Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday, 26 June 2012

አቶ በረከት ስምኦን መንግስታቸው ስካይፒንና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ለመዘጋት መወሰኑን አመኑ

ሰኔ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል መንግስት ስካይፕንና የኢንተርኔት አገልግሎትን ለመዝጋት ወስኗል በማለት የሚገልጡት የምእራባዊያን ጋዜጠኞች ናቸው በማለት መግለጫ በሰጡ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አቶ በረከት ስምኦን ኢንተርኔት ለቴሌኮም አገልግሎት የመጠቀም ተግባር አገሪቱን ከፍተኛ ገቢ እያሳጣት በመምጣቱ ስካይፒን ጨምሮ ሌሎች የኢንተርኔት የቴሌኮም አገልግሎቶችን መንግስት ለመዝጋት ወስኗል ብለዋል።
የመንግሥት የኮምኒኬሸን ሚኒስትር የሆኑት አቶ በረከት ለኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ሰሞኑን እንደተናገሩት መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የስካይፒ ዓይነት አገልግሎቶች በቴሌኮሚኒኬሸን ዓመታዊ ገቢ ላይ ከፍተኛ ጫና በማሳደራቸው ነው፡፡
አቶ በረከት በእርምጃው የተቃጣውን ትልቅ ገቢ በመመለስ ለተያዙት የባቡር ፣ የስኳርና ሌሎች ፕሮጀክቶች ለመደጎም መታቀዱን ለጋዜጠኞቹ ነግረዋቸዋል፡፡
በኢንፎርሜሸን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ተረቅቆ ለፓርላማ በቅርቡ የቀረበው የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን የሚመለከተው ረቂቅ አዋጅ በህገወጥ የቴሌኮም አገልግሎት አገሪቱ እስከ 83 በመቶ የሚሆን ገቢ እንደምታጣ በመጥቀስ በዚህ ወንጀል ውስጥ ተሰማርቶ መገኘት ከ10-20 ዓመታት እስራትና በዚህ ሕገወጥ አገልግሎት የተገኘ ገቢ እስከ አስር ዕጥፍ የሚደርስ መቀጮ የሚያስቀጣ መሆኑን ተጠቃሚዎችን ደግሞ ከ3 ወራት እስከ 2 ዓመታት እስራትና እስከ 20ሺ ብር መቀጫ የሚጥል ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት ዓርብ ዕለት በጽ/ቤታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት የአቶ በረከት ምክትል የሆኑት አቶ ሸመልስ ከማል ስካይፒ አለመከልከሉን ፣በየድረገጹ የሚነገረው ሁሉ በሬ ወለደ ነው ሲሉ ማሰተባበላቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ሽመልስ ከዚህ ቀደም የአሜሪካንን ደምጽ ለማፈን የመንግስት ዲሞክራሲያዊ ባህሪ አይፈቅድለትም ባሉ በቀናት ውስጥ አቶ መለስ ዜናዊ ቪኦኤን ማፈናቸውን ተናግረው ነበር። አሁን ደግሞ የአቶ ሽመልስ አለቃ አቶ በረከት ስካይፕንና በኢንትርኔት ስልክ የመደወልን አካሄድ እናስቆማለን ማለታቸው የተለያዩ አስተያየቶች እንዲቀርቡ አድርጓል። አንዳንድ ወገኖች ወይ የመንግስት ባለስልጣናት እርስ በርስ አይነጋገሩም ወይም  አቶ ሽመልስ ዬይስሙላ ቃል አቀባይ ናቸው ወይም እርሳቸውን ለማዋረድ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው በማለት አስተያየት ይሰጣሉ።

Monday, 25 June 2012

እየመረረ፣ እያመረረ፣ እያስመረረ…

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
ከኢትዮጵያ ሕዝብ ስንት በመቶው በራሱ ጉዳይ፣ በእህል በውሀው ጉዳይ ከማንሾካሾክ አልፎ አፍ አውጥቶ ይናገራል?፤ ለማንስ ይናገራል?፤ ማንስ ይሰማል?፤ በቴሌቪዥኑ፣ በራዲዮውኑ በጋዜጣዎች የሚነጋገረው በአጠቃላይ አምስት ሚልዮን ይሞላል? ሌላው ሰማንያ አምስቱ ሚልዮን ተመችቶት ነው? የዕለት እንጀራውን ማሳደድ ፋታ አልሰጥ ብሎት ነው? መነጋገሩን ንቆት ነው? ብሶቱን ለመናገር ዕድሉን ባለማግኘቱ ነው? ፈርቶ፣ ጎመን በጤና እያለ ነው? ሌላም ምክንያት ሳይኖር አይቀርም፤ ሁሉም ከተናገሩ ሆድ ባዶ ይቀራል! ሆድ ባዶ ከሚቀር ቁርጠት ይሻላል፤ ቆሽቱ ድብን ቢል ይሻላል፤ አንጀቱ እርር ቢል ይሻላል፤ እንደወጣ ከሚቀር! አዲስ ነገርም መጥቶአል፤ አንዳንድ ጓደኞቻችን ዓለምን ስተዋል፤ ምን ሲደረግ እንደነበረም ሆነ ምን እየተደረገ እንዳለ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም፤ እነዚህ ሰዎች እንኳ ስለምግብ ሊያስቡና መብላትም እንዳለባቸው ረስተዋል፤ ስለዚህ ምንም ችግር የለባቸውም።
