Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday 7 August 2012

የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንቅስቃሴ በወያኔና አላሙዲ ላይ እያደረሰ ያለው ክስረት

የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል


ከሃገራቸው ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው የህዝብን ብሶት እንዳያሰሙና ወያኔን በማስወገድ ትግል በቀጥታ እንዳይሳተፉ ለማድረግ አገዛዙ የማይሸርበው ተንኮል የለም። የወያኔ ህልውና መሰረት በማንኛውም መንገድ ህዝቡንና ተቃዋሚውን መከፋፈል በመሆኑ እስትንፋሱ እስካለ ድረስ ስልቱን በመቀያየር መሞከሩ አይቀርም።
በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባህል ፌደሬሽን አመራርን በመያዝ ተልእኮውን ለማስለወጥ ያደደረገው ጥረት በህዝብ ወገኖች ትግል መክሸፉ ይታወቃል። ከዚያም 29ኛውን የአንጋፋው ስፖርት ፌደሬሽን የዳላስ ዝግጅት ለማሰናከልና የህዝብ ወገኖችን ለመነጣጠል AESA ONE የሚባል ምንደኛ ቡድን በሼህ አላሙዲን ገንዘብ በመመስረት፤ በዋሽንግተን ዲሲ “ፌስቲቫል አዘጋጅቻለሁ” ብሎ ነበር። ይህ በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ የተረጨበት የሆድአደሮች ዝግጅት ግን በኢትዮጵያውያን አገር ወዳዶች ጠንካራ ተቃውሞና እቀባ ብኩን ሆኖ ቀርቷል። ይህ ታሪካዊ ድርጊት ወያኔንና አጋፋሪዎቹን የውርደት ማቅ ከማልበሱ በተጨማሪ፤ ግልፅ በሆነ የተግባር አላማ ስር በአንድነት ለተሰለፈ ወገን ያሰበውን ለማሳካት የሚያግደው ሃይል አለመኖሩን አሳይቷል።
በመሆኑም የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል BOYCOTT-TPLF Task Force ይህን በወያኔ ደጀንነት በአላሙዲና ጥቂት ሆድ-አደሮቹ የተቀነባበረውን ESFNA የማፍረስና ኢትዮጵያውያንን የመከፋፈል ሴራ በግንባርና በቁርጠኝነት ላከሸፉ ወገኖች፧ በተለይም በዲሲና አካባቢው ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለውን ከፍተኛ አክብሮትና አድናቆት ይገልፃል። ከዚሁ ባልተናነሰ አለኝታችን ESFNA ነው! አንከፋፈልም! በማለት ወደዳላስ በመትመም 29ኛው የስፖርት ክብረ-በዓል ከመቼውም በበለጠ ኢትዮጵያዊነት እንዲደምቅ ላደረጉ ሁሉ አድናቆታችን ከፍተኛ ነው።
ውድ ወገኖች!
በነፃ መገናኛ ብዙሃን ህብረት የተመሰረተው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል BOYCOTT-TPLF ግብረሃይል ዋና አላማ በወያኔና በሸሪኮቹ የንግድ ተቋማት ላይ ማእቀብ በመጣል ለህልውናው መራዘም አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የውጭ ምንዛሪ ምንጮችን ማድረቅ መሆኑን ማስታወስ እንፈልጋለን። ስለሆነም የማያባራውን የወያኔ ከፋፋይ እንቅስቃሴ ነቅተን እየጠበቅን በሚከተሉት የማእቀብ እቅዶች ላይ በየአካባቢያችን ተደራጅተን እንድንረባረብ እንጠይቃለን።
1ኛ. ፀረ-አላሙዲን ESFNAን የማፍረስ ሙከራና የዲሲው ዝግጅት ቢከሽፍም በዘርፉ የሚካሄደው ትግል ግን አልተጠናቀቀም። በተለይም የዲሲውን ዝግጅት አላማ ቢነግሯቸውና ቢመክሯቸውም አልቀበልም በማለት በአዘጋጅነት፧ በአዝማሪነትና በመሳሪያ ተጫዋችነት፤ እንዲሁም በንግድ ዘርፍ የእለት ትርፍ አገኛለሁ በሚል የተባበሩትን ሁሉ በያሉበት ኢላማ አድርገን ማግለልና ከንግድ ድርጅታቸው ጋር የነበርንን ግንኙነት ማቋረጥ ስለሚገባ ሃገር-ወዳድ
ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከሃዲዎችን አበጥሮ በመለየት በያሉበት የማግለል እርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን።
2ኛ. ብሄራዊ ኩራታችን አድርገን እንመካበት የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ የወያኔና አጋሮቹ ጥገት ሆኗል። አስተዳደሩ በወያኔ ከፍተኛ ሹማምንት ተይዞ ዘረፋና ሙስና ነግሶበታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንጡራ ገቢ አንድም አገዛዙን ለማጠናከርያ፥ ሁለትም ሹማምንቱ ከባህር ማዶ ለከፈቱት የባንክ ሂሳብ ማደለቢያ እየሆነ ይገኛል። ለኢትዮጵያ ህዝብ የተረፈው ነገር ቢኖር ስሙ ብቻ ሆኗል።
ስለዚህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለመብረርና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም የወያኔን ከፍተኛ የገቢ ምንጩን እንድናደርቅ የኢኮኖሙ ማዕቀብ ግብረሃይል በኢትዮጵያና በህዝብዋ ስም ጥሪ ያደርጋል። አንድ ሰውም ቢሆን ለውጥ ማምጣት ይችላልና በግልና በጋራ በምንወስደው እርምጃ ወያኔን በአጭር ጊዜ አዳክመን ውድቀቱን እንደምናፋጥን እርግጠኛ እንሁን።
የኢኮኖሚ ማዕቀብ ግብረሃይል
Email: boycott.tplf@gmail.com
Tel: 703 828 4821

No comments:

Post a Comment