Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Wednesday 11 July 2012

የእለተ ረቡዕ ማስታወሻ

ዳዊት ዋስይሁን

ይህን ዜና ወዳጄ የላከኝ መልእክት ነው እኔ ለአንባብያን እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ !!

·        እለቱ ረቡዕ ከጠዋቱ  3፡30

የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ዘነበወርቅ አካባቢ በሚገኘዉ ፖሊስ ጣቢያ ተይዘዉ መወሰዳቸዉተሰማ:: ዘነበወርቅ አካባቢ መኪናቸዉን ካስቆሙዋቸዉ ቡሀላ ሁለታችሁንም ስለምንፈልጋችሁ ተብለዉ 2 ቁጥር ፒካፕ መኪና ጭነዎቸዉ የወሰዱዋቸዉ ሲሆን እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ተገልጿል ::ሙስሊሙ ለምን እንደታሰሩ እስኪጣራ ድረስ በተለመደዉ ትዕግስ እንድንጠባበቅ እናሳስባለን!!!

እንዲሁም ከወደ ደሴ ደግሞ ሼህ መከተ ሙሄ በደሴ ከተማ ከሆቴላቸው ሳሉ ታፍነው ተወሰደው የት እንዳሉ አየይታወቅም !!!

አጭር ማሳሰቢያ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ከመቅስፈት በስፋት የተሰራጨ መልእክት!!



የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና ኡስታዝ አህመዲን ጀበል የእገታ ድራማ በታጋቾች ሲገለጥ

አልሀምዱሊላህ በሰላም ተፈተናል፡፡ ዛሬ ጠዋት 3፡30 ላይ ከሰፈር ከአቡበከር ጋር ሆነን ወደ ኮሚቴው ስብሰባ ስንሄድ ከወይራ ወደ ዘነበወርቅ ሰፈር ልንደርስ ስንቃረብ መንገድ ላይ ፒክአፕ መኪና መንገድ ዘጋችብን፡፡ ዘለው 4 ሰዎች ወረዱ፡፡የመኪናውን በር ለመክፈት ተጣጣሩ፡፡ የሲቪል ልብስ ስለለበሱ ማናችሁ? መታወቂያችሁን አሳዩን ብንል ቆጣ ብለው አሳዩ፡፡ ሁለቱ የፖሊስ መታወቂያ ይዘዋል፡፡ ከፍተን ወረድን፡፡ የአቡበከርን መኪናውን ኮልፌ ቀራንዮ ፖሊስ ጽ/ቤት በራፍ ላይ አቆምዋት፡፡ ፖሊሶቹ እኛን ይዘው ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ 4 ሰዓት ላይ ደረሰን፡፡ ተፈተሽን ሞባይል፣ ላፕቶፕ፣ ብር፣ዶኩሜንት፣ ቁልፍ፣ ፍላሽ ዲስክ፣ ቀበቶ፣ ማንኛውንም ወረቀት ወስደውብን መዝግበውን ወደ እስርቤት አስገቡን፡፡ ለየብቻ ባዶ ክፍል (5 ሜትር በ5 ሜትር፣ ቁመቱ 4 ሜትር ይሆናል) ዉስጥ አስገቡን፡፡ ክፍሉ ባዶና ቀዝቃዛ ነው፡፡ በሩ ተዘጋብን፡፡ እንደገባሁ አዱሃ ሰገድኩና አንድ ስለ ለውጥ የምታወጋ መጽሐፍ አግኝቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ 40 ገጽ እንደደረስኩ አንድ ደህንነት(ሀላፊ ይመስላል) በ4 ፖሊስ ታጅቦ በሯን ከፍቶ ገባ፡፡ ማነህ? የት ተወለድክ? እድሜ? ወዘተ ጠየቀ፡፡ መጽሐፍ እያነበብኩ ነበርና ደግሞ ታነባለህ? መጽሐፉን ከየት አመጣህ? ሲል ጠየቀ፡፡ ከዚሁ አገኘሁ ብዬ ቀጠልኩ፡፡ ጥለው ወጡ፡፡ 7 ሰዓት ላይ ፖሊስ መጥቶ ቢሮ ይፈልጉሃል፡፡ ብሎ ፖሊስ ይዞኝ ሄደ፡፡ ፖሊሱ አስገብቶኝ ወጣ፡፡ ገብቼ ጠበቅሁ፡፡ ያ የቅድሙ ደህንነት እና ሌላ አጠር ያለ ደህንነት አብረው መጡ፡፡ ዳግም ትውልድህ የት ነው? ብለው ጠየቁ፡፡ ‹‹ጅማ ከተማ›› ስል መለስኩ፡፡የጅማውን ግጭት የት ሆነህ ነው ያስበጠበጥቀው? ሲሉ ጠየቁ፡፡ በንግግራቸው ሳቅሁ፡፡ ቆጣ ብለው ‹‹የብጥብጡ ጊዜ የት ነበርክ?›› ብለው ጠየቁኝ፡፡ ‹‹እዚሁ አዲስ አበባ››፡፡ የት ተማርክ? የት የት ሀገር ሄደሃል? ወዘተ ጠየቁ አከታትለው፡፡ ከዚያም ‹‹ስማ ከጸረ ሰላም ሃይሎች ጋር የምታደርገውን ሁሉንም እንቅስቃሴ መንግሥት ደርሶበታል፡፡ ዝም ሲልህ መንግስት የፈራህ እንዳይመስልህ፡፡ ከዘሬ ነገ ትታረም ይሆናል ብለን ታግሰን ጠብቀን ነበር፡፡›› ሲሉ ተናገሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ሳቅሁ፡፡ ተቆጡ፡፡ ‹‹እኛ ለስብሰባ አልያም እንድትናገር አይደለም፡፡ የመጨረሻ መስጠንቀቂያ ልንሰጥህ ነው፡፡ በየመስጊዱ በሰደቃ ሽፋን ሕዝቡን የምታነሳሳውን ታቆማለህ፡፡ ሕዝቡ ወክሎኛል ብለህ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ካላቆምክ ዋጋህን ታገኛለህ፡፡›› አሉ፡፡ ይህን ሁሉ ሲናገሩ እግሬን አነባብሬ ነበርና ተቆጡ፡፡ ‹‹እግርህን አውርድ›› አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ጣልቃ ገባሁና ‹‹መረጃ ካላችሁ ፍርድ ቤት ዉሰዱና ክስ መስርቱ፡፡ ምን ታስፈራራላችሁ? እንኳን ማስፈራት ለእምነታችን ሕይወት ለመስጠት ዝግጁ ነኝ፡፡ ማስራጃ ካላችሁ ያሻችሁን አድርጉ፡፡›› አልኩ፡፡ ለምን አልፈራም ብለው ነው መሰል ቆመው ቆጣ ብለው ‹‹ላንተ ፍርድ ቤት በመውሰድ ጊዜ አናባክንም፡፡ ዋጋህን እንሰጥሃለን፡፡ አንዲት ችግር ቢፈጠር የመጀመሪው ጥይት አንተ ላይ ነው የሚያርፈው፡፡ ትሰማ እንደሆን ስማ፡፡ መስጊድ እያደራጀህ ታስበጠብጣለህ፡፡›› ሲሉ ተናገሩ፡፡ ካዋጣችሁ ቀጥሉ-ስል ተናገርኩኝ፡፡ ‹‹መንግሥት አንተን ፈርቶ መሰለህ? አንተ ስለመጅሊስ ምርጫ ምን አገባህ? እንቅስቃሴህን አቁመህ እንደ ዜጋ አርፈህ የማትኖር ከሆነ የምናሳይህን እናሳይሃለን፡፡ ኮሚቴ ምናምን ትላለህ? ህገ ወጥ ናችሁ፡፡ ማን መረጣችሁ? ሕዝቡ መንግሥትን እንጂ እናንተን መች መረጠ? ታርፍ እንደሆን ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነው!›› ብለው ጨርሰናል፡፡ ዳግም ‹‹ካዋጣችሁ ቀጥሉ›› አልኩ፡፡ ፖሊሶቹን ‹‹ጠሩና እቃውን ስጡትና ይሂድ›› ብለው ወጡ፡፡ እቃዬን ተቀብዬ 7፡30 ላይ ከዚያ ወጣሁ፡፡ ስወጣ አቡበከር ቀድሞኝ ወጥቶ ነበርና ከዚያ ሄድን፡፡ እርሱም እንደኔ ተመሳሳይ ሁኔታ ዉስጥ እንደነበረ ነገረኝ፡፡ የሁለታችንም ሂደት ተመሳሳይ ነበር፡፡ የዋህ ሰዎች! ሕጋዊውንና ሕገ መንግሥዊውን የሕዝበ ሙስሊሙን የመብት ማስከበር ሂደት በተራ ማስፈራት ሊያቆሙ ይሻሉን ? አልሀምዱሊላህ በሰላም ወጣን!

ከወደ ደሴ የተሰማ ዜና፣

ቢስቲማ ላይ የሚካሄደው የአንድነትና የሰዶቃ ፕሮግራም  በመከላከያ ሰራዊት ተከቦ ፕሮግራሙ እየተካሄደ ሲሆን ስርአቱ ሲከናወን የሚያስተባብሩና የሚመሩ ወጣቶች ደግሞ በአካባቢው የደህንነት አካላት ልዩ ክትትል እየተደረገባቸው እንዳለ የአይንእማኞች ገልጸዋል ከታች የሚታየውም ፎቶ ይህንን ያረጋግጣል።


በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመካፈል ከተለያየ ቦታ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የተመመ ሲሆን የወያኔ ሰራዊትም ይህንን እንቅስቃሴ ለመግታት መንገድ በመዝጋት እንዲሁም ትራንስፖርት በማቋረጥ እንቅስቃሴውን ለማስተጓጎል ሙከራ አድርጓል ነገር ግን ማህብረሰቡ ልቡንና ጉልበቱን በማጠናከር ከአጎራባች አካባቢዎች ሁሉ በእግሩ እያቆራረጠ በመምጣት አይበገሬነቱን አሳይቷል ነገር ግን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ወጣቶች ለጥያቄ ተብለው የተወሰዱበት ቦታ እንደማይታወቅ የአይን እማኞች ገልጸዋል በማያያዝም ከቢስቲማ ሃይቅ ወደ ደሴ በመጓዝ ላይ የነበሩ ወጣቶች ሶስት ግዜ በመንገድ ላይ በወያኔ ሰራዊት ታስረው ከቀኑ 10 ከ 30 ከቢስቲማ ሃይቅ ተነስተው ደሴ ከምሽቱ 4 ሰአት 45 ደርሰዋል ይህ ሁሉ የሚከናወነው በፊት አውራሪነት በወያኔ ሰራዊት እየተመራ ነው እንደሆነ ታጋቾቹ ገልጸዋል።

የመለስ ቅዠትና የመጪው እሁድ ሐምሌ 8 ሱናሜ

በመጪው እሁድ ሐምሌ 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት እስከ አሥር ሰዓት ተኩል በአወሊያ መስኪድ ቅጥር ጊቢ በሚካሄደው ህዝባዊ አንድነትና የተቃውሞ ስብሰባ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ ሙስሊም ማህበረሰቦችና ክርስቲያን ወንድምና እህቶች እንዲገኙ ጥሪው በሰፊው በሁሉም ማህበረሰብ ዘንድ እየተዳረሰ ሲሆን ይህንንም ታላቅ የአንድነት ስብሰባ ለማስተጓጎን  የኢህአዴግ ካድሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ተደርሶበታል ፡፡

ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት ላይ በግዳጅ የኢህአዴግ ካድሬ ስብስብ የሆነውን መጅሊስ እና የአህባሽን አስተምህሮ ለመጫን እየሞከሩነው ያሉን የኮሚቴ አባል የገጠሩ ማህበረሰብ በሃይማኖታችን መንግሥት ጣልቃ አይግባብን የሚለውን ተቃውሞ እንዳይቀላቀል መንገድ በመዝጋት፣ የመጓጓዣ መኪኖችን በማገት ሊያደናቅፍ ቢሞክርም ሰው በጋማ ከብትና በእግሩ እየተጓዘ በያካባቢው የሚደረገውን የአንድነት ስብሰባ እንዲሳተፍ ጥሪ ተደረጓል፡፡

የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴ ከታሰሩ ምን መደረግ እንዳለበት የሚገልጽ በማን እንደተዘጋጀ የማይታወቅ መመሪያ በማህበረሰቡ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራጨ ሲሆን ይዘቱም እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡

1.       ሰላማዊ ትግላችንን ያለምንም መደናበር መቀጠል
2.        ኮሚተዎች የሚደርስባቸውን ማስፈራራትና ዛቻ በመረጃ ለህዝቡና ሚዲያዎች ማሳወቅ
3.       ተተኪ አመራሮችን ማዘጋጀት
4.        ለዓለም ዓቀፍ የሰላማዊ መብት ድርጅቶች እየተካሄደ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ማሳወቅ (ህጋዊ ትግላችን አለማቀፋዊ ይዘት እንዲኖረው ማድረግ )
5.        ከታሰሩብን _አላህ አያድርገውና_ በህብረት ረብሻ ሳንፈጥር ወደ ታሰሩበት ቦታ ሄዶ መሰብሰብና የጉዳዩን ግዝፈት ማንጸባረቅ
6.        እነዚህ እንቅስቃሴዎች አዲስ አበባ ሳይገደቡ በሁሉም ክፍለ ሃገራቶች ማንኛውንም መንገድ ተጠቅሞ የሰላማዊውን ትግል ማጠናከር
7.        በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ላይ እየሰሩ ያሉ ሙስሊሞችና ፍትህ ወዳድ የሆኑ ክርስትያን ወገኖቻችን አድማ መምታት
8.        በመጀመርያና ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም በዩንቨርሲቲ ተማሪዎ አድማ ማድረግ
9.        ዲያስፖራ ያሉትም ሰላማዊ ሰልፎችንና የተቃውሞ ደብዳቤዎች መላክ
10.   በፓልቶክ እየተደረገ ያለው ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ ወደ ሶሊዳሪቲነት መቀየር
11.   በመጨረሻም ተውበት በማድረግ ወደ አላህ ተጸተን መመለስና ወደሱ ማልቀስ ማልቀስ

ድል ያለመስዋእትነት እንደማይገኝ ስለምናውቅ 34 ሚልየን ሙስሊም በቂ የሆነ እስር ቤት ካለ ካሁኑ አዘጋጁልን። ልትገሉንም ከሆነ 34 ሚልየን ጥይት አዘጋጁ ነጣጥሎ መምታት የማይገኝ የተስፋ ዳቦ መሆኑን ተረድታችሁ መብታችንን ነጻነታችንን ሳይሸራረፍ መልሱልን
ወላሂ ወላሂ ወላሂ ቃላችን ነው የምንለው ከኮሚቴዎቻችን ጋራ አብረን እንቀበራለን ወይ አብረን ታችንን እናስከብራለን !!
ጁላይ 11፣ 2012
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

No comments:

Post a Comment