እንግዲህ አፍ አውጥቶ ራበኝ፤ ጠማኝ፤ በረደኝ፤ አመመኝ፤ ታፈንሁ፤ ተበደልሁ፤ ተጠቃሁ፤ የሚለው ከአምስት ሚልዮን ግምታችን ውስጥ አራት ሚልዮን ይሆናል? ይህ ወደ እውነቱ የሚጠጋ ከሆነ የተመቸው አንድ ሚልዮን ነው ማለት ነው፤ እንግዲህ ንግግሩ ሁሉ በጠገቡና በተመቻቸው በአንድ ሚልዮንና በተጨቆኑትና በደሃዎቹ አራት ሚልዮን መሀከል ነው ማለት ነው፤ የቀረው ሰማንያ አምስት ሚልዮን የሚሆነው (ከሠላሳ በላይ የሚሆኑ ዩኒቨርስቲዎችንም ጨምሮ) በዝምታ ተውጦአል! (አንድ ሚልዮን፣ አራት ሚልዮንና ሰማንያ አምስት ሚልዮን ግምቶች እንጂ የተረጋገጡ ቁጥሮች አይደሉም፤ ካልተስማማችሁባቸው በራሳችሁ ግምት መለወጥ ትችላላችሁ)።
ደሀውና ጭቁኑ ዕለት በዕለት የብሶቱን ቁስል የሚጎረጉሩት ነገር ያያል፤ ይሰማል፤ የሚሰማው ነገር ሁሉ እውነት መሆኑ ወይም አለመሆኑ ለሱ ጉዳይ አይደለም፤ ለሱ ዋናው ነገር ያሳደረበት ስሜትና የሚፈጠርበት ጥላቻ ነው፣ የምሬቱ ሕመም መባባስ ነው፤ እውነቱን ለማጣራት ጊዜ የለውም፤ በዜና ማሰራጫዎቹ የሚሰማቸውና የሚያያቸው ሁሉ የተቀነባበሩና የተዋቡ ሐሰቶች መሆናቸው ከገባው ቆይቶአል፤
ሕመሙ ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ረሀቡ ሲያመው፣ ሲመርረው፣
ብርዱ ሲያመው፣ ሲመርረው፣
ጭቆናው ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ውርደቱ ሲያምመው፣ ሲመርረው፣
ሲመርረው፣ ሲያስመርረው
መኖር ሲያስጠላው
ሞትን ሲያስመኘው፤
በገዛ እጁ ተቃጥሎ ሲሞት፣ ተሰቅሎ ሲሞት፣ ተኝቶ ሲሞት፣ አንድ በአንድ እያለ አራት ሚልዮኑ ቢያልቅ፣ የደላው አንድ ሚልዮኑ ከዝምተኛው ሰማንያ አምስት ሚልዮን ጋር ቢቀር ምን ዓይነት ማኅበረሰብ ይፈጠራል? እንዲያውስ ማኅበረሰብ የሚባል ነገር ይኖራል?
አረቦቹም እንደኛ መረራቸው፤ አመረሩ፤ አስመረሩ፣ ለየላቸው፤ እነሱ ከአደረጉት ለእኛ ምን አስተማሩ? ለአንድ ሚልዮኑ? ለአራት ሚልዮን አረቦቹ የሄዱበትን መንገድ ጭራሽ አይመኘውም፤ አራት ሚልዮኑ ሁሌም ግራ የገባው በመሆኑ ከትግሉ ሜዳ ካልወጣ አይፎክርም፤ ከትግሉ ሜዳ የወጣ ፉከራ ደግሞ ከቲያትር ቤት ጨዋታ አያልፍም፤ ሰማንያ አምስት ሚልዮኑ የዕለት እንጀራውን ለራሱና ለቤተሰቡ ሲያስብ አምስት ሚልዮኑ ለሚሠሩት ቲያትር ለተመልካችነትም ጊዜ ያለው አይመስልም።
ሊብያውያን የጋዳፊን ጭቆና አስወግደው አሁን እየተደባደቡ ነው፤ ግብጻውያንም ለድብድብ እየተዘጋጁ ይመስላል፤ የመናውያን ደንበኛ ጦርነት ላይ ናቸው፤ በቅርቡ የየመኑ ጄኔራል ተገደለ፤… ሶርያውያን ምናልባት ማንም የማያሸንፍበት በጣም ከባድ የሆነ የጦርነት ሁኔታ ውስጥ ናቸው፤ በእነዚህ የአረብ አገሮች የተፈለገው ምን ነበረ? ምን ተገኘ? ለብዙኃኑ ሕዝብ ሥልጣንን የሚያስረክብ ሁኔታ በአንዱም አገር አልተፈጠረም፤ የዓለም ልዕለ-ኃያላኑም የብዙኃኑን ሥልጣን መረከብ አይፈልጉም፤ ወይም አንዱ ቢፈልግ ሌላው አይፈልግም፤ በሥልጣን ወንበር ላይ ለብዙ ዓመታት ተጣብቀው የነበሩት በግድ ወረዱ፤ ተደራጅተው ለሥልጣን አሰፈስፈው ሲጠብቁ የነበሩት ደግሞ አንዱን ዓይነት ጭቆና በሌላ ዓይነት ጭቆና ለመተካት ተጣደፉ፤ በ1966/67 እድሜያቸው ሃያ ዓመት ግድም የደረሰ በዚያን ጊዜ በኢትዮጵያ የሆነውን ያስተዋሉና የሚያስታውሱ ሁሉ የዚያን ጊዜ ተዋናዮች እነማን ነበሩ? አሰላለፋቸውና ትግላቸው እንዴት ነበረ? ውጤታቸውስ ምን ሆነ? ዛሬ በግብጽ ያለውን ሁኔታ ልብ ላለ፣ ልዩነቱ የኢትዮጵያ ጄኔራሎች ፈቃዱም ወኔውም ስላልነበራቸው የጦር ኃይሉ በሻለቆችና በበታች ሹማምንት መመራቱ ብቻ ይመስለኛል፤ ወይም ከላይ በአቀረብሁት ምሳሌ ለመቀጠል የ1966/67 የኢትዮጵያ የጦር ኃይል በጠቅላላ ከተመቸው አንድ ሚልዮን ጋር ሳይሆን ከአራት ሚልዮኑ ጋር ሲቆም ጄኔራሎቹ ከአንዱ ሚልዮን ጋር ቀሩ።
ስለዚህ በራሳችን ታሪክ በተከታታይ ሀሳብ በጥይት እየተጨናገፈ፣ ሰላም በጉልበት እየታመሰ፣ እውነተኛ እድገት በማታለል እየጫጨ፣ ስምምነትና ትብብር በግል ምኞትና በፍቅረ ንዋይ እየመነመነ፣ አፈና ጥላቻን እየወለደ፣ ጥላቻም አፈናን እየወለደ፣ አንዱ ሌላውን እያስመረረው፣ የመረረው እያመረረ ሠላሳ ስምንት ዓመቶች ቆጥረናል፤ ከዛሬዎቹ አንድ ሚልዮን ጋርም ሃያ አንድ ዓመቶችን ቆጥረናል፤ እየመረረንም፣ እያስመረረንም ምንም አልተማርንም? አናሳዝንም?

Sunday, 24 June 2012

ፍትህን እና አልሸባብን ምን አገናኛቸው?

በተመስገን ደሳለኝ
እንደመንደርደሪያ
አዲስ ዘመን እና በተመሳሳይ መስመር የተሰለፉ ሚዲያዎች (አይጋ ፎረም፣ ዋልታ እና ዛሚ) በፍትህ ጋዜጣ ላይ ‹‹አርማጌዲዮን›› መጀመራቸው ይታወቃል። ሆኖም ለረጅም ጊዜ ምላሽ የመስጠት ፍላጐት ስላልነበረኝ ‹‹ውሾቹ ይጮኻሉ፤ ግመሉ…›› በሚል ብሂል ነበር ለማለፍ የመረጥኩት። አሁን ግን ይህ ውንጀላ አንድ ደረጃ ከፍ እያለ በመሄዱ እና አደገኛ አዝማሚያ እየያዘ በመምጣቱ፤ በአናቱም የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆኔ በአንዳንድ ባልደረቦቼ ላይ ከዚሁ ጫና የመነጨ የስነ ልቦና ተፅዕኖ እያደረሰ በመሆኑ ቢያንስ ህዝብ ይወቀው በሚል መንፈስ ነው ይህንን ፅሁፍ ለመፃፍ የተገደድኩት።
በቅድሚያ ግን አሁንም ከዚህ ቀደም ደጋግሜ እንደገለፅኩት እኔም ሆንኩ ባልደረቦቼ የምናገለግለው አንዱን ለማስደሰት ወይም ሌላውን ለማስከፋት የሚል አላማ ኖሮን አለመሆኑን አፅንኦት መስጠት እፈልጋለሁ። የእኛ አላማ አንድ እና አንድ ነው። ሀገርን ማገልገል እና ለምንወዳት ሀገራችን የዜግነት ግዴታችንን መወጣት። ስለዚህም ፍትህ ምንጊዜም የህዝብ አንደበት እና ጆሮ ሆና ትቀጥል ዘንድ አቅማችን የፈቀደውን ያህል እንሰራለን። ይህንን ግዴታችንን ስንወጣ ህገ-መንግስታዊ መብታችንን አክብረን እስከሆነ ድረስ ደግሞ ለየትኛውም ጫናም ሆነ የፈጠራ ክስ፣ አሊያም ማስፈራሪያ ወይም ማባበያ እጅ የምንሰጥበት ሁኔታ እንደማይኖር ደጋግመን በዚሁ ጋዜጣ፣ በዚሁ ገፅ ላይ ተናግረናል። ይህ አንድ እውነት ነው፡፡ ሌላው እውነት ደግሞ ይኽ ነው፡፡ ሰሞኑን የመጭውን ጊዜ የአደጋ ‹‹ቀለም›› የሚያመላክቱ ምልክቶች በፍትህና አዘጋጆቿ ዙሪያ እያንዣበቡ ነው። ስለነዚህ ምልክቶች ከመነጋገራችን በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ፍትህን በሚመለከት ስለወጡ ፅሁፎች ጥቂት እናንብብ፡፡
የመንግስት አንደበት ምን አለ?
ከተመሰረተበት ዘመን (1933ዓ.ም.) ጀምሮ የመንግስት አይንና ጆሮ ሆኖ ዛሬ ላይ የደረሰው አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚያንፀባርቃቸው አቋሞች እና ለንባብ የሚያበቃቸው መጣጥፎች ‹‹የመንግስትን አቋም›› ያመላክታሉ ወይስ አያመላክቱም? በሚል ክርክር ጉልበት ማባከኑ አስፈላጊ አይመስለኝም፤ ግልፅ ነውና። በዚህ ከተስማማን ደግሞ ከዚህ ቀደም በአዲስ ዘመን ላይ አዲስ ነገር እና አውራምባ ታይምስን በሚመለከት ይታተሙ የነበሩ ውንጀላዎች መንግስታዊ ባለቤት እንዳላቸው እንስማማለን ማለት ነው፤ ከ2002ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ፍትህን የሚመልከቱ የውንጀላ መጣጥፎች የጋዜጣው መለያ ሆነዋል። በተለይ በገፅ 3፤ አልፎ አልፎ ደግሞ በገፅ 11 ላይ ‹‹ፖለቲካ›› በሚል አምድ ስር ነው እነዚህ ውንጀላዎች የሚስተናገዱት። እዚህች ጋር አንድ አስቂኝ ነገር ልንገራችሁ። የአዲስ ዘመን ‹‹ገፅ ሶስት›› በትላልቅ ፊደል ‹‹አጀንዳ/ደብዳቤዎች›› የሚል የአምድ ስም ተሰጥቶት ሲያበቃ ‹‹ርዕሰ- አንቀጽና›› እንዲህ የሚል ማብራሪያ ተለጥፎበታል ‹‹ይህ ዓምድ በተለያዩ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዜጐች ነፃ አስተያየታቸውን የሚሰጡበት ነው››፤ በዚህች ፉገራ ፈገግ ብለን በገፁ ላይ የሚስተናገዱ ፅሁፎችን ብናየው ሙሉ በሙሉ መጀመሪያ ላይ በኢንተርኔት በሚሰራጩ ድረ ገፆች (አይጋ ፎረም እና ዋልታ) ላይ ከታተሙ በኋላ ‹‹የህዝብ አስተያየት›› በሚል የዳቦ ስም ወደአዲስ ዘመን ጋዜጣ ተላልፈው በድጋሚ እንደሚታተሙ እንረዳለን፡፡ መቼም እዚህች ጋርም ለተጨማሪ ጊዜ መሳቃችን አይቀርም ምክንያቱም በመንግስት የሚተዳደረው እና በቂ በጀት የተመደበለት ጋዜጣ ‹‹ፅሁፎችን የማትመው ከኢንተርኔት እየለቃቀምኩ ነው›› እያለን ነውና።
የሆነ ሆኖ አዲስ ዘመን እና ግብረአበሮቹ ለረጅም ጊዜ ፍትህን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ያለእረፍት እየሰሩ መሆኑን የጨረፍታ ግንዛቤ ለመስጠት ያህል የሩቆቹን ትተን የቅርቡን ማለትም በሚያዚያ እና ግንቦት ወር ብቻ የታተሙትን የውንጀላ ጽሑፎች የጥቂቶቹን ርዕሶች ብቻ ላመላክታችሁ፡-
‹‹ተነስ ያሉት እምቢ ቢል በ‹ጊዜ ለኩሉ…›› (የዚህ ፅሁፍ ፀሐፊ የጋዜጣው ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ገፅ ም/ዋና አዘጋጅ የሆነው ሰይፉ ደርቤ ነው፣ ‹‹የገደል ጫፍ ላይ ሩጫ››፣ ‹‹በአዲስ መልክ ሥራ ጀምረናል!› ሌላው የመድረክ የፕሮፓጋንዳ ‹ጭብጥ› ይሆን እንዴ?››፣ ‹‹ፍትህና አምደኞቿን በጨረፍታ›› (ስድስት ክፍል ያለው በስድስት እትም የተስተናገደ)፣ ‹‹የጨለማው ዘማሪዎች መናኸሪያና ደቀ-መዝሙሮቹ›› (በአራት ክፍል ለአራት ጊዜ የታተመ)፣ ‹‹የዋህ ነፍሰ ገዳይ››፣ ‹‹ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚመች ፕሬስ ነፃ አይደለም››፣ ‹‹አንቀጽ 29፣ የፕሬስ ቀንና ማተሚያ ድርጅት››፣ ‹‹በደም የተፃፈው ህገ-መንግስት ያደፈው በማን ነው?››፣ ግራ የተጋባው የፖሊሲ ሰነድ ‹ትንተና›…›› በሚሉ ርዕሶች በሁለት ወር ውስጥ ብቻ በፍትህና ባልደረቦቿ ላይ ያነጣጠሩ አስራ ስምንት (18) ፅሁፎች ታትመዋል።
የፅሑፎቹን ይዘት ስንመለከት ደግሞ ሁሉም ፍትህ በአሸባሪ ድርጅቶች እና በኤርትራ መንግስት በገንዘብ ይደገፋል በሚል መደምደሚያ የሚያልቁ ናቸው። ለዚህ ደግሞ እንደምክንያት የሚያቀርቡት ጋዜጣዋ ያለ በቂ ማስታወቂያ እስከአሁን በህትመት መቆየቷን ነው። ለምሳሌ ‹‹የጨለማው ዘማሪዎች መናኸሪያና ደቀ-መዝሙሮቹ›› በሚል ርዕስ በወጣው ክፍል ሁለት ፅሁፍ ላይ ‹‹ፍትህ ጋዜጣ ባለ16 ገጽ እንደመሆኑ መጠን፣ 6 ገፅ ተኩል የሚጠጋውን ማስታወቂያና 9 ተኩል የሚጠጋውን ገፅ ደግሞ ፅሑፎችን መያዝ ይገባው ነበር። ሆኖም ጋዜጣው ግን 16ቱንም ገፆች ሊባል በሚችል የጭፍን ጥላቻ አሉባልታ መጋለቢያ ጽሑፍ አድርጎ ያለምንም ማስታወቂያ ወጪዎቹን በሙሉ እየሸፈነ ህልውናው ሳይናጋ ገበያው ላይ ከዘለቀ አራት ዓመቱን ሊያስቆጥር ነው።…. የገቢያቸው ምንጭ ከወዴት ነው? የሚለው ጥያቄ በማናቸውም መስፈርቶች ምላሽ የሚያሻው ጉዳይ ነው።›› ይልና ቀጥሎ እንዲህ ሲል ይጠነቁላል ወይም ይወነጅላል ‹‹የገቢ ምንጩም ከእነዚሁ ፀረ-ሰላም ኃይሎች እንደሚሆን ለመገመት አይከብድም። ጋዜጣውም ቢሆን በእነዚህ ኃይሎች የማይደጎም መሆኑን በአሳማኝ አመክንዮ ማረጋገጥ የሚችል አይመስለኝም። በእንካ ሰላምቲያ ዙሪያ ጥምጥም እየሄደ ዓይኔን ግንባር ያድርገው ለማለት ካልፈለገ በስተቀር።››
