Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Wednesday 2 May 2012

ቤኒሻንጉል ጉምዝ ማቡክ ወረዳ…ፍኖተ ነጻነተ


በተለያዩ ጊዜ ከተለያየ የአገሪቱ ክፍሎች ተንቀሳቅሰው በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልላዊ መንግስት ማቡክ ወረዳ ላይ ሠፍረው በግብርና ይተዳደሩ የነበሩ አማርኛ ተናጋሪ አርሶአደሮች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ በመደረጉ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠናል ሲሉ አማረሩ፡፡ ከሥፍራው ተባረን ባህርዳር የመጣን ነን የሚሉ አርሶአደሮች ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት በአካባቢው ኃላፊዎች አስገዳጅነት 2 በላይ አባውራዎች ከሥፍራው ተፈናቅለናል፡፡ የተሰጠን ትዕዛዝ ወደ ትውልድ ሥፍራችሁ ተመለሱ ብንባልም ትውልድ ሥፍራችን ለመድረስም ከደረስንም በኋላ ቦታ ባለማግኘታችን
ለችግር ተጋልጠናል፡፡ይላሉ፡፡ እነዚህ ተፈናቃዮች ነን የሚሉት ሰባት አባውራ አርሶ አደሮች በትላንትናው እለት ባህርዳር ለምግብ ዋስትና አመልክተው መፍትሔ አለማግኘታቸውን በቅሬታ ገልፀዋል፡፡ አርሶአደሮቹ እንደሚሉት ከመኖሪያ ሥፍራችን ካፈናቀሉን የአካባቢው ባለሥልጣናትና ታጣቂዎች ባልተናነሰ መልኩ በትውልድ ሥፍራችን የሚገኙ የአካባቢው ባለሥልጣናትም በጥላቻ እያመናጨቁን ናቸውይላሉ፡፡ አያይዘውም አቤት የምንልበት ቦታ
አተናል፡፡ ማንም ሊሰማን አልቻለም፡፡ እባካችሁን ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አሳውቁልንሲሉ የድረሱልን ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

No comments:

Post a Comment