ዶክተር እሌኒ ከያራ ያገኙትን ሽልማት ለበጐ አድራጐት ድርጅት ማቋቋሚያ ሊያውሉት ነው
በዳዊት ታዬ
በዳዊት ታዬ
የኢትዮጵያ የምርት ገበያ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር እሌኒ ገብረ መድህን በግብርና ግብዓት አምራችነቱ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚታወቀው ያራ ፋውንዴሽን የዘንድሮ ተሸላሚ በመሆን የተበረከተላቸውን 30 ሺሕ ዶላር ለታዳጊ
ሴቶች በጐ አድራጐት ድርጅት ማቋቋሚያ እንደሚያውሉት ገለጹ፡፡
ዶክተር እሌኒ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ 30 ሺሕ ዶላሩን ለታዳጊ ሴቶች ድጋፍ ለማድረግ እንዲወስኑ ያደረጋቸው
በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል ታዳጊ ሴቶች ወደ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳይሸጋገሩ ትምህርታቸውን የሚያቋርጡባቸው
አጋጣሚዎችን በመመልከታቸው ነው፡፡
በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ታዳጊ ሴቶች የወንዶችን ያህል ዕድል ኖሯቸው ትምህርታቸውን ለመግፋት ብዙ ሳንካ ያለባቸው በመሆኑ፣ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊገቡ ይችሉ የነበሩ ሴቶች ቁጥር እንዲቀንስ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ እንዳለውም ያስታውሳሉ፡፡
ለታዳጊ ሴቶች ሊሰጥ የሚችለውን ድጋፍ በቋሚነት ለማስቀጠልም 30 ሺሕ ዶላሩ እንደመነሻ በማድረግ አንድ የበጐ አድራጐት ማዕከል የሚያቋቁሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉም በተመረጡ የክልል ከተሞች ውስጥ ጽሕፈት ቤት ኖሮት የሚሠራ ሲሆን፣ ሥራው በቋሚነት እንዲቀጥል ለማድረግ ደግሞ ሌሎች ዕርዳታ ሰጪና ስፖንሰሮች እንዲካተቱበት ይደረጋልም ብለዋል፡፡
በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ታዳጊ ሴቶች የወንዶችን ያህል ዕድል ኖሯቸው ትምህርታቸውን ለመግፋት ብዙ ሳንካ ያለባቸው በመሆኑ፣ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊገቡ ይችሉ የነበሩ ሴቶች ቁጥር እንዲቀንስ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ እንዳለውም ያስታውሳሉ፡፡
ለታዳጊ ሴቶች ሊሰጥ የሚችለውን ድጋፍ በቋሚነት ለማስቀጠልም 30 ሺሕ ዶላሩ እንደመነሻ በማድረግ አንድ የበጐ አድራጐት ማዕከል የሚያቋቁሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉም በተመረጡ የክልል ከተሞች ውስጥ ጽሕፈት ቤት ኖሮት የሚሠራ ሲሆን፣ ሥራው በቋሚነት እንዲቀጥል ለማድረግ ደግሞ ሌሎች ዕርዳታ ሰጪና ስፖንሰሮች እንዲካተቱበት ይደረጋልም ብለዋል፡፡