አሁንም ቆይታችንን ከአዲስ ዘመን ጋር እንዳደረግን እንቀጥልና ‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ-ክፍል ሶስት›› በሚል ርዕስ ከታተመው ፅሁፍ ላይ ሌላ ጥንቆላ እንቀንጭብ ‹‹የፍትህና አምደኞቹን ጀርባ ለማየት ባደረኩት ጥረት የደረስኩበት ነጥብ የባዕድ እጅ ድጋፋቸው የጠላት ገንዘብ ኪሳቸውን መሙላቱን ነው›› ይላል። መቼም አዲስ ዘመን ‹‹ጋዜጣ›› እንጂ ‹‹የስለላ›› /የደህንነት/ መስሪያ ቤት እንዳልሆነ እናውቃለን። ነገር ግን ያለአንዳች ይሉኝታ ‹‹የፍትህና አምደኞቹን ጀርባ ለማየት ባደረኩት ጥረት…›› ይልና ሲሰልለን እንደቆየ ይነግረናል፡፡ አሁን ነው ‹‹እሪ በይ!›› ሀገሬ ማለት፡፡ እንግዲህ አዲስ ዘመን ስለራሱ፣ በራሱ ጋዜጣ ከሰጠን ምስክርነት ስንነሳ ከጋዜጣው ጀርባ እነማን ተሰልፈው የሀሰት ውንጀላ እየለጠፉ እንደሆነ ለመናገር ነቢይ መሆን አይጠይቅም።
‹‹የዋህ ነፍሰ ገዳይ›› የሚል ርዕስ ያለው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ፅሁፍም እንደሌሎቹ ፅሁፎች በጥንቆላ የተገኙ ውንጀላዎችን ዘርዝሮ ሲያበቃ እንዲህ ይልና ይደመድማል፡- ‹‹የተመስገን ‹ተቀጣጣይ› አጀንዳዎቹ ደግሞ የተመስገን ብቻ ሳይሆኑ የግንቦት 7፣ የኦነግና የኦብነግ እንዲሁም የዜሮ ድምር ፖለቲካው ስብስቦች ሁሉ ናቸው። ለዚህ ነው የፍትህና የአምደኞቿ ጭንቀት የሽብር ተግባራቸውን የሚመሩበትን አካሄድ ውሉ እንዳያግድባቸው የፈጠረባቸው ስጋት ነው የምለው።››
እንግዲህ እነዚህን ሁሉ መንግስታዊ ሽብሮችን ነው መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በምክትል ዋና አዘጋጁ ሰይፈ ደርቤ እና በተለያዩ ሰዎች ስም እያተመ በመወንጀል ላይ ያለው። በነገራችን ላይ ጋዜጣው ከፀሀፊዎቹ ጀርባ ማን እንዳለ አልፎ አልፎም ቢሆን ሳት እያለው ይናገራል። ለምሳሌ በስድስት የአዲስ ዘመን እትሞች ላይ በተስተናገደው ‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ›› ፅሁፍ ክፍል አምስት ላይ ድንገት ተነስቶ ‹‹እነሆ የጨረፍታዬን አምስተኛ ክፍል በግሌ ለመፃፍ ስነሳ የመንግስት ማስፈራሪያ ስላለመሆኑ አንባቢያን እንደሚረዱልኝ በማመን ነው›› ሲል የውስጡን ይነግረናል። እዚህ ጋር የሚተኮርበት ነጥብ የዚህ ፅሁፍ ባለቤት ወይም ባለቤቶች እስከ ክፍል አራት ድረስ ሲፅፉ ‹‹መንግስት አልላከኝም›› የሚል ማሳሰቢያ አያይዘው አልፃፉም፡፡ አምስተኛው ላይ ነው ‹‹የአቡዬን መገበሪያ የበላ…›› እንደሚባለው መለፍለፍ የጀመሩት። እናም ከዚህ ‹‹ማሳሰቢያ›› ስነሳ ጋዜጣው ይህን ያለው በራሱ ፍላጎት ነው ለማለት ይቸግረኛል። ምን አልባት የጋዜጣው ባለቤት (መንግስት) ‹‹እንዴት አንድ ጋዜጣን እንዲህ ታስፈራራለህ?›› የሚል ጫና ስለተፈጠረበት ሊሆንም ይችላል እንዲህ በደፈናው ማስተባበል የፈለገው፡፡ ይህ ማስተባበያ ከዚህ ቀደም የታዋቂው አክቲቪስት እና አርቲስት ታማኝ በየነ ወንድም ተወልደ /ተቦርነ/ በየነ በፍትህ ላይ በፃፈው ፅሁፍ ያጣቀሳትን አይነት የጦጢት ታሪክን ያስታውሰኛል፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፤ አንዲት ጦጣ ከዛፍ ስር ቆማ ሳለ ድንገት አንበሳ ወደ እሷ ሲመጣ ታያለች፤ እናም አደጋ ስለሸተታት በፈጣን ሁኔታ ተደግፋው በነበረው ዛፍ ላይ ዘላ ትወጣለች። አያ አንበሶም ‹‹ጦጢት ውረጂ! አልበላሽም›› ይላታል-የሆዱን በሆዱ ይዞ፡፡ ይህን ጊዜም ጦጣዋ ‹‹አልበላሽምን ምን አመጣው›› አለችው ይላል የተረቱ ትርክት። እኔ ደግሞ እንዲህ እጠይቃለሁ አዲስ ዘመን ሆይ! ‹‹በፍትህ ላይ የሚፃፈው ሁሉ የመንግስት ማስፈራሪያ አይደለም›› ማለትን ምን አመጣው?
ከሚያዚያ ወር ጀምሮ በተደራጀ መልኩ መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በፍትህ ላይ አፍራሽ እና ወንጃይ ዘመቻ እንደከፈተ ለማብራራት እየሞከርኩ እንደሆነ ይሰማኛል። በዚህ የውንጀላ ዘመቻ ውስጥም በዋናነት እየተራገበ ያለው ‹‹ፍትህ ያለማስታወቂያ እስከዛሬ ድረስ በገበያ ላይ የቆየችው በአለም አቀፍ አሸባሪ ድርጅቶች፣ በኤርትራ መንግስት፣ በግንቦት 7፣ በኦብነግ፣ በኦነግ፣ በአክራሪ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ… ድጋፍ ነው›› የሚል እንደሆነም ተነጋግረናል። (መቼም ከላይ የተጠቀሱትን ሀገር እና ድርጅቶች በጨረፍታም ቢሆን የሚያውቅ ግለሰብ እነዚህ ኃይሎች ‹‹ፍትህን መደገፍ›› በሚል አጀንዳ ቀርቶ፣ በሀገሪቱ የቀን አቆጣጠር ስርአት እንኳ በጋራ እንደማይስማሙ ይረዳል። ለዚህም ነው አዲስ ዘመን እንዲህ በአንድ ላይ ሊያሰልፋቸው የቻለበትን ምክንያት ከጋዜጣው አለቆች ባሻገር ሰይጣንም ቢሆን አያውቀውም እያልኳችሁ ነው ያለሁት)
የሆነ ሆኖ በተለይም ያለፈው ሳምንት ፍትህ ለንባብ ከበቃች በኋላ ነገሮች እየተበላሹ እየሄዱ እንደሆነ የሚያመላክቱ ‹‹እከሌ›› ወይም ‹‹እከሊት›› የሚል መጠሪያ እና ባለቤት የሌለው መልእክት እየደረሰን ነው። በእርግጥ ለእኔ የደረሰኝን መልእክት ከቀድሞዎቹ የአዲስ ዘመን ውንጀላዎች የተለየ የሚያደርገው የላኪው ማንነት እና የተፃፈበት ቋንቋ የተለየ መሆኑ ብቻ ነው። ምክንያቱም በዚህ መልእክት ላይ ‹‹ላኪ›› ተብሎ የተቀመጠው እንደተለመደው ‹‹አዲስ ዘመን›› ሳይሆን ‹‹አልሸባብ›› የተባለው የሶማሊያ አሸባሪ ድርጅት ነውና፡፡ የመልእክቱ ይዘት ግን አዲስ ዘመን በሚያዚያ እና በግንቦት ወር ፍትህን ሲወነጅልበት ከነበረው በምንም አይለይም፤ ተመሳስሎአቸው ቃል በቃል ነው። ይህንን መመሳሰል ለማስረዳት ሁሉንም እዚህ ቦታ ላይ መፃፉ አንድም የቦታ ጥበት ስላለ፣ ሁለትም አስፈላጊ ባለመሆኑ አንዱን ብቻ መርጬ በሁለት ምክንያት አቀርባለሁ፡፡ የመጀመሪያው ለአንባብያን ግንዛቤ እንዲረዳ የሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው የሚመለከተው አካል እኛ ጋዜጠኞችን ከዚህ መሰሉ ማስፈራሪያ ይጠብቀንና ይከላከለን ዘንድ ግዴታው እንደሆነ ለማሳወቅ ነው፡፡ (ምንም እንኳን አስቀድሞም ቢሆን የሚያውቀው ቢሆንም እንዲህ በህዝብ ፊት ማሳወቁ ቢያንስ ለታሪክ መጥቀሙ ስለማይቀር ነው) መልእክቱ የመጣው ጋዜጣው ላይ በግልፅ በተፃፈ የጋዜጣው የ‹‹ኢ-ሜል›› (E-mail) አድራሻ ሲሆን ሙሉ ቃሉን እንደወረደ ስናነበው እንዲህ ይላል፡-
“To Ato Temesgen Desalegne
Chief Editor of Fitih magazine
Ethiopia
It has to be remembered that AlShebab has assigned me secretly to make propagation activities in Ethiopia, Somaliland, Kenya and Uganda. To accomplish the task we have agreed with you through your representative Ato Mamush Sentie in Eritrea to publish propaganda articles against the Ethiopian government, against the interest of the Ethiopian people and the American government. It has to be remembered that we have paid US dollar 24,000 for 30 consecutive editions. Now alshebab has made strategic change to accomplish its tasks. Therefore we need the 14 edition charges US dollar 11,200 dollar to alshebab. We believe that you will return back the money to our organization. If this is not fulfilled on time you will bear a cost on your representative Ato Mamush Sentie and your life according to the rule of the organization.
Alshebab wins
Ahmedin Nasir”
(ለአቶ ተመስገን ደሳለኝ
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ
ኢትዮጵያ
እንደሚታወሰው አልሸባብ በኢትዮጵያ፣ በሱማሌላንድ፣ በኬንያ እና በኡጋንዳ የፕሮፓጋንዳ ስራ እንድሰራ በሚስጥር መድቦኛል። ይህንኑ ግዴታዬን ለመወጣት በአንተ ጋዜጣ ላይ የኢትዮጵያ መንግስትን፣ የኢትዮጵያ ህዝብን እና የአሜሪካንን መንግስት ጥቅም የሚጎዳ የቅስቀሳ ፅሁፎች ይታተሙ ዘንድ አቶ ማሙሽ ሴንጢ በተባለው ተወካይህ አማካኝነት ኤርትራ ውስጥ ተስማምተን ነበር። እንደምታውቀውም ለ30 ተከታታይ እትምች 24,000 የአሜሪካን ዶላር ከፍለንሃል። አሁን ግን አልሸባብ ዕቅዶቹን ለመፈፀም የስልት ለውጥ አድርጓል። ስለዚህም 11,200 የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን የ14 እትሞች ክፍያ ለአልሸባብ እንዲመለስ እንፈልጋለን። ይህንን ገንዘብ ለድርጅታችን ትመልሳለህ ብለንም እናምናለን። ነገረ ግን ምናልባት ይህ ሁኔታ በሰዓቱ ባይሳካ በድርጅቱ ህግ መሰረት በአቶ ማሙሽ ሴንጢና በአንተ ህይወት ዋጋ ትከፍላለህ።
አልሸባብ ያሸንፋል።
አህመድ ናስር)
እንግዲህ ይህ መልዕክት የተላከው ከአልሸባብ-ለእኔ መሆኑ ነው። በእርግጥ የዚህ መልዕክት ዋናው ቅጅ ሚያዚያ 2/2004 ዓ.ም በወጣው‹‹ፍትህና አምደኞቹን በጨረፍታ-ክፍል ሶስት›› በሚል ርዕስ የታተመው ጋዜጣ ላይ የተጠቀሰ ሲሆን ይህ ደግሞ የእንግሊዝኛው ግልባጭ መሆኑ ነው፡፡ ለማስታወስ ያህልም በጠቀስኩት ቀን ከታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ልቀንጭብላችሁ፡- ‹‹ከምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ለተቀመጠችው ሀገራችን አልሸባብን ጨምሮ ሌሎችን ከውስጥም ከውጭም የፀረ-ሰላም ኃይሎች ያሰባሰበው የኢሳያስ አፈወርቄ መንግስት ናቅፋ እስከፍትህ ቢሮና አምደኞች ኪስ አይደርስም ማለት አይቻልም፤ ይህ ባይሆን እመኛለሁ፤ እኔ ግን በበኩሌ ጠረጠርኩ፤ በርካታ ማሳያዎች አሉኛ›› የሚል ሆኖ እናገኘዋለን። አልሸባብ እንኳን ከፍትህ ጋር የስራ ስምምነት ሊያደርግ ቀርቶ ፍትህ የሚባል የአማርኛ ጋዜጣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስከመኖሩ ያውቃል? የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ መልዕክቱን ስናነብው በእርግጥም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ደጋግሞ ፍትህን ሲወነጀል የነበረበት መልዕክት መሆኑ አያከራክርም። ልዩነቱ የአዲስ ዘመን በአማርኛ ቋንቋ፣ አልሸባብ ላከው የተባለው ደግሞ በእንግሊዝኛ መሆኑ ብቻ ነው። በነገራችን ላይ ይህንን የሀሰት መልእክት ፈጥሮ እኔን ለመወንጀል ያሰበው ሰው ለውንጀላው ከመጣደፉ የተነሳ፣ የላከው መልዕክት እና ከፍትህ ጋር ያቆራኘው አልሸባብ ጭራሹኑ እንደማይተዋወቁ በግልፅ የሚያሳይ ስህተት ሰርቷል። ይኸውም ላኪው የአራት የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ወኪል ነኝ ብሎን ሲያበቃ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በላከው መልዕክት ላይ ግን የኢትየጵያ የስራ ቋንቋ የሆነውን አማርኛ ደባልቆበታል፡፡ ‹‹አቶ…›› እያለ ፅፎ ማለቴ ነው፡፡
መቼም አልሸባብ የተቋቋመውም ሆነ እየታገለ ያለው እንደ አልቃይዳ ‹‹ድንበር የለሽ›› ወይም ሳውዲአረቢያን አልያም ግብፅን በሼሪያ ህግ ላስተዳድር ብሎ አይደለም፡፡ የአልሸባብ አፈጣጠር ግልፅና አጭር ነው፡፡ ይህ አሸባሪ ድርጅት የተመሰረተው ‹‹ሶማሊያ ሀገራችን›› ባሉ የሶማሊያ ተወላጆች ሲሆን አላማቸውም ‹‹ሶማሊያን በሼሪያ ህግ ማስተዳደር›› የሚል እንደሆነ ደጋግመው ገልፀዋል፡፡ እንግዲህ በዚህ ከተስማማን ‹‹በዕቅዴ ላይ ጣልቃ ገቡ›› በሚል ኩርፊያ በኢትዮጵያ፣ በኬኒያ፣ በኡጋንዳ እና ከራሷ ሶማሊያ በተገነጠለችው ሶማሌላንድ ላይ የሽብር ድርጊት ለማካሄድ አፉን በአማርኛ የፈታ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ የፕሮፓጋንዳ ሀላፊ የሚሾምበት ምንም አይነት ምክንያት የለውም፡፡ ስለዚህም የአልሸባብ ወኪል ነኝ የሚለው ሰው ‹‹አቶ…›› የሚለውን የአማርኛ የአክብሮት አጠራር ሳይሆን ‹‹ሚስተር…›› የሚለውን የእንግሊዝኛ አቻ ትርጉምን ነው ይጠቀም የነበረው ማለት ነው፡፡ ይህን አይነት ቅድመ-ጥንቃቄ ቢያደርግ ደግሞ ቢያንስ የእኔ አስፈራሪና ወንጃይ ‹‹ድርሰት›› የተዋጣለት ይሆን ነበር። አሊያም ‹‹አቶ…›› የሚለውን የአማርኛ ቃል የግድ መጠቀም አለበኝ ካለ እንደተለመደው ከአንዱ ኢትዮጵያዊ አሸባሪ ድርጅት ጋር አቆራኝቶ ቢወነጅለኝ የተሻለ ይሆንለት ነበር።
ሌላው የዚህ መልእክት ባለቤት የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ እንደሆነ የሚያሳየው ፍትህን በእንግሊዘኛ ሲፅፍ፣ እንግሊዝኛ ሆሄያት ተጠቅሞ አማርኛ በሚፃፍበት መልክ “Fitih” ብሎ መሆኑን ልብ ስንል ነው። መቼም ‹‹ፍትህ›› የሚለው ቃል የአማርኛ እንጂ የእንግሊዘኛ ቃል አይደለም። ስለዚም ፀሐፊው አልሸባብ ቢሆን ይህንን አፃፃፍ ከየትም ሊያገኘው ስለማይችል ‹‹ፍትህ›› ብሎ ለመፃፍ ሁለት አማራጭ ብቻ ነው የሚኖረው። የመጀመሪያው አማራጭ ከፍትህ ኢ-ሜል አካውንት ላይ ‹‹ፍትህ›› የሚለውን በሚያውቀው እንግሊዘኛ የተፃፈውን መውሰድ ነው። ይህን ቢያደርግ ኖሮ የፍትህ አካውንት ‹‹fetih_gazeta@yahoo.com” የሚል ስለሆነ የማስፈራሪያው ባለቤት ‹‹fitih›› ብሎ ሳይሆን የሚፅፈው ‹‹fetih›› ብሎ ይሆን ነበር፡፡ ሁለተኛው ምርጫው ደግሞ ከፍትህ ዌብሳይት ላይ መውሰድ ነው። ዌብሳይቱ ላይ ያለው “www.fetehe.com” ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያዊ ያልሆነው አልሸባብ ፍትህ የሚለውን የአማርኛ ቃል የዌብሳይቱ መጠሪያ የሆነውን ‹‹fetehe›› ብሎ ይጠቀም ነበር ማለት ነው፡፡ ታዲያ አማርኛ የማያውቀው አልሸባብ “Fitih” የምትለውን በእንግሊዝኛ ፊደል የተፃፈች የአማርኛ ቃል ከየት አመጣት? (እንዴት ነው ነገሩ? አልያም አንድዬውን እኛ እዚሁ አራት ኪሎ ተጎልተን ሳንሰማ አልሸባብ የሚባል ኢትዮጵያዊ ድርጅት ተመስርቷል በሉንና በሳቅ እንፈንዳ? ሌላ ማድረግ ባንችል በሳቅ ራሳችንን ማፈንዳት ማን ይከለክለናል?)
የአልሸባቡ ሰው ፃፈው ከተባለው ተጨማሪ አንድ ስህተት እንምዘዝ፡፡ ደህና! እንደሚታወቀው የእኔ የሀላፊነት ደረጃ ‹‹ዋና አዘጋጅ›› የሚል ነው፡፡ ይህ ሀላፊነት በእንግሊዝኛ ሲሆን ደግሞ ‹‹Editor in chief›› የሚል ይሆናል፡፡ ሆኖም ‹‹ዋና አዘጋጅ›› የሚለውን ቃል ከአማርኛ ወደ እንግሊዘኛ ቃል በቃል ስንቀይረው ‹‹Chief Editor›› የሚል ይሆናል፡፡ ይህ ትርጓሜ ደግሞ አማርኛ ቋንቋን ለማይናገር ሰው ስህተት ሆኖ ሳለ፣ የአልሸባብ ወኪል የተባለው የፃፈው ግን ከአማርኛ በቀጥታ ተርጉሞ ‹‹Chief Editor›› ብሎ ነው፡፡ እዚሁ ጋር ያለው ሌላ ስህተት ፅሁፉን ለመወንጀል የቸኮለ ፀሀፊ እንደፃፈው ያሳየናል፡፡ ምክንያቱም ፍትህ ጋዜጣ ስትሆን፤ ጋዜጣ ደግሞ በእንግሊዘኛ ‹‹News paper›› እንጂ ‹‹Magazine›› አይደለም፡፡ ሜጋዚን ለሚለው ቃል አቻ የአማርኛ ትርጉም ‹‹መፅሄት›› ነው፡፡ አልሸባብ የተባለው ሰው ‹‹Magazine›› እያለ መፃፉን ልብ በሉ፡፡ እዚሁ መልዕክት ላይ አንድ ግጥምጥሞሽ ልጥቀስላችሁ፡፡ ከዚህ ቀደም የፍትህ ሚኒስቴር በበርካታ ክስ በከሰሰኝ ጊዜ ያቀረበው ማስረጃ በተከታታይ የታተሙ 14 የፍትህ እትሞችን ሲሆን፣ አልሸባብም ፍትህ ላይ ቀረኝ አለ የተባለው ሂሳብ የ14 ዕትም ነው፡፡ …ይህ መመሳሰልስ የአጋጣሚ ይሆን? ወይስ…
የሆነ ሆኖ ከዚህ የሀሰት መወንጀያ ለማሳያ ያህል እነዚህን የመዘዝኩት በሀገራችን ዜጎች ምን ያህል በሀሰተኛ ማስረጃ እና ምስክር ለእስር እየተዳረጉ እንደሆነ እንድትረዱት ነው። ከዚህ ውጭ ከአራት ሳምንት በፊት ያቀረብኩላችሁ የሲሳይ አጌና ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› መጽሐፍ ለፍርድ ቤት ይቀርቡ የነበሩ ማስረጃዎች በፎርጅድ እና በሀሰተኛ ምስክርነት የተሞሉ በመሆኑ ራሱ አቃቤ ህግ ለተደጋጋሚ ጊዜ በፍርድ ቤት ሲያፍር እንደነበረ ማስነበቡን አስታውሰን እንለፍ።
በተቀረ በመልዕክቱ ውስጥ አልሸባብ በፍትህ አስራ ስድስት ተከታታይ እትሞች ላይ የሽብር ፅሁፎቹ እንደታተሙለት ገልጿል፡፡ መቼም የትኛውም የፍትህ አንባቢ እንደሚያስታውሰው በፍትህ ላይ አንድም ቀን ቢሆን የኢትዮጵያን ህዝብና የአሜሪካንን መንግስት ጥቅም የሚፃረር ወይም አልሸባብን የሚደግፍ ፅሁፍ ታትሞ አያውቅም፡፡ ይህ ማለት ግን የኢትዮጵያን መንግስት ደካማ ፖሊሲ፣ የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የፕሬስ አፈና፣ የባለስልጣናቶችን ዘረፋና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምክንያታዊ ትችቶች አላቀረብንም ማለት አይደለም፡፡ ህዝብ ማወቅ አለበት ያልነውንም ህገወጥ ድርጊት አጋልጠናል፡፡ ይህ ደግሞ አንድም የሞያ ግዴታችን ሲሆን ሁለትም እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ ሀላፊነታችንን መወጣታችን ነው፡፡ ስለዚህም እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ፍትህን ከአልሸባብ ጋር አያይዞ መወንጀሉ ክፉ ጥርጣሬን ያጭራል፡፡ ከጥርጣሬዎቹ ውስጥ ምናልባት የተለመደው የክስ ቻርጅ በዚህ በኩል እንዲያልፍ ለማድረግ ይሆን? የሚለው አንዱ ሊሆን ይችላል፡፡ በመልዕክቱ ላይ የተገለፀውን ዛቻ ተከልሎ በፍትህ አዘጋጆች ላይ የ‹‹ቀይ ሽብር›› እርምጃ ለመውሰድ ያሰበ አካል ‹‹በልጅ አመካኝቶ…›› አካሄድን ለመከተል አስቦ ይሆን? የሚለው ደግሞ ሌላኛው ክፉ ጥርጣሬ ሊሆን ይችላል፡፡ …ጊዜ የሚፈታው ቋጠሮ ነው፡፡
ርዕሰ ጉዳዩን ስናጠቃልለውም እነዚህ በመንግስታዊው ጋዜጣ እና በአፍቃሬ ኢህአዴግ ድረ-ገፅ ከወጡት ቁጥራቸው የበዛ ፅሁፎች መሀከል በጥቂቱ ለማሳያነት ያህል የጠቀስኳቸው ውንጀላዎች በአምባገነዊ ስርዓት ውስጥ ያለውን የነፃ ጋዜጠኝነት ፈተና በበቂ የሚያሳይ ይመስለኛል። ስርዓቱ እዚህ ድረስ ወርዶ ለመወንጀል እየሞከረ ያለው ሀገራችንን ጥለን እንድንሄድ አልያም ራሳችንን በዝምታ እንድንሸብብ ከሆነ፤ የሚሰማ ካለ አቋማችንን በተደጋጋሚ ማሳወቃችንን ብቻ አስታውሶ ከማለፍ ውጭ አማራጭ የለውም፡፡ እንዲሁም የሃገሪቱ ህገ-መንግስት ላይ የሰፈሩ የዜግነት ነፃነት አክባሪ ዕሴቶችን አምነን ስለሀገራችን በዋተትን፣ ለተጎዱና ለተገፉት ወገኖቻችን ባበርን፣ የህዝባችን ያለስጋት በነፃነት የመኖር መሻት ይተገበር ዘንድ በብዕሮቻችን በቃተትን፤ በማንኛውም መልክ ሊመጣ የሚችል አደጋ ካለ ከመቀበል ውጪ ሌላ ምርጫ የለንም። ምክንያቱም ሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ናትና።

Saturday, 23 June 2012

Internet, Skype and Ethiopia

by Yilma Bekele
The origins of the Internet can be traced to ARPANET (Advanced Research Projects Agency Network) that was funded
The Ethiopian government has made using Skype a crime punishable up to fifteen years in prison.
The Ethiopian government has made using Skype a crime punishable up to fifteen years in prison
by the US Department of Defense (DARPA) for use by its research labs in the 1960’s. The Internet as we know moved from connecting research institutions and Universities into commercial use in the middle of the 1980’s.
Today the Internet is a global system of interconnected computer networks. The beauty of the Internet is nobody really owns it. Every computer that is connected to the Internet is part of the network. Your laptop or desktop together with millions of private, public, academic, business, government networks forms part of this vast system of interconnected computers.
The Internet has revolutionized human communication like nothing before. It is the most outstanding innovation in human history regarding communication capability. Our lives have changed dramatically due to the Internet. The great economic boom of the 90’s all over the world can be traced to innovation that accompanied the Internet. Where does our Ethiopia fit in this human advancement story?
I am afraid we are absent or unaccounted for! We are not even in the periphery. Our participation in this humongous, game changer event is nothing to write home about. It is so embarrassing the best option is not to talk about it, discuss it or raise the issue. If our country was a computer it will be considered to be in hibernation mode, not on not off barely alive. The Meles regime and his TPLF party can get all the credit for condemning eighty million people to live in darkness. That is exactly where we find ourselves-in complete darkness and no chance of light at the end of the tunnel either. You think I am exaggerating and being so negative because I am filled with hate. I am afraid that is not so. Look at the table below and you be the judge my friend.
See what I mean? Out of eighty million plus people only half a million Internet users. That leaves seventy nine million five hundred thousand in the dark. Why do you think this is so? Is it because we are poor? We are stupid? Uneducated? Unable to figure how it works? Not interested? Didn’t think it is important? Felt investment in such technology is a waste of time and resources? Or too busy developing other technology? Or you think it could it be due to lack of leadership? As people we are no different than Americans Europeans or our African neighbors. The only thing we see here is the quality of leadership that differentiates our country from others. The leaders set the pace, define the priorities and the people follow.
When it comes to the Internet our leader felt that is not a priority and that is not where our budget should be invested on. Why do you think Ato Meles and company felt the Internet not to be the place to invest and grow? The simple but obvious answer is the word ‘communication’. Communication is knowledge and knowledge is the first causality of a tyrannical regime. Keeping people in the dark is the main goal of a dictatorship. Illiterate people are docile. It is easy to manipulate a damned down population. Internet is the number one enemy of the Ethiopian government. Instead of laying fiber optic to speed up the wiring of our country the Meles regime invests the limited budget in blocking, censoring and spying on the citizen. The last two weeks have been a busy time to the TPLF regime. It has rolled out one draconian law after another to bully, intimidate and ride rough on our people. Here is the evidence.
Skype is a voice- over-Internet Protocol service and software application. Skype allows users to communicate over the Internet using voice, video and instant messaging. As of September of 2011 Skype has over six hundred million users worldwide. The Ethiopian government has made using Skype a crime punishable up to fifteen years in prison.
Tor (short for The onion router) is a system intended to enable online anonymity. The Tor project a 501(c) research/education nonprofit organization distributes the software free of charge. According to the wonderful people of Tor network their ‘client software routes Internet traffic through a worldwide volunteer network of servers to conceal a user’s location or usage from anyone conducting network surveillance or traffic analysis.’ The Ethiopian government is actively blocking Tor network.
There are over eighty million Ethiopians. As of 2012 there are about a million fixed line service users and close to three million mobile users in Ethiopia. It is the lowest teledensity in Africa. There are less than half a million Internet users in Ethiopia and that is in the bottom even for Africa. That number constitutes .06% of the Ethiopian population.
Why is the Ethiopian government enacting such draconian law when you can clearly see Internet does not play any major role in the life of the citizen? Why is the government becoming the laughing stock of the planet by equating phone usage to committing murder? All indications are the issue is not about Skype or Tor but it is all about control and bullying into submission. It is all about instilling fear. Fear is the main currency of a dictator. They are not worried about the .06% but they are very much interested in showing the ninety nine percent who exactly is in charge. In your face is how they like to operate. They are saying we can do anything we want and tough luck there is nothing you can do about it!
Do you think they are crazy? I am afraid not. They have been getting away with that kind of attitude the last twenty years what makes you think it will be different this time? We will talk about it, we will gossip, we will condemn silently ( yechelema gelmecha) and life will go on as usual. Actually that is not true about all of us. There are a few working hard to circumvent this tragedy. Groups such as Ginbot7, OLF, ONLF, ALF, Andenet Party, our independent Web sites, ESAT among others are working day and night to teach, organize and help our people stand up to Woyane abuse.
There are different avenues to fight injustice. There are hundreds of ways to resist oppression. I will paraphrase two Chinese educators on this subject. According to Sun Tzu the ‘best defense is a good offense’ and Mao Zedong followed it with ‘the only real defense is active defense.’ meaning for the purpose of counter attacking and taking offense. I believe the current aggression against our people begs for a robust counter offense. Here I am speaking about cyber warfare.
It is about time our people developed this type of self-defense to protect our freedom. It is within our capability and it is our moral duty to protect our country and people. According to a recent Time magazine article that is what the US is helping the Syrian opposition with. Developing a cyber warfare capability. They are training the freedom fighters to resist the Assad regime in the art of circumvention technology. The use of encryption, SIM card in cheap burner phones that can easily be discarded and developing ‘Internet in a suitcase’ to provide Web access when Assad shuts it down is being explored. Apps are being developed that download a panic button that will instantly wipe out contacts and documents from smart phones and computers. They are experimenting with Apps that present a false screen when the wrong security code is entered and Apps that blur the faces of dissidents when posting videos and photos on line. Today the camera is as powerful as the AK47.
It is also important our highly educated lawyers and Human Rights advocates explore the concept of ‘I am just following order’ defense that is sure to be used by those that are doing the dirty work for the minority based illegal regime. Whereas the current Ethiopian Constitution is full of guarantees of rights and freedom to the citizen those that are killing, imprisoning, torturing, spying and using their know how to block and jam should be warned about accountability. They should be made aware of their oath to uphold the Constitution not the rule of one man or a single party. ‘I am just following order’ did not hold water in the Nuremberg trials of Nazi criminals.
Those educated Ethiopians that are enabling the regime to spy on fellow citizens, block Web sites, target emails and social media postings should be warned about the consequences of their actions. They are following illegal and immoral orders given by those that are using force and coercion to stay in power. Sooner or later this house of cards will come tumbling down and it will be time to answer for all those that used their technical know how to hurt their people. Blind allegiance is not a wining strategy or ignorance a valid defense. It is a shame some sell their soul to the devil for fame and fortune.
Read more: http://world.time.com/2012/06/13/hillarys-little-startup-how-the-u-s-is-using-technology-to-aid-syrias-rebels/#ixzz1yXisIkPB

Wednesday, 20 June 2012

World leaders weigh stimulus vs. austerity at G-20



( Chinese authorities have removed their video from YouTube. The video clip shows an ailing Prime Minister Meles Zenawi having talks with Chinese President Hu Jintao in Los Cabos, Mexico, on June 18, 2012). The above picture shows Meles shaking hands with Mexican President Calderon on June 18, 2012. Photo courtesy of Getty images but you can check in this link http://www.youtube.com/watch?v=jfuG5E3AtDM&feature=player_embedded#! )

Tuesday, 19 June 2012

ጠላታችን ማነው?

ዓለማየሁ ገላጋይ
ሮማዊው የታሪክ ሰው Tranquillus suetonius (75-150)ዓ.ም “Lives of the twelve Caesars” የሚል መጽሐፍ አለው። የአሥራ ሁለት ቄሳሮችን ስንክሳር ያካተተበት ሥራው ነው። ከእነዚህ ቄሳሮች መካከል ‹‹እብዱ›› በሚል ተቀጥላ የሚጠራው ካሊጉላን (Caligula) ነው። በእርግጥም አንዳንድ የቄሳሩ ተግባሮች ጤነኞች የሚያከናውኗቸው አይደሉም። ለምሳሌ መኳንንቱና ሹማምንቱ እንዲሁም መሳፍንቱ በተገኙበት አዳራሽ ውስጥ ሚስቱ ቄሶኒያ (Caesonia) እርቃነ-ሥጋዋን እንድትመጣ ያዝዛታል። ልብሷን ጥላ እራቁቷን ስትመጣ የአዳራሹን ሁናቴ ይቃኛል። ከዚህ የሚያገኘውን ትርፍ እራሱ ካሊጉላ ይወቀው። ሌላም የእብድ መዝናኛ አለው። በመኳንንቱ ፊት መኳንንቱ እርስ በእርስ ትግል እንዲገጥሙ ማዘዝ። አንዱ ይጥላል፣ ሌላው ይወድቃል። ካሊጉላ ይስቃል። ቄሳሩ ከሳቀ የተቀረው መኳንንት አያኮርፍም- አብሮ ያውካካል። ከዚህ ትዕይንት ካሊጉላ የሚያተርፈው መዝናናትን ብቻ አልነበረም። ፖለቲካዊ ረብጣም አለው። የወደቀው መኳንንት በጣለው መኳንንት ላይ ያቄማል፤ ጠላትነትም ያበቅላል። እርስ በእርስ ተፈላላጊ ይሆናሉ።
ወደኛ አገር እንምጣ… …ፊታውራሪ ተክለሐዋርያት ተክለማሪያም ‹‹ኦቶባዮግራፊ (የህይወቴ ታሪክ)›› የተሰኘ መጽሐፋቸው ላይ የሚያስተዋውቁን ልጅ ኢያሱም የካሊጉላ ከፊል መንፈስ ያረፈባቸው ናቸው። የተከበሩትን መኳንንቶች ለእረኝነት እንደወጣ ኩታራ ትግል ያጋጥሟቸዋል። ፊታውራሪ ተክለሐዋርያት እንዲህ ይላሉ፡-
‹‹… ታዲያ ልጅ ኢያሱ ቀኛዝማች ወልደአማኑኤልንና ቀኛዝማች ፋሪስን አታገሏቸው። ቀኛዝማች ወልደአማኑኤል በንቀት አስተያየት እያየ ተጋጠመ። (ቀኛዝማች ወልደአማኑኤል በራስ መኮንን ቤት ጉልበታምነቱ የታወቀ ነው።) ቀኛዝማች ፋሪስ ጣለ፣ ልጅ ኢያሱ እያጨበጨቡ ደስታቸውን ገለጡ። እኛ ግን ዐፈርን። ቀኛዝማች ወልደአማኑኤል ተገረመና እንደገና ታገሉ። ቀኛዝማች ወልደአማኑኤል ጣለ።››
በፊታውራሪ ተክለሐዋርያት ግምጋሜ ልጅ ኢያሱ ለመቦረቅ ያመጡት የልጅነት ፍላጐት እንጂ የመኳንንቱን ትግል መግጠም በፖለቲካ ትርፍነት አይተውት አልነበረም። ይሁንና ለታዛቢዎቹ ለእነፊታውራሪ ተክለሐዋርያት ትግሉ ከግለሰቦች አልፎ ብሔርና ሃይማኖት ተኮር ሆኖ ተተርጉሞላቸዋል። በቅንፍ ውስጥ ይሄንን ትርጓሜ ጣል ያደርጋሉ። ‹‹በልባችን ውስጥ የሚታገሉት ወልደአማኑኤልና ፋሪስ አይደሉም ሸዋና ወሎ፣ ክርስቲያንና እስላም ናቸው (አልን)›› ይላሉ። የዚያ ወቅት ፖለቲካ ይሄው ነበር። ከሸዋ ወገን እነደጃዝማች ተፈሪ (ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ)፣ ከወሎ እነራስ አሊ (ንጉስ ሚካኤል) የተፋጠጡበት። ትውልዳቸውንና ሃይማኖታቸውን የወከሉት ቀኛዝማቾች በግጥሚያው አንድ ለአንድ ባይወጡ ምን አይነት ቂም ውስጣቸው ይፈጠር ነበር? በእንዴት አይነት ሁኔታስ ወደበቀል ይለወጥ ነበር?
አብዛኛው መንግሥት የራሱን ፖለቲካዊ ሁኔታና ሥልጣን የሚያስጠብቀው ትኩረት የሰጠባቸውን ‹‹ቀኛዝማች ወልደአማኑኤል እና ቀኛዝማች ፋሪስ›› በጠላትነት አኳኩኖ በማታገል ነው። ለምሳሌ በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን የነበሩ ትግል ገጣሚዎች ‹‹በተወላጅነት›› እና ‹‹በትምህርት›› ሥልጣን የያዙ ሁለት ቡድኖች ነበሩ። የእነዚህ ቡድኖች ጠላትነት በአፄ ኃይለሥላሴ የሥልጣን ማስጠበቅ ፖለቲካዊ ፍላጐት የተፈበረከ ቢሆንም ደርግ እስኪመጣ ድረስ እንደተናነቁ ሥራ መሥራት ተስኗቸው ቆይተዋል። አንዴ አንዱ ሲጥል አፄ ኃይለሥላሴ እንደልጅ እያሱ ያለ ግን ስውር ጭብጨባ በማካሄድ ደስታቸውን ሲገልጡ፤ ሌላ ጊዜ ሌላው ሲጥል እንዲሁ ሲደረግ በመካከል ዋነኛው የንጉሱ ሥልጣን ከመካከላቸው የሚማትረው ሳይኖር ለረጅም ጊዜ ቆይቷል። ስለዚህ ጉዳይ ባህሩ ዘውዴ እንዲህ ይላሉ፡-
‹‹የአብዛኛዎቹ ሚኒስትሮች የመደብ ጀርባም በንጉሰ ነገሥቱ ፊት ነፃ አቋም ለመውሰድ የሚያደፋፍር አልነበረም። ብዙዎቹ የመሣፍንት ወገን ባለመሆናቸውና ሹመቱና ክብሩንም በቀጥታ ከንጉሠ ነገሥቱ ያገኙ በመሆናቸው ታማኝነታቸው የተረጋገጠ ነበር። በዚህም አኳኋን ንጉሠ-ነገሥቱ ሚኒስትሮቹን የመሣፍንቱን ኃይል ለመቋቋም አይነተኛ መሣሪያው አድርጓቸው ነበር። የድህረ 1933 የኢትዮጵያ ፖለቲካ አንዱ ገፅታ ይህ በመኳንንቱና በመሣፍንቱ መካከል ይካሄድ የነበረው ስውር ትግል ነበር ማለት ይቻላል።›› (‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ…›› ገፅ 213)
በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን በጠላትነት ትግሉን የገጠሙት ከመኳንንቱ ወገን ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ ሲሆኑ ከሚኒስትሮች ወገን ደግሞ የእርሻ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር የሆኑት መኮንን ኃብተወልድ ናቸው። ሁለቱም በሥራቸው የስለላ ቡድን በማቋቋም አንዱ የሌላውን ድክመት ሲያነፈንፍ ይውልና ያድር ነበር።
በደርግ ዘመን ‹‹ቀኛዝማች ወልደአማኑኤልም ሆነ ቀኛዝማች ፋሪስ›› እራሱ ደርግ ነበር። ለጠላት ሌላ ጠላት ፈጥሮ ከማታገል ይልቅ አድሀሪ፣ በዝባዥ፣ ከላሽ፣ ቀልባሽ፣ ገንጣይ፣ አስገንጣይ… የሚለውን እራሱ እጅጌውን ሰብስቦ ይገጥማል። ከጣለ በኋላ በአዋጅ ይፎክራል። የሚወረሰውን እራሱ ይወርሳል፣ የሚገደለውን እራሱ ይገድላል፣ የሚሾመውን እራሱ ይሾማል…። በሽኩቻ ጠላት በጠላት እስኪጣፋ አይጠብቅም፣ ትዕግሥት የለውም። ዘው ብሎ እራሱ አጣጥሞ ቁልጭ ለማለት ይፈጥናል።
ወደዚህ ዘመን እንምጣ…
…ከሁሉም ዘመን እጅግ የከፋው የዚህ ወቅት ሽኩቻ ነው። ያለማጋነን ህዝቡ እንዳለ ‹‹ቀኛዝማች ወልደአማኑኤሎችንና፣ ቀኛዝማች ፋሪሶችን›› እንዲሆን ተጥሯል። በብሔር፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በክልል አስተዳደር፣ በፖለቲካ… እየተናነቀ ሙሉ ትኩረቱን አጠገቡ ያለ ወገኑ ላይ እንዲያደርግ እየተሴረ ነው። በገዢዎች የተመደበለትን ተጋጣሚ የመጣል ባዕድ ትልም ግቡ አድርጐ እንዲቀርና ወደላይ እንዳያማትር በዕለት ተዕለት ሽኩቻ እርስ በእርሱ እንዲጠላለፍ ተደርጓል። ከበድ ያሉትን አገር አቀፍ ጉዳዮች ትተን በህግ፣ በፖሊሲና በደንብ እየታከኩ የሚጠሩትን የእርስ-በርስ ጠላትነቶች እንመልከት።
የልማት ተነሺ በመሆናችን ስንት የቀበሌ ነገሥታት እያጣደፉና እያክፋፉ እንድንጠላቸው አደረጉን? መኖሪያችንን በላያችን ላይ ለማፍረስ ሲቋምጥና ሲቁነጠነጥ በማየት ስንት አፍራሽ ግብረኃይል ላይ ቂም ያዝን? ስለመፈናቀሉ
በመደስኮር በቁስላችን እንጨት እየሰደደ ስንቱ ጠላታችን ሆነ? በቤት ግምት ወሽመጣችንን ከቆረጠ ስንት ባለስልጣን ጋር ተቂያቂያምን? ያልተገባ፣ የተጋነነ የቤት ግምት የወሰደ ስንት ጐረቤት ታዘብን?...
….ደግሞ በተከራይ አከራይ ያልተብላላ ደንብ ስንቱ ተባላ? ስንቱስ ስንት የዘለአለም ባላጋራ አፈራ? ምን ያህሉስ ለመጋደል ተፈላለገ? እኔ እንኳን ሦስት አሰቃቂ የተከራይ አከራዮች ጭፍጭፍ አጋጥሞኛል። ሃያ ሁለት አካባቢ ገብርኤል ሆስፒታል መስመር፣ አትክልት ተራ እና ካሳንቺስ። ካልወረስክ መንግሥት ይወርሰዋል የተባለ ተከራይ ምርጫ በማጣት ከአከራዩ ጋር ጥርስ ከተናከሰ በኋላ እንደገና መልስለት በሚል የመንግሥት ትዕዛዝ ነው እንደጐሣ ወረራ በገጀራ ሲጨፋጨፉ የታዩት።
….እናስ? ልጅ ኢያሱ ያታገሏቸውን ቀኛዝማች ወልደአማኑኤልንና ቀኛዝማች ፋሪስን አልሆንም? ያታገለንን ትተን የታገለንን አልጠላንም? ከመታገላችን የሚያተርፈውን ‹‹የፖለቲካ ቁማርተኛ›› አልፈን የኛ ብጤ ሰለባውን ጠላት አላደረግንም? ለመሆኑ ጠላታችን ማነው?