Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Friday 20 April 2012

የአሶሳ ሚሊኒየም ፓርክ በእሳት ቃጠሎ ወደመ

ሚያዚያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የአሶሳ ሚሊኒየም ፓርክ ሰሞኑን በደረሰበት የ እሳት ቃጠሎ ሙሉ በሙሉ ወደመ።
መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ የአሶሳን ፖሊስ ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የአሶሳን ሚሊኒየም ፓርክ ሙሉ ለሙሉ ላወደመው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ አንድ አርሶ አደር በቁጥጥር ሥር ውሏል።
መንግስት ፤የእሳት ቃጠሎው የተነሳው በፓርኩ አቅራቢያ የሚገኘው ይኸው አርሶአደር የእርሻ ማሳውን ለማፅዳት የለኮሰው እሳት ወደ ፓርኩ በመዛመቱ ነው ባይ ነው።
ይሁንና ይህ የአሶሳ ፖሊስ ሪፖርትና እና የመንግስት ምክንያት በሌላ ገለልተኛ አካል አልተረጋገጠም።
በአደጋው የወደመው ፓርክ ከከተማው አቅራቢያ ከ2000 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ተከልሎ የለማና 150 ሔክታር መሬት ያህል ስፋት እንዳለው ተመልክቷል።
በእሳት አደጋው ከፓርኩ በተጨማሪ በአቅራቢያው የሚገኙ ስድስት መኖሪያ ቤቶችም ተቃጥለዋል::
የከተማው ነዋሪዎች ከአካባቢው ፖሊሶች ጋር በመተባበር ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ ከተማው ሳይዛመት ሊጠፋ መቻሉ ተገልጿል::
አሶሳ ሚሊኒየም ፓርክ፤ በቀርከሃ፣ በዋንዛ፣ በግራር፣ በሳርና በሌሎች ዕፅዋቶች የተሸፈነ ጥቅጥቅ ያለ ደን የነበረ ሲሆን፤ አሁን ግን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሞ ራቁቱን ይታያል።
አቶ መለስ በሰሞኑ የፓርላማ ንግግራቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ መሬት ባለቤት የሌለው ሆኗል በማለት መናገራቸው ይታወሳል። በክልሉ ያለው ደን በከፍተኛ ደረጃ እየወደመ መሆኑን በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment