድ እንደሚያስፈልግ ይታመናል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት እየጨሰ ከሚገኘው የፀረ ሙስና ትግል ባሻገር፣ በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ጉዳዮችን ጥቂት ዓመታት ወደኋላ መለስ ተብሎ ቢመረመርና አሁን ካለበት ደረጃ ጋር ቢመዘን የጉዳዩን አሳሳቢነት መረዳት ያስችላል በማለት የሚገልጹ አሉ፡፡
የቀድሞወ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ አስተዳደር ሥልጣኑን ከእሳት አጥፊው ባለአደራ አስተዳደር ሲረከቡ ወደ ከተማው ይዘው ከመጧቸው ቁም ነገሮች መካከል መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ ሙስናን መታገልና መሠረታዊ የሥራ ሒደት ለውጥ ተግባራዊ ማድረግ ይገኙበታል፡፡


