Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Wednesday 2 May 2012

ቤንቺ ማጂ ጉራፋርዳ ወረዳ….ፍኖተ ነጻነት


ባለፈው ተከታታይ ሳምንታት በከፍተኛ የክልሉ ባለሥልጣናት ትዕዛዝ ከመኖሪያቸው በመፈናቀል ላይ ያሉት የቤንች ማጂ ዞን ጉራፋርዳ ወረዳ ነዋሪዎች ዛሬም የማፈናቀሉ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሎአል ሲሉ የዜና ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ ምንጮቹ እንደሚሉትከዚህ በፊት 2 በላይ አባወራዎች ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ወደ የተለያየ ቦታ ተበታትነዋል፡፡ መሄጃ የለንም ብለው አዲስ አበባ አዋሬ አካባቢ የነበሩ ወደ ቦታችሁ ትመለሳላችሁ ብለው መልሰው
ቢወሰዷቸውም እስከአሁን ድረስ በሥፍራቸው ላይ አልመለሷቸውም፡፡ በሚዛን ተፈሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ለፊት ሜዳ ላይ ሰፍረው ለሥቃይ ተዳርገዋልይላሉ፡፡ሌሎች ከመኖሪያ ቦታቸው ያልተነሱትን አሁንም ታጣቂዎች በማስገደድ እያፈናቀሉ ይገኛሉ፡፡ የክልሉ ባለሥልጣናትና /ሚኒስትሩ የተፈናቀሉት33 ሰዎች ብቻ ናቸው ቢሉም የማፈናቀል ሥራው ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሎአልይላሉ፡፡

No comments:

Post a Comment