Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 29 June 2012

የኦሎምፒክ ችቦ ቅብብል አባል እንዲሆን የተመረጠው ታዳጊ ወጣት ጠፋ

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ቢቢሲ ዛሬ ባወጠው ዘገባ እንደገለጠው ኢትዮጵያዊው የ15 ዓመት ታዳጊ ወጣት ፣ ናትናኤል የማነ፣ የኦሎምፒክ ችቦ ከሚያዞሩ ወጣቶች መካከል በመሆን ወደ እንግሊዟ ኖቲንግሀም ከተማ ባለፈው ሀሙስ አቅንቷል። ይሁን እንጅ ታዳጊው ወጣት ዛሬ ረፋዱ ላይ ከሆቴሉ እንደወጣ አልተመለሰም።
የታዳጊው እንግሊዝኛ ችሎታ ውስን መሆንና መንገዶችን የማያውቅ በመሆኑ ፣ ታዳጊው ችግር ሊፈጠርበት ይችላል በማለት ፖሊሶቹ ስጋታቸውን ገልጠዋል።
ናትናኤል የማነ የኦሎምፒክን ችቦ እንዲያዞሩ ከ20 አገራት ከተመረጡ ታዳጊዎች መካከል ከኢትዮጵያ ተመርጦ የሄደ ነው።
__________________________________________________________

No comments:

Post a Comment