Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 28 September 2012

የሠዓሊያንና ቀራፂያን ማኅበር ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሐውልት አሠራ

Wednesday, 26 September 2012 09:34, By Tamirat Getachew
በታምራት ጌታቸው
ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ሠዓሊያንና ቀራፂያን ማኅበር በሃያ ሺሕ ብር ወጪ ሐውልት አሠራ፡፡
በማኅበሩ የተሠራው ሐውልት ሁለት ሜትር ከፍታ ያለው ሲሆን፣ አቶ መለስ የሰላም ምልክት መሆናቸውን ለማመላከት እጃቸውን አንስተው ለሕዝብ ሰላምታ ሲያቀርቡ የሚያሳይ ሐውልት መቀረጹን ማኅበሩ ገልጿል፡፡ ሐውልቱ በሃያ ሺሕ ብር ወጪ መሠራቱን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ሥዩም አያሌው  ለሪፖርተር ገልጸው፣ የሐውልቱ ሥራ ሙሉ ወጪ በአንድ ድርጅት አማካይነት መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡ ሐውልቱ  የማኅበሩ አባላት በሆኑ አምስት ቀራፂያን በአንድ ወር ውስጥ መሠራቱንም ተናግረዋል፡፡ ገንዘቡ የዋለው ለግብዓት ግዢ ብቻ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕይወት ሳሉ ለአገራቸው ከሠሩት ታሪክ አኳያ ሐውልቱ በብሔራዊ ሙዚየም ውስጥ እንዲቆም የማኅበሩ ፍላጎት መሆኑን አቶ ሥዩም ገልጸዋል፡፡

ማኅበሩ ሐውልቱን በሙዚየሙ ውስጥ ለማቆም በመፈለጉ ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጥያቄ ማቅረባቸውንም አስረድተዋል፡፡ ማኅበሩ ወደፊት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ስም አደባባይ የሚሰየም ከሆነ፣ አምስት ሜትር ከፍታ ያለው ሐውልት ለመሥራት ዝግጁ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

አሁን የተሠራው ሐውልት ሌሎችም በክፍያ እንዲሠሩት ቢደረግ ኖሮ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ያስወጣ ነበር ሲሉ አቶ ሥዩም ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment