Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday 21 August 2012

ሰባት አባላት ያሉት ቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ ተዋቀረ እስከቀብሩ ድረስ የሚቆይ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ታወጀ

ሰባት አባላት ያሉት ቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ ተዋቀረ
እስከቀብሩ ድረስ የሚቆይ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ታወጀ
የጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት በይፋ ከተነገረ በኃላ የመጀመሪያ በሆነው የመንግስት መግለጫ የቀብር አስፈጻሚ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋሙን፣ከዛሬ ጀምሮ እስከቀብር ቀን የሚዘልቅ ብሔራዊ የሐዘን ቀን መታወጁን፣የአገሪቱ ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ አቶ በረከት ስምኦን አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ ጠዋት በሒልተን ሆቴል በሰጡት መግለጫ ብሔራዊ ኮሚቴው የቀብሩን ቀንና ሥነሥርዓት በተመለከተ በቀጣይ መግለጫ እንደሚሰጥ ጠቁመው ጠ/ሚኒስትሩ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተጠባባቂ ጠ/ሚኒስትር ሆነው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡
አቶ በረከት ጠ/ሚኒስትሩ የት አገር እንደታከሙ፣የት አገር እንደሞቱ ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡

No comments:

Post a Comment