Welcome

"The thing that lies at the foundation of positive change, the way I see it, is service to a fellow human being." - Lech Walesa

Thursday 10 May 2012

ነፍሰ-ጡሯ ለመገላገል ወደ ሆስፒቷል ሲሄዱ በዘራፊዎች ተደብድበው ህይወታቸው አለፈ…ፍኖተ ነጻነት



ልዩ ቦታው ላፈቶ ኮንዶሚኒየም አካባቢ ነዋሪ የሆኑት / ምስራቅ አክመል ሚያዚያ 17 ቀን 2ዐዐ4 . ከሌሊቱ 73 ሰዓት ላይ ምጥ ይዟቸው ከባለቤታቸው ጋር ሲሄዱ ጎፋ ገብርኤል አደባባይ አካባቢ በዘራፊዎች ተደብድበው ህይወታቸው ማለፉ ተገለፀ፡፡ / ምስራቅ እና ባለቤታቸው አቶ ታሪኩ ጉዲሳ ላዳ ታክሲ ተኮናትረው ሜክሲኮ በሚገኘው ላንድማርክ ሆስፒቷል እየሄዱ ሳለ
ባለታክሲው በድንገት ጎፋ ገብርኤል አደባባይ አካባቢ በድንገት እዚህ ውረዱ ብሎ ካወረዳቸው በኋላ ሁለት ያልታወቁ ሰዎች ወዲያውኑ መጥተው በእጃቸው ያለውን ንብረት መዝረፋቸው ተጠቁሟል፡፡ በወቅቱም ዘራፊዎቹ ያላችሁን ሁሉ አምጡ እያሉ
ሲደበድቡ ነፈሰጡሯ ለመጮህ ሲሞክሩ በኃይል ከጀርባቸው እንደገፈተሯቸውና ወደፊት በሆዳቸው በመውደቃቸው አንድ ድምጽ ካሰሙ በኋላ ፀጥ እንዳሉ ባለቤታቸው አቶ ታሪኩ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም እኔ ነቅቼ እየጮህኩ የድረሱልን የእርዳታ ጥሪ ሳሰማ በአካባቢው ያሉ መኪና ጠባቂዎች ደርሰው ታክሲ ፈልገው እንዳመጡላቸውና ወዲያው ላንድማርክ ሆስፒታል ሲሄዱ ባለቤታቸው ህይወታቸው አልፎ እንደነበር ከዶክተሮቹ መስማታቸውን አቶ ታሪኩ ይናገራሉ፡፡ በስፍራው ጎፋ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቢኖርም ፖሊሶቹ ግን መኪና ላይ ተኝተው መገኘታቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለው ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ክፍል እንደሚገኙ

No comments:

Post a Comment