Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 9 November 2012

ወይዘሮ አዜብ አደገኛ ቦታ "ማኖ" ነኩ........... አቤ ቶክቻው


በዛ ሰሞን አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆኑ የአፍሪካ መሪ ናቸው የሚለው ደግሞ ደግሞ ሲነገረን እንግዲህ እኛ እስከዛሬ ባንሰማ ነው እንጂ አዎ የአፍሪካ መሪ ናቸው ብለን አምነን ቁጭ ብለን ባለበት በዚህ ሰዓት፤ ወሮዋ ብቅ ብለው “መለስ ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ የቀየሰው ስትራቴጂ ነበር!” ብለው ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ተናግረዋል።

እኔማ “አረ ባክዎን መለስ የኢትዮጵያ መሪ ናቸው” “አረ እባክዎን መለስ የአፍሪካ መሪ ናቸው” “አረ እባክዎን እርሳቸው አድሎ አያውቁም” ብዬ ሀገር ይያያዝልኝ እያልኩ በማየው ቪዲዮ ላይ ለፍልፌ ነበር።

ማን ይስማኝ “ኢህአዴግ አፍ እንጂ ጆሮ የላትም” አሉ ፕሮፌሰሩ…! አንድ ወዳጄ “እኚህ ሰውዬ በጥረታቸው ፕሮፌሰር ባይሆኑም ኖር ለዝች ንግግራቸው ብቻ ፕሮፌሰር አደርጋቸው ነበር” ብሎኛል…!

እንደ ወይዘሮ አዜብ ንግግር ከሆነ ይሄ ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል የማድረግ ስትራቴጂ በመለስ የተፃፈ ሲሆን ኢፈርት የተባለው የብዙ ኩባንያዎች እናት በዋናነት ያንቀሳቅሰዋል። እርሱንም እርሳቸው እና መሌ በመላ ያንቀሳቅሱታል።

ኢፈርት በሀብቱ ከኢትዮጵያ የሚደርስበት እንደሌለም “እንቁልጭልጭ” እያሉ ወሮ አዜብ ነግረውናል። ታድያ ይሄ ድርጅት ለትግራይ ብቻ እንዲሰራ ምነው ተፈረደበት!? አቶ መለስስ የኢትዮጵያ መሪ ሆነው ሳለ ስለ አንዲት ክልል ብቻ እንዲህ አብዝተው ሲጨነቁ መኖራቸው ለምን ይሆን!?

ለማንኛውም የወይዘሮ አዜብ ቃለ ምልልስን ልብ ብሎ ለተመለከተው ሰው በዚህ ክፉ ሰዓት እና መጥፎ ቦታ ኳስ በእጅ የመጠፍጠፍ ያክል ነው! እያሉ ብዙዎች እየተናገሩ ይገኛሉ!
http://www.youtube.com/watch?v=34yUalEtrDA&feature=youtu.be

No comments:

Post a Comment