Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Tuesday 22 May 2012

ገዢው ፓርቲ በዋልድባ ከፍተኛ ሰራዊት በማሰማራት አካባቢውን ማረስ መጀመሩ ህዝቡን አስቆጣ

ግንቦት ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ዋልድባ አካባቢ የሚገኙ የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ባለፉት ስድስት ቀናት በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ አካባቢው በመሄድ የሰፈሩ ሲሆን፣ የመከላከያ ሰራዊቱን መስፈር ተከትሎ  አካባቢው መታረስ መጀመሩን ለማወቅ ተችሎአል። የአካባቢው ህዝብ መከላከያ ሰራዊቱ ጋር ተፋጦ የሚገኝ ቢሆንም እስካሁን ድረስ የተፈጠረ ግጭት የለም። አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሰው  የአካባቢው ህዝብ በመንግስት ድርጊት በእጅጉ ማዘኑን ገልጠው፣ በመላው አለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን ተቃውመው እንዲነሱ ጠይቀዋል።
መንግስት በዋልድባ ገዳም አካባቢ የጀመረው የሸንኮራ አገዳ ተክል እንቅስቃሴ ኢትዮጵያውያንን እያስቆጣ መሆኑ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment